የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ አንድ ሺህ አንድ መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር ባለፈዉ ዓመት ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ያወጣውን ማስታወቂያ ተከትሎ ተመዝጋቢ ስራ ፈላጊ ሃኪሞች ባለማግኘቱ በጀቱን ማዛወሩን አስታወቀ። ሃኪሞች ከተመረቁ በሁዋላ ስራ ማጣታቸው በተደጋጋሚ የሚገለጸውን ሮሮ እንደነበር ይታወሳል።
“ቢሮው ማስታወቂያ ቢያወጣም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ በጀቱን ወደ ሌላ ዘረፍ ማዛወሩን ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታዉቋል” ሲል ገጹ እንዳስታወቀው ክልሉ የሃኪሞች እጥረት እንዳለበት ሃላፊው አስታውቀዋል።
የቢሮዉ ምክትል ሃላፊ ዶ/ር ጉሻ በለኮ በሰኔ 2015 ላይ 1ሺህ 1መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር ማስታወቂያ የወጣ ቢሆንም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ ቢሮዉ በጀቱን ለሌላ ጉዳይ ማዋሉን ቢያስታውቁም አሁንም ከተገኘ ሃኪም መቅጠር እንደሚፈልጉ ገልጸዋል። ይሁን እንጂ በምን ምክንያት ገበያው ላይ ሃኪም ማግኘት እንዳልተቻለ አላብራሩም። “ለሁለት ወራት ያክል ማስታወቂያዉን ክፍት ባደርግም ገበያ ላይ ተቀጣሪዎችን አላገኘሁም” ከማለት ውጭ ዝርዝር አላቀረቡም።
በክልሉ በተያዘው አሰራር በየአንዳንዱ ጤና ተቋም ሀኪሞች መኖር አለባቸው። በዚሁ መሰረት በገጠር ጤና ተቋማት ሃኪሞችን መድቦ ለማሰራት ማስታወቂያ ቢወጣም ሀኪሞችን ማግኘት አልተቻለም። በዚህም ሳቢያ በምትኩ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን፣ አዋላጆችን እና ነርሶችን ለመቅጠር መገደዳቸውን ሃላፊው ገልጸዋል፡፡
“ከዚህ በፊት ለመላዉ ኦሮሚያ አገልግሎት የሚሰጡ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር 72ሺህ ነበር” ያሉት ሃላፊዉ አሁን ላይ ቁጥሩ ወደ 85ሺህ ከፍ ማለቱን ግልጸዋል፡፡
“በተቻለን አቅም ማስታወቂያ አዉጥተን ገበያ ላይ የነበሩትን ለመዉሰድ ሞክረናል። ነገር ግን አሁንም የሀኪሞች ዕጥረት አለብን” ያሉት ሃላፊው፣ “ማስታወቂያዉን አይተዉ የመጡትን እንቀጥራለን ፤ካልመጡ ግን ገበያዉ ላይ የሰዉ ሃይል እንደሌለ ነዉ የሚቆጠረዉ” ብለዋል። ይህ ንግግራቸው “ተመርቀው ስራ አላገኙም፣ አይ ይህቺ አገር” በሚል ሲወቅሱና ሲያማርሩ የነበሩ አካላትን መረጃ ጥያቄ ውስጥ የሚጥል ሆኗል።
ሃላፊዉ በተጨማሪም ባለፈዉ ዓመት ሃኪሞችን ለመቅጠር ባወጣነዉ ማስታወቂያ ሀኪሞችን ማግኘት ስላልቻልን ወደ 7 መቶ አከባቢ የሚሆኑ የተለያዩ ባለሙያዎችን ቀጥረናል ሲሉም ነግረዉናል፡፡
ከኦርሚያ ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ አካባቢ አስተዳእሮች እንደሚሰማው ሃኪሞች ገጠር ገብተው ማገልገል አይፈልጉም። ምንም የሰላም ችግር በሌለባቸው አካባቢዎች እንኳን ቢሆን ለተወሰነ ጊዜ ገጠር ገብተው ያስተማራቸውን ህዝብ የማግለገል ተነሳሽነት የላቸውም። እርግጥ አስፈጊ የመኖሪያ ሁኔታዎች መሟላት እንዳለባቸው ቢታመንም “ገጠር ግብቶ የመስራት ፍላጎት ማጣት በአገር ደረጃ መነጋገሪይ፣ በማህበራቸው ዘንዳም አጀንዳ ሊሆን ይገባል” የሚሉ አሉ።
- ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed GroupsVOA NEWS – The Ogaden National Liberation Front (ONLF) categorically rejects claims of affiliation with armed groups and reaffirms its unwavering… Read more: ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed Groups
- Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETVIn an incisive broadcast on EBC English analyzing the architectural shifts of Ethiopia’s 7th General Election, renowned scholar Professor Alemayehu G.… Read more: Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETV
- Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science”VOE June 06, 2026 – Although genetic engineering is a relatively new field of science—spanning no more than 40 years—it is… Read more: Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science”
- ዶ/ር ጆቴ ታፈሰ- መድኃኒት አልባ ሕመሞችን በሳይንስ መፈወስሰዎችን – ከሞት አፋፍ መመለስቪኦኢ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም – የዘረ መል ምህንድስና (Genetic Engineering) ዕድሜው ከ40 ዓመታት የማይበልጥ አዲስ የሳይንስ ዘርፍ ቢሆንም፣ በአሁኑ… Read more: ዶ/ር ጆቴ ታፈሰ- መድኃኒት አልባ ሕመሞችን በሳይንስ መፈወስሰዎችን – ከሞት አፋፍ መመለስ
- ኬሞቴራፒን ማስቀረት የተቻለበት አዲስ ተስፋ፡ የ64 ዓመቷ ካረን የ«ዳግም መወለድ»ቪኦኢ ሰኔ 30 ቀን 2018 – ከካርዲፍ የመጣችው የ64 ዓመቷ አዛውንት ካረን ቦንሃም፣ የጡት ካንሰር እንዳለባት በወቀችበት ወቅት እንደማንኛውም ታካሚ ከፍተኛ… Read more: ኬሞቴራፒን ማስቀረት የተቻለበት አዲስ ተስፋ፡ የ64 ዓመቷ ካረን የ«ዳግም መወለድ»







