Skip to content
  Wednesday 10 June 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • News
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የትግራይ ህዝብ የሰላም፣የህልውናው እና ደህንነቱ ዘብ እራሱ ህዝቡ ነው -ዶ/ር አብርሃም በላይ

    May 29, 20210

    በሰሜን ወሎ በኩል ሰርጎ የገባው አሸባሪ በጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን እርምጃ ተወሰደበት

    September 4, 20210

    Ethiopian Envoy Briefs Sudan Based Media On GERD

    July 4, 20210

    በአዳማ ከተማ የምርጫ ሂደቱን ለማወክ በመሞከርና በምርጫ ጣቢያ የጦር መሳሪያ ይዞ በመገኘት የተከሰሱ ተቀጡ

    June 21, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1875
  • Design
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ልጆቻቸው መቀለ ዩኒቨርስቲ የቀሩባቸው ወላጆች የተመድ ፊት እያነቡ ነው “ልጆቻችንን አስለቅቁልን”

    July 23, 20210

    መከላከያ በኦሮሚያና አማራ ክልል የማጽዳት ስራ እንደቀረው አስታወቀ፤ አማራ ክልል መዋቅሩን እያጠራ ነው፤

    September 1, 20230

    “ሁሉንም ያማከለ ዴሞክራሲያዊ ስረዓተ መንግስት ካልተመሰረተ ወቅታዊና ረጅም ጊዜ ያስቆጠሩ ችግሮች ለመፍታት አስቸጋሪ ነው”

    April 17, 20210

    “በተለመደው አሰራር ማስቀጠል የምንችለው ድህነትን ብቻ ነው” ሽመልስ አብዲሳ

    June 3, 20220

    “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች?”

    March 9, 20220
    Prev Next Showing 1 Of 1500
  • Video
    video

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለፓርላማ የሰጡት ማብራሪያ

    July 4, 2024
    video

    የህብታቸውን ምንጭ የሚያውቁ አይሰጉም! ማብራሪያ

    June 22, 2024
    video

    የሀገር አቀፍ የምክክር ሂደት ይፋዊ የማስጀመሪያ ሥነ ስርዓት

    June 4, 2024
    video

    የምክክር ሂደት ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር

    June 4, 2024
    Prev Next Showing 1 Of 5
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • News
  • Design
  • Video
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  መከላከያ “ለሁሉም ልክ አለው፤ ሁለት ቦታ ረግጠው የሚያስወጉና የሚያዋጉ ላይ ማናቸውም ዓይነት እርምጃ ይወሰዳል”
News

መከላከያ “ለሁሉም ልክ አለው፤ ሁለት ቦታ ረግጠው የሚያስወጉና የሚያዋጉ ላይ ማናቸውም ዓይነት እርምጃ ይወሰዳል”

Ethioreview newsEthioreview news—August 1, 20230
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

“የኢትዮጵያ ህዝብ የመጨረሻ ህልውናዬ” የሚለውና ከአብራኩ በውወጡ ልጆቹ ያቆመውን የአገር መከላከያ ሰራዊት ስም ማጠልሸት ከአሁን በሁዋላ በዝምታ እንደማይታይ፣ በአገር ሰላምና ልማት እንቅፋት በሚፈጥሩ አካላት ላይም እገሌ ከእገሌ ሳይል የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ የተቋሙ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት አዳነ “በቃ” ሲሉ ያስታወቁት ከወትሮው በከረረ መልኩ ነው። “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንስቼ እዋጋለሁ ካለ መከላከያ አያርፍም” ሲሉ ስም ባይጠቅሱም የህግ ከለላ ያላቸውም ይሁን ሌሎች፣ ከሃዲድ ወርደው በሁለት እግራቸው የሚረግጡ የወጉና የሚያስወጉ ላይ የትኛውም ዓይነት እርምጃ እንደሚወሰድ ሲያስታውቁ ” በገጠሙን መጥን ስለምንገጥም ወዳጅ ዘመድ ሃይ ይበል” በሚል ምልጃም ጭምር ነው።

  • ህወሃት በፕሪቶሪያው ስምምነት ፍርስራሽ ላይ ! አዲስ የህወሃት የጦርነት ማስጠንቀቂያና “አሸማግሉኝ”
    ቪኦኢ ሰኔ 2026 ዓ.ም (አዲስ አበባ) — በኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት እና በሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ህወሃት) መካከል… Read more: ህወሃት በፕሪቶሪያው ስምምነት ፍርስራሽ ላይ ! አዲስ የህወሃት የጦርነት ማስጠንቀቂያና “አሸማግሉኝ”
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! – ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
    ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ… Read more: ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! – ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
  • የዘለንስኪ ጥሪ፦ “ጦርነቱን ለማቆም ከፑቲን ጋር ፊት ለፊት ለመወያየት ዝግጁ ነኝ”
    VOE NEWS – የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነትን በዘላቂነት ለማቆም አዲስና ታሪካዊ የተባለ የሰላም ጥሪ አቀረቡ።… Read more: የዘለንስኪ ጥሪ፦ “ጦርነቱን ለማቆም ከፑቲን ጋር ፊት ለፊት ለመወያየት ዝግጁ ነኝ”
  • ጃዋር ለአርሲው ግድያ ቀዳሚ ተሟጋች ሆነ፤ “እንቀነጥሳችኋለን” ያለበትን ሜንጫ የት ጣለው?
    ጃዋር “ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምን ወለጋ ሄዱ? የዘር ጭፍጭፍ የፈጠራል” ባለበት ሰሞን በምስራቅ ሃረርጌ ጎረጉቱና መሰላ / እሱ… Read more: ጃዋር ለአርሲው ግድያ ቀዳሚ ተሟጋች ሆነ፤ “እንቀነጥሳችኋለን” ያለበትን ሜንጫ የት ጣለው?
  • ዓለም አቀፍ አጋሮች የኢትዮጵያን 7ኛ አጠቃላይ ምርጫ በበጎ ተቀበሉ፤
    VOE ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. የአውሮፓ ኅብረት (EU) ከሌሎች በርካታ ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመሆን፣ በኢትዮጵያ… Read more: ዓለም አቀፍ አጋሮች የኢትዮጵያን 7ኛ አጠቃላይ ምርጫ በበጎ ተቀበሉ፤

በሸኔ ላይ አስፈጊ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑንን አመልክተው፣ አባ ገዳዎች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ህዝብ ከመከላከያ ጋር ሆኖ ቁጥራቸው የበዛ የሸኔ ታጣቂዎች እጅ እየሰጡ ወደ ሰላማዊ መንገድ መግባታቸውን አመልክተዋል። ከመከላከያ ዱላ የተረፈው ሃይል ተገዶ ወደ ሰላም እስካልመጣ እጣ ፈንታው መጥፋት እንደሆነ ኮሎኔሉ አመልክተዋል።

ኮሎኔሉ ይህን ያሉት የአገር መከላከያ ሰራዊትን አሁናዊ ሁኔታ በማስመልከት መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው። እንደ እሳቸው ገለጻ አሁን ላይ መከላከያ ያለበትን ደረጃና ቁመና ከበፊቱ ወይም ከዛሬ አምስት ወይም ሁለት ዓመት በፊት እንዳልነበረ ጠቅሰው ዘመኑንን በሚመጥን ደረጃ ራሱን እያበቃ በመገሰገስ ላይ ስለሆነ ከቀድሞ ጋር በማመሳሰል ስህተት ውስጥ የገቡ ሀይሎች ወደ ቀልባቸው ሊመለሱ እንደሚገባ ጠቁመዋል። መከላከያ ባለበት የቆመ የመሰላቸውን ” እነሱ ባሉበት የቆሙ ናቸው” ሲሉ ኮሎኔሉ ማስገንዘቢያ ሰጥተዋል። የአገር መከላከያን መስዋዕትነትና በደምና አጥንቱ ያስመዘገበውን ድል ማሳነስም ከህዝብ ጋር መጣላት እንደሆነ የመከላከያ መኮንኖች ” አይበጅም” ሲሉ ደጋግመው በተለያዩ መድረኮች ከህዝብ ጋር ሲመከሩ መናገራቸው አይዘነጋም።

የመግለጫው ዋነኛ ዓላማም ሕዝብ መረጃ እንዲደርሰው ለማድረግና በጠራ መረጃ ቅጥፈትን እንዲመዝን ታስቦ መሆኑን ያመለከቱት ኮሎኔል ጌትነት፣ “እውነተኛ” ሲሉ በክብር የጠሩት የፋኖ ሃይል ከመከላከያ ጋር ዋጋ የከፈለና አብሮ በመናበብ የሚሰራ መሆኑንን አመልክተዋል። ይሁን እንጂ በስሙ የሚነገዱት የማህበራዊ ገጽ ጀግኖች ያልሆነውንና የልተደረገውን በማወጅ መሬት ላይ ካለው እውነት በተለየ የአየር ላይ ማጠልሸት ዘመቻ ላይ መጥመዳቸውን መከላከያ ሊታገሰው ከማይችልበት ደረጃ መድረሱን ገልጸዋል።

More stories

የጉምሩክ ኮሚሽን ኮንትሮባንዲስቶች፣ የወንጀሉ ተባባሪ የኮሚሽኑ ሰራተኞችን እና የፖሊስ አባላትን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ

April 5, 2021

ትህነግ አፍሪካ ሕብረት አስቸኳስ ስብሰባ እንዲቀመጥ ጠየቀ፤ “የትህነግ መታገድ በፕሪቶሪያ ስምምነት እንቅፋት አይሆንም”

May 16, 2025

በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ የተሰጠ መግለጫ

April 22, 2022

“በሽፋን under cover የሚደረግ ምርመራ በፍርድ ቤት ትዕዛዝና በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚከናወን ነው”

June 20, 2025

“እስከአሁን ደረስ ራሳችንን ከመግለጫ ያቀብነው ሰራዊታችን የሚያከናውናቸው ተግባራት በራሳቸው ገላጭ ስለነበሩና በማህበራዊ ሚዲያውም የዚህን ህዝባዊ ሰራዊት መልካም ስራ በመደገፍ ስም የማጥፋት ዘመቻው ሲከሰተም የሚሟገቱ የእውነት ዘቦች በመኖራቸው ነው” ካሉ በሁዋላ “አሁን ግን” አሉ ኮሎኔሉ፣ ” አሁን ግን ሰራዊታችንን ፊት ለፊት ገጥመው ማሸነፍ ያልቻሉ ሀይሎች በተለያየ መንገድ በጀግናው ሰራዊታችን ላይ የሚጎነጉኑት ሴራ ከፍ እያለ በመምጣቱ ውሸት ሲደጋገም እውነት የሚመስላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ሊኖሩ ስለሚችሉ ሰራዊቱ ሸሽቷል ፣ተማርኳል፣ በዚህ ወቷል፣ በዚህ ገብቷል የሚለው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን ለህዝብ ማሳወቅ አስፈላጊ ሆኗል” ሲሉ የመረጃውን አስፈላጊነት አስታውቀዋል።

“ማንም ይሁን ማን” አሉ ኮሎኔሉ፣ ” የመንግስት ሃላፊም ሆነ ሌላ” ካሁን በሁዋላ አስፈላጊ ነው የተባለ ህጋዊም ሆነ የሃይል እርምጃ እንደሚወሰድበት ሊታወቅ እንደሚገባ ” በቃን። ትዕግስትም ልክ አለው” የሚል አዝማሚያ ያለው መልዕክት አስተላልፈዋል። ለሰላም ሲባል መከላከያ ብዙ ጉዳዮችን ሲያስታምም እንደቆየ ያመለከቱት ኮሎኔሉ ይህ አካሄድ ካሁን በሁዋላ እንደማይቀጥል ይፋ አድርገዋል።

በአማራ ክልል አንዳንድ ስፍራዎችን ስም በመጥራት የተዘገቡ ዜናዎችን ” ፍርዱን ለአካባቢው ህዝብ ትቼዋለሁ” በማለት እንዳስታወቁት ከሆነ የሚወራው ወሬ መሬት ላይ ካለው ጋር ዝምድና ቀርቶ ግንኙነት እንደሌለው ነው። ለማሳያ ያህል አካባቢዎችን ጠቅሰው ምን ተፈጥሮ፣ እንዴት መላ እንደተበጀ ካስረዱ በሁዋላ ” ካሁን በሁዋላ ሃዲስ የሳተ አዋጊም ይሁን ተዋጊ፣ አክቲቪስትም ሆነ ፌስቡከኛ አስፈላጊው እርምጃ ይወሰድበታል” ሲሉ በግልጽ ተናግረዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተከበው ነበር፣ በሄሊኮፕተር አመለጡ፣ ጀነራሎች በሃሳብ ተለያዩ፣ ከተማ ነጻ አወጣን … ወዘተ በሚል የሚሰራጩ የዓየር ላይ ወሬዎች እንደሆኑ ካመለከቱ በሁዋላ አጥብቀው ያሳሰቡት ” መከላከያን ማጠልሸት የትም ይሁን የት፣ ማንም ይሁን ማን ይጠየቃል፣ እርምጃ ይወሰድበታል” በሚል ማስጠንቀቂያ ነው። በተለያዩ ወቅቶች “መከላከያ ራሱን ከሚዲያ አዋጊዎች ሊጠብቅና ስሙን ሊያስከብር ይገባል” የሚል ጥያቄ በተቆርቋሪዎች ሲነሳ መቆየቱ አይዘነጋም።

የሰራዊታችን አሁናዊ ቁመናም ሲታይ በወታደራዊ ትብብር፣በውጭ የትምህርት እድሎች፣በዓለምአቀፋዊ እና አህጉራዊ የሰላም ማስከበር ተልእኮዎች አመርቂ ውጤት ማምጣት የቻለ ከዚህ ቀደም በነበሩት ሀገርን የማዳን ዘመቻም ኢትዮጵያን ከመፍረስ በመታደግ የጠላቶቻችንን ህልም ቅዠት ማደረግ የቻለ ትጉህ ሰራዊት እንደሆነ አብይ ማስረጃ አመላክተው ኮሎኔል ጌትነት አዳነ አስረድተዋል። ይህ አቅምና አቋም አስፈላጊ ሲሆን በማናቸውም ወቅቶች ማንም ላይ እንደሚደገም ሳያቅማሙ አመልክተዋል።

“የተለያዩ ግጭቶች በሚስተዋልባቸው አካባቢም ‘ሰራዊቱ ትእዛዝ አልተሰጠንም በማለት የሰው ህይወት እንዲጠፋና ንብረት እንዲወድም አድርጓል’ የሚሉ ትችት ለሚሰነዝሩ አካላት የሰራዊቱን ሕዝባዊ የግዳጅና የግዳጅ አፈጻጸም መርሆች በየደረጃው ጠንቅቆ ካለማወቅ የሚመነጭ እንደሆነ አስታውቀዋል። ካለማወቅ በዘለለም ሆን ተብሎ ሴራ በመጎንጎን የሚመረት የስም ማጠልሸት እንደሆነና ይህ ተራ ስም ማጥፋት ኢትዮጵያን በደሙና አጥንቱ እየተከላከለ ለሚያጸናው ሰራዊት እንደማይመጥን ማስተዋል ለሚችሉ ሁሉ በማሳሰቢያ መልኩ ነግረዋል።

“አድርግ ተብሎ ትእዛዝ በተሰጠው ቦታ ሁሉ ውጤታማ ግዳጅ ሲፈፅም የቆየ ወደፊትም ለታላቅ ተልእኮ ከጊዜ ወደ ጊዜ ራሱን እያዘመነ የመጣ፣ በሰላም ጊዜ የልማት ሰራዊት፣ በጦርነት ጊዜ ደግሞ የጦር ሰራዊት ሆኖ ሀገሩን ከጠላት መንጋጋ በመከላከል በቅንነት ህዝቡን የሚያገለግል ጀግና ሰራዊት ነው” ሲሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ አለኝታ የሆነውን የአገር መከላከያ ሰራዊት ስብዕና ያመላከቱት ኮሎኔል ጌትነት፣ ካሁን በሁዋላ ይህን ስብእና በሚጥስና በሚያቆሽሽ መልኩ ለሚደረግ ማናቸውን ተልዕኮ አንጋቢዎች አስፈጊ ምላሽ እንደሚሰጥ አጠንክረው አስገንዝበዋል።

የመከላከያ ሰራዊቱ በአገር ሰላም እና ልማት እንቅፋት በሚፈጥሩ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ፣ በኢትዮጵያ ልማትና ሰላም ላይ ቀልድ እንደሌለ ያመለከቱት ኮሎኔሉ፣ ” የተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሰራዊቱን ስም የሚያጠለሹ አካላት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ” ሲሉ ከወዲሁ መክረዋል። መከላከያን መንካት ጉዳዩ የኢትዮጵያን ህዝብ የመጨረሻ ቀይ መስመርና የአገሩን ኢትዮጵያን ህልውና መገዳደር እንደሆነ ትህነግ የአገር መከላከያ ላይ ክህደት ፈጽሞ ጥቃት ባደረሰ ወቅት ህዝብ ከዳር እስከዳር በቁጣ መነሳቱ የሚታወስ ነው።

“ነፍጥ በማንገብ በሀገር ሰላምና ልማት ላይ እንቅፋት ለመፍጠር በሚሰሩ አካላት ላይ ሰራዊቱ እርምጃ ይወስዳል” ሲሉ በግልጽ ያስታወቁት ኮሎኔል ጌትነት ቃል በቃል ባይናገሩትም እስከ አፍንጫው ታጥቆና ሚሊሻ ሰብስቦ ኢትዮጵያን ለመበተን የተነሳውን ትህነግን በደፈናው ማሳያ በማድረግ አሁን ላይ መከላከያ የደረሰበትን ደረጃ አክለው መከላከያን እየተነኮሱ ያሉትን አስጠንቅቀቀዋል።

የመከላከያ ሰራዊት አገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን መሰረት አድርጎ ግዳጁን በብቃት እየተወጣ ለህዝብ ይፋ አድርገዋል። በቅርቡ አቶ ዮሐንስ ቧያለው መከላከያ ከአማራ ክልል እንዲወጣ በይፋ መጠየቃቸው ይታወሳል። አቶ ዮሐንስ በአማራ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ መከላከያን “አሸባሪና ወራሪ” ሲሉ ጠርተዋታል። እሳቸው ይህን ቢሉም ኮሎኔል ደመቀ ወዲያውኑ “ከመከላከያ ጋር ተስማምተን እየሰራን ነው። በአካባቢያችን ምን ጦርነት የለም” ሲሉ ለሪፖርተር መናገራቸው ግራሞት ፈጥሮ ነበር።

አዲስ አበባና በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ መከላከያን የሚያራክስ መረጃ ሲያሰራጩ መስማትና ማየት፣ ለዩቲዩብ ገበያ ከተመቸ ምንም ሆነ ምን እንደሚሰራጭ የሚጠቅሱ መንግስት ዝምታ መምረጡ ያመጣው ጣጣ እንደሆነ ገልጸው በርካቶች ቅሬታቸውን ሲገልጹ እንደነበር ይታወሳል። መንግስትን መቃወም፣ መተቸትና ማጋለጥ መረጃ ላይ ተደግፎ ለህዝብ አሳልፎ መስጠት የሚደገፍና የሚበረታታ ቢሆንም ይህ ሲሆን እንደማይታይ አብዛኞች ይስማማሉ።

አቅዶ፣ መርምሮና ሰርስሮ ለህዝብ በሚተቅም ደረጃ የሚሰሩ ሚዲያዎች ባለመኖራቸው ህዝብ ለአሉባልታ፣ ለስድብ፣ ለግልብ አመለካከትና ለፈጠራ ወሬ መጋለጡን የሚናገሩ “አንዳንዶች በዩኒቨርስቲና ታላላቅ ተቋም የሚሰሩ ወገኖች ሳይቀር የንፋስ ዘራሽ ወሬ አስተላላፊና ፈጣሪዎች ሲሆኑ ታይቷል። ይህ ገደብ ሊበጅለት ይገባል። ሁሉም አልፎ ዛሬ መከላከያ ላይ ተደርሷል። መከላከያ ከተነካ ምን ቀረ?” የሚል አስተያየት ስም እየጠቀሱ የሚሰጡም ጥቂት አይደሉም። እነዚህ ወገኖች ” መከላከያችን ሳይነካ መንግስትን እርቃኑ እስኪቀር ለመተቸትና ለማጋለጥ ትንሽ መንቀሳቀስ ለሚወዱ ሚዲያዎች ሁሉ ከበቂ በላይ አጀንዳዎች አሉ” የሚል አሳብም አላቸው።

“የትህነግን መጨረሻ ያየ ከመከላከያ ጋር አጉል አይላፋም፤ ከአገር መከላከያ ጋር መጣላት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ቤት እሳት መለኮስ ነው” ሲሉ አንድ አባት ትህነግ መከላከያ ላይ እጁን ባነሳ ማግስት ማስታወቃቸው ይታወሳል።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

Ethioreview news

A journalist

“ኢቦላ” – ለድሆች የቀረበ የወረርሽኝ ኢንቨስትመንት!?
ያላገገመው አማራ ክልል ዳግም ጦርነት፤ የፌደራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ ተጠየቀ፤ ” ሁሉንም እንዳናጣ” ደመቀ መኮንን
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ህወሃት በፕሪቶሪያው ስምምነት ፍርስራሽ ላይ ! አዲስ የህወሃት የጦርነት ማስጠንቀቂያና “አሸማግሉኝ”

June 6, 20260
News

ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! – ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

June 5, 20260
News

ጃዋር ለአርሲው ግድያ ቀዳሚ ተሟጋች ሆነ፤ “እንቀነጥሳችኋለን” ያለበትን ሜንጫ የት ጣለው?

June 3, 20260
Load more
Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Read also
TOP NEWS

ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed Groups

June 7, 20260
TOP NEWS

Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETV

June 7, 20260
AFRICA

Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science”

June 7, 20260
ENTERTAINMENT

ዶ/ር ጆቴ ታፈሰ- መድኃኒት አልባ ሕመሞችን በሳይንስ መፈወስሰዎችን – ከሞት አፋፍ መመለስ

June 7, 20260
ENTERTAINMENT

ኬሞቴራፒን ማስቀረት የተቻለበት አዲስ ተስፋ፡ የ64 ዓመቷ ካረን የ«ዳግም መወለድ»

June 7, 20260
News

ህወሃት በፕሪቶሪያው ስምምነት ፍርስራሽ ላይ ! አዲስ የህወሃት የጦርነት ማስጠንቀቂያና “አሸማግሉኝ”

June 6, 20260
Load more
Recent Posts
  • ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed Groups June 7, 2026
  • Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETV June 7, 2026
  • Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science” June 7, 2026
  • ዶ/ር ጆቴ ታፈሰ- መድኃኒት አልባ ሕመሞችን በሳይንስ መፈወስሰዎችን – ከሞት አፋፍ መመለስ June 7, 2026
  • ኬሞቴራፒን ማስቀረት የተቻለበት አዲስ ተስፋ፡ የ64 ዓመቷ ካረን የ«ዳግም መወለድ» June 7, 2026
  • ህወሃት በፕሪቶሪያው ስምምነት ፍርስራሽ ላይ ! አዲስ የህወሃት የጦርነት ማስጠንቀቂያና “አሸማግሉኝ” June 6, 2026
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! – ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ June 5, 2026
  • Agricultural Sovereignty, Economic Transformation, and the Defiance of Extremism Ahead of the 7th National Election June 5, 2026
  • የዘለንስኪ ጥሪ፦ “ጦርነቱን ለማቆም ከፑቲን ጋር ፊት ለፊት ለመወያየት ዝግጁ ነኝ” June 5, 2026
  • የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምርጫውን አደነቀ June 5, 2026
  • The Inverted Frontlines: How Secret Alliances and the Western Tigray Fault Line Threaten to Reignite Ethiopia June 4, 2026
  • Analysis: Ja-War, Aljazeera, Bloodshed and Terror in Ethiopia June 4, 2026
  • ጃዋር ለአርሲው ግድያ ቀዳሚ ተሟጋች ሆነ፤ “እንቀነጥሳችኋለን” ያለበትን ሜንጫ የት ጣለው? June 3, 2026
  • International Partner Welcomes Ethiopia’s 7th General Election, Calls for Inclusive Voting in Remaining Constituencies June 3, 2026
  • ዓለም አቀፍ አጋሮች የኢትዮጵያን 7ኛ አጠቃላይ ምርጫ በበጎ ተቀበሉ፤ June 3, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedbusinesshotarchivetips
    © Copyright 2026, All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2
    • Home Demo news