Skip to content
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
  • News
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    Western Pressure on Ethiopia Intended to See Weak Gov’t, Nation – Scholars

    July 10, 20210

    Journalist demands UNWFP to tell truth about missing trucks

    October 3, 20210

    ብርሃኑ ባይህ እና አዲስ ተድላ ምህረት ሊደረግላቸው ይችላል ተባለ

    December 19, 20200

    አብንና ባልደራስ ከተሸነፉ ” ውጤቱን አንቀበልም” ሊሉ የሚችሉ ፓርቲዎች እንደሚሆኑ ዲፕሎማቶች ገለጹ

    May 23, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1866
  • Design
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ሚስጥራዊ የቻይና ፖሊስ ጣቢያዎች በአሜሪካ ተገኙ

    December 19, 20240

    ሦስተኛው ዕድል እንዳይባክን … !

    May 21, 20220

    “Why I decided to extend my time at the club”

    May 24, 20230

    የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ዋና የጦሩ መሪ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለመንግስት እጁን ሰጠ

    February 24, 20220

    “Ethiopia’s success reflects a new alternative for Africa’s development”

    January 29, 20240
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • Video
    video

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለፓርላማ የሰጡት ማብራሪያ

    July 4, 2024
    video

    የህብታቸውን ምንጭ የሚያውቁ አይሰጉም! ማብራሪያ

    June 22, 2024
    video

    የሀገር አቀፍ የምክክር ሂደት ይፋዊ የማስጀመሪያ ሥነ ስርዓት

    June 4, 2024
    video

    የምክክር ሂደት ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር

    June 4, 2024
    Prev Next Showing 1 Of 5
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • News
  • Design
  • Video
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  ትህነግ እየጎመዘዘው እንዲውጠው የቀረበለት የአብይ አሕመድ የመጀመሪያ ስጦታ “ሰራዊትህን በትን”
NewsNews2

ትህነግ እየጎመዘዘው እንዲውጠው የቀረበለት የአብይ አሕመድ የመጀመሪያ ስጦታ “ሰራዊትህን በትን”

Ethioreview newsEthioreview news—January 15, 20220
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አሁን ላይ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ፣ እንዲሁም አገልግሎት አልባ መሆን የትግራይ ክልል ልዩ አጀንዳ ሆኖ በስፋት እየተሰማ ነው። የጦርነት ዝግጅት ስለመኖሩ ቢነገርም በመንግስት ወገን “ተራ ግጭት” በሚልና በቂ የአጻፋ ዝግጅት እንዳለም ይነገራል። በትህይነግና በትህነግ ወዳጆች በኩል ግን ማህበራዊ ቀውስ እጅግ ገኖና ሰፊ መልክ ይዞ እየተገለጸ ይገኛል።

“አፈገፈኩ” ቢልም በሽንፈት ከጥቃት የተረፈና የተበታተነ ሃይሉን ይዞ ወደ ትግራይ ተመልሷል የሚባልለት የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር አመራሮች ተተኳሽ በመጨረሳቸውና ካሁን በሁዋላ የመዋጋት አቅማቸው ስለተዳከመ አሜሪካ በይፋ አመራሮቹ እጅ እንዲሰጡ ጥሪ በማቅረብ ጦርነቱ እንዲቆም በይፋ ለኢትዮጵያ ሰላም ያላትን ተባባሪነት ልታሳይ እንደሚገባ የተገለጸው በማስረጃ ነው። ይህንኑ ተከትሎ ” የትህነግ አዋላጅ” የሚባሉት ኽርማን ኮሆን ” ምህረት ይደረግላችሁና አገር ለቃችሁ ውጡ” የሚል የመጨረሻ ምክራቸውን ሰንዝረዋል። ብርቅርብ የሚያውቋቸው “የማይጨበጡ” ሲሉ የሚገልጿቸው አምባሳደር ዴቪድ ሼን አሜሪካ ምንም አይነት የአቋም ለውጥ እንዳላደረገች ገልጸው ቢናገሩም ከትህነግ ሰዎች የእርቅና የድርድር ጥያቄ በተደጋጋሚ እየተሰማ ነው።

በአትላንቲክ ምክር ቤቱ የአፍሪካ ማዕከል ተመራማሪ የሆኑት ብሮንዋይን ብሩተንና የባልሲሊ ዓለማቀፋዊ ጉዳዮች ትምህርት ቤት ሊቀመንበርና የዓለም አቀፍ ደኅንነት ፕሮፌሰር አን ፊትዝ ጀራልድ ፖሊሲ አውጪዎችና ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ዘንድ ተነባቢነት እንዳለው በሚነገርለት የፎሬን ፖሊሲ መፅሄት ላይ ባወጡት ፅሑፍ ነው ለጆ ባይደን የትህነግ አመራሮች እጅ እንዲሰጡ ጥያቄና ምክረ ሃሳብ ሲያቀርቡ በአመክንዮ አስደግፈው ነበር። ከልምድ እንደሚታወቀው ተቋሙ ዝም ብሎ አይጽፍምና እነሱ ይህን ሃሳብ ባቅረቡ ቀናት ውስጥ፣ ጆ ባይደን ለተቅላይ ሚኒስትር አብይ ስልክ መደወላቸው የተነጋገሩት ቃል በቃል ባይታወቅም አንድ ነገር እንዳለ አመላካች ሆኗል።

ከቀድሞ የትህነግ መሪ አቶ ስብሃት ነጋ ጋር ስድስት አቅማቸው የደከሙ የተባሉ መፈታታቸውን ተከትሎ የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንት መቀለ ሄዶ መመለስ፣ የጆ ባይደን ተደጋጋሚ የስልክ ውይይት እንደሚደረግ መጠቆምና አሜሪካ ሰላም እንዲሰፍን አብዝታ እንደምትሰራ በይፋ ማስታወቋ በቅርቡ ” በግድ የሚዋጡ” አለያም ” የሚያስፈነጥዙ ዜናዎች” እንደሚሰሙ እሙን ነው። በርካቶች እንደሚሉት ሕዝብ እየተሰቃየ የፖለቲካ ቁማር በሁሉም ወገን ሊቆም ይገባል። ተፈለገም አልተፈለገም በድፍረት እርምጃ ተወስዶ ሰላም እንዲወርድ መሰራት አለበት።

More stories

ኤርትራ መንግሥትና ተከፋይ አልቃሽና አስለቃሾቹ ፤ አዲስ አበባ ተቃዋሚዎች በገሃድ መከሩ

January 29, 2025

ከትህነግ የዲያስፖራ ክንፍ – በውስጥ የተሰራጨ መልዕክት ” እንረጋጋ”

December 15, 2021

ከሩብ ቢሊዮን ብር በላይ የታቀፈቸው ” የትህነግ መሪ” ሰንሰለታማ የዝርፊያ ድራማ

October 29, 2021

በመቶ ሺህ የትግራይ ተወላጆችን የጨፈጨፉት ኢሳያስ ” አትራቡም የምንበላውን ቂጣ እናካፍላችኋለን” አሉ፤ ኢሳያስና መጨረሻቸው

May 8, 2025

የትግራይ ሕዝብም ሆነ ሌላው ሕዝብ ከዚህ በላይ ችግርና የፖለቲካ ሴራ መሸከም ስለማይችል በሁሉም ረገድ ለሰላም አስፈላጊው ሁሉ መደረግ እንደሚኖርበት የሚያምኑ እንደሚሉት ኬንያ ላይ እንዳንድ የሰላም ሂደቶች ተጀምረዋል። አካሄዳቸው እጅግ ጥንቃቄ የተመላበት በመሆኑ ይፋ ባይደረግም፣ ትህነግ ሰራዊቱን ካላፈረሰ መንግስት አንድ ስንዝር እንደማይነቃነቅ በሁሉም አደራዳሪ ወገኖች ዘንዳ አሜሪካንን ጨምሮ ታምኖበታል።

በአንድ አገር ውስጥ ሁለት የመከላከያ ሃይል ሊኖር እንደማይገባ፣ ትግራይ ልክ እንደሌላው ክልል በመከላከያ ውስጥ በልኳ ትወከላለች እንጂ ታንክና መድፍ የታጠቀ ሃይል ይዞ ወደ ድርድር ለመምጣት እንደማይቻል መንግስት የያዘውን ቁርጠኛ አቋም ኦባሳንጆ እያግባቡበት ያለና አሜሪካ የምትደግፈው እንደሆነ ስለ ጉዳዩ የሚያውቁ ገልጸውልናል። መንግስት “ድርድር” ያለው እንዴትና ከማን ጋር፣ በምን አግባብ እንደሆነ ግልጽ ባይቀመጥም፣ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ቅድሚያ ያቀረቡት ቅድመ ሁኔታ “ትህነግ ሰራዊቱን ትጥቅ ያስፈታ፣ ይበትን” የሚል እንደሆነ ታውቋል። ይህ ጥያቄ ትህነግ ስጋት እንዳይሆን የሚያደርግና ሰሎአም የሚያሰፍን እንደሆነ አሜሪካም አምናለች። የሁሉም ጉዳይ ቁልፍ ያለው እዚህ ነጥብ ላይ ስለመሆኑ ስምምነት መኖሩን ዜናውን የሰጡን ገልጸዋል።

This image has an empty alt attribute; its file name is Ann-and-Bruton-1024x576.jpg

ለመረጃ ይረዳ ዘንድ ይህን አካሄድ አስቀድመው የተረዱት፤ በአትላንቲክ ምክር ቤቱ የአፍሪካ ማዕከል ተመራማሪ የሆኑት ብሮንዋይን ብሩተንና የባልሲሊ ዓለማቀፋዊ ጉዳዮች ትምህርት ቤት ሊቀመንበርና የዓለም አቀፍ ደኅንነት ፕሮፌሰር አን ፊትዝ ጀራል አስቀድመው የጻፉትንና እኛ ያተምነውን ከታች አቅርበን ነበር።

ምንም እንኳን አሜሪካ ለአሸባሪ ቡድኑ ህወሃት በማድላት ሥህተት ሥትፈጽም ብትቆይም አሁንም ለሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ማብቃት አዎንታዊ ሚና ለመጫወት ያላት ዕድል  እንዳልተሟጠጠ የሚያትተው ጽሁፍ የተሰራጨው የትህነግ ወራሪ ሰራዊት መሪ ጻድቃንና የኖርዌይ ተወላጅ የሆኑት ፕሮፌሰር ሺትል ትሮድቮል በተከታታይ የሰላም ጥሪ በያዘና “ከቃል ያለፈ ድጋፍ አልተደረገም” በሚል የትጥቅ ድጋፍ በጠየቁበት ተመሳሳይ ወቅት መሆኑ ጽሁፉን ሰፊ መነጋገሪያ አድርጎታል። ምሁራኑ በጽሑፋቸው ከአራት ዓመት በፊት ለ27 ዓመታት ሲገዛ በነበረው አንባገነኑ የህወሓት ቡድን ላይ ህዝባዊ አመጽ እንደተቀሰቀሰና አገዛዙ እንደተገረሰሰ አስታውሰዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወደ ማዕከላዊ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ምንም እንኳን በህወሓት ታፍነው የቆዩ የብሄር ተኮር ጥያቄዎች እዛም እዚህም እየፈነዱ ሀገሪቷ ባትረጋጋም በርካታ ማሻሻያዎች አድርገው የዜጎችን ጥያቄዎች በልካቸው ለመመለስ እንደሰሩ ትዝብታቸውን አኑረዋል። “ነገር ግን” ይላሉ ጸሐፊዎቹ ምንም እንኳን አሸባሪ ቡድኑ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን መንግስት “አልቀበልም” ብሎ በማመጽ ወደ ትግራይ ሄዶ ቢመሽግም  ቡድኑ ቀደም ብሎ በዘረጋው የእንደራሴዎቹ ሠንሠለት የሀገሪቷን ኢኮኖሚ እና የመከላከያ ኃይል መልሶ ለመቆጣጠር ሰርቷል ብለዋል። የውክልና ሥራውን ለማስፈጸምም ከሀገሪቷ የዘረፈውን በቢሊየን ዶላሮች የሚቆጠር ሐብት ጥቅም ላይ እንዳዋለ አንስተዋል፡፡

በወቅቱ አብዛኞቹ ምዕራባውያን በለውጡ ሲደሰቱ አንዳንዶቹ ግን ከህወሓት ጋር ወታደራዊ ግጭት ሊፈጠር እንደሚችል ሲናገሩ እንደነበርም ጽሁፉ ያወሳል፡፡ ጸሐፊዎቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከኤርትራ ጋር ሠላም መፍጠሩ ለኖቤል የሠላም ሽልማት እንዳበቃቸው፣ በሀገራቱ መካከል ለሁለት አሥርት ዓመታት አኮራርፏቸው የዘለቀው የድንበር ጉዳይም በዕርቁ መፈታቱ ህወሓትን እንዳስኮረፈውና ጥግ እንዳስያዘው፣ ህወሓት በኤርትራ ድንበር አቅራቢያ ያሰፈራቸውን ኃይሎች ትጥቅ እንዲያስፈታ መንግስት ቢጠይቅም አሻፈረኝ እንዳለ፣ ይህም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ራስ ምታት ሆኖ መቆየቱን ዘርዝረዋል፡፡

ጽሑፉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሠላምን ለማስፈንና ዕርቅ ለመፍጠር በርካታ የዕርቀ-ሠላም ልዑካን ወደ ትግራይ ቢልኩም በአሸባሪው የህወሓት ቡድን እብሪት እንዳልተሳካ አመላክቷል። አክሎም ዐቢይ አህመድ በርካታ የህወሓትን ባለሥልጣናት ማንሳቱ፣ በተለይም የወታደራዊውን ማዕከላዊ ዕዝ በፈለጋቸው አመራሮች መተካቱና በትግራይ ተወላጆች ቁጥጥር ሥር ብቻ የነበረው የዕዝ ሠንሠለት በበርካታ ብሄሮች ስብጥር እንዲዋቀር መደረጉ እንዳስደነገጣቸው፣ እንዳስኮረፋቸውና ወደ ጦርነት ለመግባት መስማማት ላይ እንዳደረሳቸው ገልጸዋል። የሰሜን ዕዝ ላይ የተከፈተው ጦርነትም የዚሁ አካል እንደሆነ አመልክተዋል።

የትግራይ ባለሥልጣናት በሰሜን የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዕዝ ላይ የፈጸሙት “መብረቃዊ ጥቃት” ጦርነትን ቀስቅሷል ሲሉ ያስታወቁትና በኢትዮጵያ ጉዳይ በቂ መረጃ ያላቸው ሁለቱ ጸሃፊዎች፣ አሸባሪው የህወሓት ቡድን ከዚህ ጥቃት በኋላ የአማራን ዘር ለማጥፋት በሚመስል መልኩ በማይካድራ በበርካታ መቶዎች የሚቆጠሩ አማራዎችን መጨፍጨፉን አግለጠዋል።

የምዕራባውያኑ መገናኛ ብዙኃንም ጭፍጨፋውን በማነሳሳቱ ረገድ መንግስት ተጠያቂ መሆን እንዳለበት እንዲሁም በትግራይ ላይ የዘር ማጥፋት እንደፈጸመ አድርገው አጀንዳ በመቅረጽ መሥራት መጀመራቸውን ብሮንዋይን ብሩተን እና አን ፊትዝ-ጀራልድ በጋራ ባወጡት ጽሑፍ አሳይተዋል። መገናኛ ብዙኃኑ ከህወሓት ባልተናነሰ ለአሸባሪው ሸኔም እውቅና በመስጠት ከተገፋው ህወሓት ጋር በማበር የኦሮሞን ህዝብ ከጭቆና ነጻ ለማውጣት በጋር እየሠሩ መሆናቸውን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማሳመን ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቅሰዋል። ከመገናኛ ብዙኃኑ በተጨማሪ ዓለምአቀፍ የዕርዳታ ድርጅቶችም ህወሓትን ሲደግፉ መቆየታቸው ይፋ አድረገዋል።

አሁን አሁን አሸባሪው የህወሓት ቡድን እየተዳከመ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ መገናኛ ብዙኃኑ ጉዳዩን እንደ ቀድሞው ከማራገብ ጋብ ብሏል ሲሉ ሐፊዎቹ ምልከታቸውን በታዋቂው መጽሄት ላይ አስፍረዋል።

ፀሃፊዎቹ የፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር ያለምንም ምክንያት የአሸባሪ ቡድኑን ህወሃት ወንጀል ለመሸፈን በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ብቻ ያነጣጠረ ቅጣት እየጣለ መቆየቱን አንስተዋል።

ምንም እንኳ ጦርነቱን የቀሰቀሰው፣ ከሰሜን እዝ የጦር መሳሪያን ዘርፎ እና ቁጥሩ አያሌ የሆነ ሚሊሻ ያሰለፈው ህወሃት ሆኖ ሳለ የምእራቡ ዓለም መገናኛ ብዙሃን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግስትን የጦርነት ቀስቃሽና ፈላጊ አድርገው መሳላቸውን ነው አጉልተዋል። በዚህ መልኩ ዩናይትድ ስቴትስ ለህወሃት በማድላት ለአሸባሪ ቡድኑ የፖለቲካ ድጋፍ መስጠቷን በመጠቆም ስህተት መፈፀሟን አመልክተዋል።  የባይደን አስተዳደር ይህንን የተሳሳተ አካሄዱን በማረም የሰሜን ኢትዮጵያን ግጭት በማቆሙ አወንታዊ ሚና ለመጫወት አሁንም እድል እንዳለው መክረዋል።

ህወሃት ከአማራ እና አፋር ክልሎች ተሸንፎ መውጣቱን የሚያነሱት ፀሃፊዎቹ፥ ይህ ቡድን በተተኳሽ እጦት እና በሎጀስቲክ ድርቅ ምክንያት ምንም ወታደራዊ ስኬት የማየት እድል የለውም ባይ ናቸው።

እናም ዩናይትድ ስቴትስ ቁልፍ የህወሃት አመራሮች እጃቸውን እንዲሰጡ በይፋ በመጠየቅ፥ ለዚህ የሽብር ቡድን ምንም ድጋፍ እንደሌላት ለኢትዮጵያ ህዝብ ልታሳይ እንደሚገባ አመልክተዋል።

እነዚህ ቁልፍ የህወሃት አመራሮች ሰላምን በመምረጥ እጅ ለመስጠት ፈቃደኛ ካልሆኑም በውጭ ዓለም የተከማቸ ሀብት እና ቤተሰብ ባላቸው በእነዚህ የህወሃት መሪዎች ላይ ማእቀብ ልትጥል እንደሚገባ ገልፀዋል።

አሜሪካ አጀንዳዎቿን የሚያስፈጽሙ መገናኛ ብዙኃን፣ የእርዳታ ድርጅቶች በሰብዓዊነት ስም የሚንቀሳቀሱ ካውንስሎች እና ኤጀንሲዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦቿን ጋብ እንዲሉ በማድረግ እና አሸባሪው ቡድን ለፈፀማቸው ጥሰቶች ሁሉ በወንጀል ተጠያቂ የሚሆንበትን ምህዳር በማመቻቸት በኢትዮጵያ ላይ የፈጸመችውን አድልዖ እና በደል በመጠኑም ቢሆን መካስ እና ግንኙነቷን ወደ ቀደመው ሁኔታ መመለስ እንደምትችል ምሁራኑ ባሰፈሩት ጽሑፍ መክረዋል።

  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ እስከታተመ ድረስ ቴዲም… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ ግለሰቦች የኋይት… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም አውርደው ብዙም… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድንገተኛ አደጋ ጊዜ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
    ቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች ስህተት” መሆኑን ጽህፈት… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

Ethioreview news

A journalist

ኦብነግና ሙስጣፌ ዑመር ከስምምነት ደረሱ፤ ስምምነቱ በኬንያ እየተሰባሰቡ ላሉት አስደንጋጭ ሆኗል
ውሳኔው ወደ መጨረሻው እየቀረበ ነው – አሜሪካ አደራዳሪ ባለስልታኖቿ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 20260
Load more
Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 20260
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 20260
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 20260
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedbusinesshotarchivetips
    © Copyright 2026, All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2
    • Home Demo news