የጀመረው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በተገመቀውና በሚጥበቀው ደረጃ በስኬት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሶ፣ ብሔራዊ ባንክ በህገወጥ የዉጪ ምንዛሪ እንቅስቃሴዎች ላይ በሚሳተፉ የፋይናንስ ተቋማት ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠነቀቀ። ከሪፎርሙ መጀመር አንስቶ ጥናት ሲያደርግ እንደነበር አመልክቶ ” መረጃ አለኝ” ብሏል።
የፋይናንስ ኢንዱስትሪው ተቆጣጣሪ ባለስልጣን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከውጭ ምንዛሪ ገበያ ጋር በተገናኘ ህገወጥ ተግባር ላይ ለሚሳተፉ የፋይናንስ ተቋማትና የንግድ ድርጅቶች ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን አመልክቷል።
የብሔራዊ ባንክ በእያንዳንዱ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አሠራርና አያያዝ ላይ ጥብቅ ምርመራ ማደረጉን አምለክተው፣ እርምጃው በዚሁ በጥናትና ምርመራው መሰረት እንደሆነ ያመለከቱት የባንኩ ገዢ ናቸው።ማድረጋቸውን አስታዉቋል ።
የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ከፋና ብሮድካስቲንግ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለፁት በሪፎርሙ በመጀመርያ ሩብ ዓመት አውንታዊ እና አበረታች ውጤቶች ተመዝግቧል። ከዚሁ በአዲስ ተግብራዊ ከሆነው የፋይናንስ አሰራር ለውጥ ጀምሮ በርካታ አዳዲስ አሀዛዊ መረጃዎችን እና እድገቶችን መኖራቸዉን አጉልተው አመልክተዋል። ይህ እድገት ቀጣይነት ያለውና የሚጠበቀውን ለውጥ እንደሚያሳካ እምነታቸው መሆኑን በቃለ ምልልሳቸው አመ፤ልክተዋል።
ሪፎርሙ የሚጠበቀውን ለውጥ እንደሚያስመዘግብ በሙሉ ዕምነት የተናገሩት የባንኩ ገዢ፣ “ይህ ሲባል ቸግር አይገጥምም፣ ችግር የለም ማለት አይደለም” ብለዋል። ” አንፈራም” በማለት ለሚገጥሙ ችግሮች መፍትሄ እየሰጡ መራመድ ግን የግድ መሆኑን ገልጸዋል። ይህን ሲያነሱ ነው በስም ያልጠቀሷቸው የፋይናንስ ተቋማት በጥናት ችግር እንዳለባቸውና በታማኝነት እንደማይሰሩ ያስታወቁት።
የብሔራዊ ባንክ ማሻሻያ ለወንጀል ድርጊቶች የተጋለጠውን ጊዜ ያለፈበትና ውጤታማ ያልሆነውን ሥርዓት በቀላልና ጊዜውን በዋጀ አሰራር መተካቱን ያስረዱት አቶ ማሞ፣ ምንም የሚደበቅ አሰራር እንደሌለ አውስተዋል። ሁሉንም የፋይናንስ ዑደት ባንኩ ጠንቅቆ እንደሚያውቀውም ተናገረዋል።
የባንኩን በጥናት የተደገፈ የምርመራና ክትትል ሂደት ካስረጉ በሁዋላ፣ “በተወሰኑ ባንኮች ጤናማ ያልሆኑ ተግባራት እየተስተዋሉ ነው” ብለዋል።ያሉት ገዢዉ፣ ብሔራዊ ባንክ ማንኛውንም ሕገወጥ ተግባር የሚፈጽሙ ተቋማትና የባንክ ኃላፊዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ ግልጽ አድርገዋል።
የውጭ ምንዛሪ ስራዎችን፣ ፖሊሲዎችን እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ የብሔራዊ ባንክ ባለስልጣናት ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ በሁሉም ባንኮች ላይ ምርመራ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ጠቅሰዋል።
“አሁን ተጠናቆ ለውሳኔ በቀረበው የምርመራ ሪፖርት መሰረት ህጋዊ እርምጃ እንወስዳለን” ሲሉም አክለዋል።
የውጭ ምንዛሪ ግብይት ላይ ባንኮች የሚጫወቱትን ወሳኝ ሚና መኖሩን ያስታወሱት ገዥው በቀድሞው የተበላሸ ሰአራር ለመቀጠል የሚፈልጉ የባንክ አመራሮች ላይ እርምጃ መወሰዱ እንደማይቀር ፍንጭ ሰጥተዋል።


