እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ በኢትዮጵያ ምድር እየኖሩ የኤርዶኻን መልእክተኛ ለመሆን የሚንፈራፈሩ ወኪሎች፣ እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ ይሻላል። የዓለም ፖለቲካ ዳር ሆኖ እንደማጨብጨብ ቀላል እንዳይመስላቸው።
እንደው ነገሩን ላለማድበስበስ፣ የAbraham Accords ሃሳብ አመንጭው ጠሚ ዓቢይ እንደሆኑ ለማወቅ ትልቅ ተመራማሪ መሆን አይጠይቅም። ታስታውሱ ከሆነ ጠሚ ዓቢይ የኖቤል ሽልማቱን በ2019 ከተቀበሉ በኋላ፣ በሰይፉ ፋንታሁን ሾው ላይ ቀርበው ስለ ኔታኒያሁ እና ስለ ኤምሬትሱ መሪ ሼይኽ መሀመድ ቢን ዛይድ ያወሩት ጉዳይ ነበር። ቃላቸውም እንዲህ ነበር፦
“…በቅርቡ የገጠመኝ አንድ ኢንተረስቲንግ ነገር አለ። እስራኤል አገር ሄጄ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ሳገኛቸው ስለ ዩናይትድ አረብ ኤሚሬቱ አሚር አናገርኳቸው። እና ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ ይባላሉ። ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ በጣም ዋይዝና አዋቂ ሰው ናቸው። ብትገናኙ፣ ብትነጋገሩ እኔ ላመቻች፣ ኢትዮጵያ ሆስት ማድረግ እንችላለን ብዬ በጣም ብዙ አወራሁ…..።”
እንግዲህ አስተውሉ! ዓለም በኮረና በምትታመስበት እና በእስራኤልና በኤምሬትስ መካከል የዲፕሎማሲ ግድግዳ ተገትሮ በነበረበት ወቅት፣ ጠሚ ዓቢይ ግን የኖቤል ሽልማታቸውን እንደ ፓስፖርት በመጠቀም በመካከለኛው ምስራቅ ኃያላን መካከል የአብረሃም ስምምነት ድልድይን እየሰሩ ነበር። “እኔ ላመቻች” የሚለው ቃል በራሱ፣ ስምምነቱ ዋሽንግተን ሳይሆን አዲስ አበባ ውስጥ እንደተጠነሰሰ አያሳይም ትላላችሁ?
በ2020 የተፈረመው የአብርሃም ስምምነት በዋነኝነት በዩናይትድ ስቴትስ አደራዳሪነት የተከናወነ “የመድረክ ትርኢት” ቢመስልም፣ ከበስተጀርባው ግን የኢትዮጵያ ዝምተኛ ግን ዋና ሚና እንደነበራት ግልጽ ነው (የሰይፉ ቃለ መጠይቅ በእንግሊዘኛ ቢሆን ኖሮ እንዲሁም የዓለማችን ጉምቱ የፖለቲካ ተንታኞች በወቅቱ ቢሰሙት ኖሮ ይህን ነበር የሚሉት)።
ኢትዮጵያ ቀደም ሲል በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ብቻ ታጥራ እንድትቀር ይፈልጉ ለነበሩት ወገኖች፣ ጠሚው ግን ሀገሪቱን በመካከለኛው ምስራቅ ቼዝ ሰሌዳ ላይ እንደ ንግስት አስቀምጠዋታል። (ጠሚ ዓቢይን ባንወዳቸውም ከሞራል አንጻር ግን ለዚህ ተግባራቸው Credit መስጠት ተገቢ ነው ፤ ጨዋነትም ነው)።
እስራኤልና UAE ሲተባበሩ ቀይ ባህርና የኤደን ባህረ ሰላጤ ላይ የሚፈጠረው ተጽዕኖ ለኢትዮጵያ የባህር በርና የንግድ ጥቅም የሚፈስ ወተት መሆኑን ያልተረዱት፣ የመንጋ ጭብጨባ ያሰከራቸው ወገኖቻችን ናቸው። አንድ እግራቸውን ፖለቲካ፣ ሌላኛውን ደግሞ ሃይማኖት ላይ አሳርፈው አዲስ አበባ ድረስ መጥቶ ሊያስፈራራን ለሞክረው የቱርኩ መሪ አቤት ወዴት የሚሉት እነዚህ ሰዎች፣ የአብርሃም ስምምነት እውነተኛ ጠንሳሽ ማን እንደሆነ ሲረዱ የሚሉትን ለመስማት እጓጓለሁ።
ቀበሮዋ ቱርክም ብትሆን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ መንገድ ተከትላ በሶማሊያ ጉዳይ አስታራቂ ነኝ ብላ ጊዜ የሰጣትን የበላይነቷን ተጠቅማ በኛ ጉዳይ ላይ ልትፈተፍት ሞክራለች። የሆነ ሆኖ ግን ለመሆኑ እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲህ ያለውን ጥልቅ የብሔራዊ ጥቅም ስሌት የመረዳት አቅም ይኖራቸው ይሆን?
ብሩክ አበጋዝ በፌስ ቡክ ገጹ እንደጻፈው

