Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ታላቁ ህዳሴ ግድብ በመገባደጃ ምዕራፍ ላይ

    April 1, 2023

    የአሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችል ስራ መጀመሩን ይፋ አደረገ

    August 22, 2024

    ዶናልድ ትራምፕ በቁጥጥር ሥር ውለው በቀረበባቸው ሰላሳ አራት ክሶች ጥፋተኛ አይደለሁም አሉ

    April 6, 2023

    የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰነድ የሌላቸው የኤርትራዊ ስደተኞች መታሰራቸውን ኮነን፤ “ያለ ህጋዊ ማስረጃ የትኛው አገር መኖር ይቻላል?”

    June 4, 2023

    ቻይናዊው የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ከ9 ግብረ አበሮቻቸው ጋር የውጭ አገር ብሮች በማተምና በጥቁር ገበያ ወንጀል ታስረው ፍ/ቤት ቀረቡ

    September 5, 2023
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  EDITORIA  በኦሮሚያ ለሚገደሉ ዜጎች የፖለቲካ ቁማርና የሴራ ትንተና ፋይዳ የለውም!!
EDITORIA

በኦሮሚያ ለሚገደሉ ዜጎች የፖለቲካ ቁማርና የሴራ ትንተና ፋይዳ የለውም!!

Ethioreview newsEthioreview news—October 14, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ” ሰበር ዜና” ብር ሆኗል። ሃፍረት፣ ሃዘን፣ መራራት ቀርቶ ” ምስጢሩ ይፋ ሆነ፣ መጋረጃው ተገለጠ፣ ሰበር ዜና እንደውረደና ጥብቅ መረጃ… ” እየተባለ ሳንቲም መልቀም ቅድሚያ የተሰጠው ተግባር ሆኗል። የፕሪስ ነጻነት ባፍጢሙ ቢደፋስ ብለን እስክንመኝ ፕሬሱ በአብዛኛው ሕዝብና አገርን ሳይሆን ኪሱን መሰረት አድርጎ እየሰራ ነው። እንደ አገር ያሳፍራል። መውጪያው መንገዱም ግራ ነው። ይህ ሲባል ጨዋና ተቆርቋሪዎች የሉም ማለት አይደለም።

ራሳቸውን ” አክቲቪስት” የሚሉ ቀንና ሌት ሲሳደቡ፣ መርዝ ሲረጩ፣ ሲያተራምሱ፣ ልዩነትና ክፋት ሲግቱ፣ ቃላትና ሃረግ እየሰነጠቁ በድርሰት ሲያነበንቡ የሚውሉበትና የሚያድሩበት መከረኛ የዩቲዩብ መንደር የእለት ጉርሳቸው፣ ከዛም በላይ ለተሸጡበት ዓላማቸው ቅድሚያ የሚሰጡበት እንጂ አገርና ሕዝብን ከችግር የሚታደጉበት አውድ አይደለም። መልካም አሳቢዎችን አይመለከትም።

ሕጻን ሲገደል ” ሰበር መረጃ”፣ እናት ስትሞት ” ትኩስ ዜና፣ ሕዝብ ሲታረድ ” ልዩ ዜና” … ወዘተ በሚልና ይህንኑ ጉዳይ ቀንድና ጭራ እየተከሉለት ሲተነትኑ ውለው የሚያድሩ፣ በመካከሉ ” እናመሰግናለን ለሱፐር ቻት ድጋፍዎ” በሚል ልመናቸውን የሚያካሂዱ፣ በችግሩ ላይ ነዳጅ እየጨመሩ አገሪቱን እያሟሟት ነው።

የተሰጣቸውን ተልዕኮ ለመወጣት የእርስ በርስ ጭፍጭፍን የሚጋብዙን የኢትዮጵያን የእንግዴ ልጆች የሚደጉሙ፣ የሚደግፉ፣ የሚያበረታቱ፣ የሚያሞካሹ ክፍሎች ለየትኛዋ አገርና ሕዝብ እየሰሩ እንደሆነ አለመረዳታቸው የኢትዮጵያን ሃዘን ድርብ ያደርገዋል። እጅግ የሚያሳዝንና ወራዳነትም ነው። ቀን ቤተክርስቲያን ማታ አክቲቪዝምን እያቀላቀሉ እሳት የሚተፉ ደደቦችን ቁጭ ብለው የሚያዳምጡ ዜጎች ከአጠቃላዩ የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ መቶኛ ባይሞሉም፣ ከማን ምን መማርና ማወቅ እንደሚፈልጉ ማሰብ ያደክማል።

More stories

በአማራ ስም ሆነ በ”ጎጃምነት”ኦሮሚያን መውረር ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም

January 8, 2023

ካድሬዎች በዛብን በቃን !! አገርም ጫንቃዋ ይርዳል፤

October 16, 2022

መከላከያን አለማመን የአገር ክህደት ነው! በአጥንት ካባ ህዝብ አታጋድሉ!

April 10, 2023

አደዋ መንፈስ ነው ይጋባብን!!

March 2, 2024

“እኔ በሃይልና በቁጣ ስናገር ልጆቼ እየሰሙ ተጨነቁብኝ” ብሎ ለራሱ ልጆች የድምጽ ብክለት የሚያስብ ለማኝ፣ አገር ለማፍረስና ሕዝብ እንዲበተን ምድር ቤት ተከራይቶ ማታ ማታ መርዝ እንደሚረጭ ስንቶቻቸን እናውቅ ይሆን? ኢትዮጵያን የማድማቱና የመፈረካከሱ ዘመቻ አገር አልባ እንደሚያደርገን እንዴት መረዳት አቃተን፣ እኛ መደንቆራችንና እነሱን መስማታችን ቢያሳዝንም ይህ እንዲሆን ሌት ተቀን የሚተጉ ዓላማቸው ሲሳካ ምን እንደሚያተርፉ ማሰብ ደግሞ ከሰውነት ደረጃ የሚያወርድ ይሆናል።

ኢትዮጵያ ከፍተኛ በጀት በተመደበለት የትርምስ አጀንዳና አተራማሾች አማካይነት ላለፉት ሶስት ዓመታት ነፍራለች። ከዛ በፊት ለሶስት ዓመታት ለውጥ አርግዛ ስትለበለብ ነበር። በድምሩ ስድስት ዓመት ሙሉ ኢትዮጵያ ታማለች። በስተመጨረሻ በትግራይና በአማራ ክልል፣ እንዲሁም በአፋር የከፋ ቀውስ ገጥሟታል። በጥቂት ስግብግቦች አማካይነት እየሆነ ያለው ሁሉ እንደ ዜጋ አንገት የሚያስደፋ፣ የሚያሳፍር፣ የሚያሳዝንና የሚጨንቅ ሆኖ ሳለ በዚህ ሁሉ መከራ ውስጥ የፖለቲካና የኪስ ትርፍ ላይ የተጠመዱ ዜጎችን መመለከት ህመሙ ….

ይህን ከላይ ያለውን ያነሳነው በኪራሙ ወረዳ ሀሮ ቀበሌ ባለፉት ተከታታይ ቀናት በተፈፀመ ጥቃት በርካታ ሰዎች ተገድለዋል፣ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ተፈናቅለውም ተሰደዋል የሚለውን ሪፖርት መስማታችንን ተከትሎ ነው። ጥቃቱ የሚፈጸመው ከትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ጋር ግንባር መፍጠሩን ባስታወቀው ኦነግ ሸኔ አማካይነት እንደሆነ የመሰከሩት በህይወት ያሉ የሰለባው ቤሰቦችና የዓይን እማኞች ናቸው። ይህን እውነት መከራከር ወይም አለማመን አይቻልም።

እነዚህ ሰላማዊ ያልታጠቁ ዜጎች ንብረታቸው ተዘርፎ ወደ ኪረሙ፣ ጊዳና፣ ነቀምት መሰደዳቸው ታውቋል። ይህ ቀን እየጠበቀ የሚፈጸምና ምክንያት ሊቀርብለት የማይችል ጭፍጨፋ ማስቆም አልተቻለም። በአማራ ስም የሚነግዱ “አክቲቪስት ነን” ባዮች ተቀርጾ የተላከላቸውን የመጨረሻ ማተራመሻ ቪዲዮ እየተቀባበሉ ተጨማሪ ጥፋት እየጋበዙ ነው።

ሸኔ የሚባለው ቡድን ኦሮሞን እንደማይወክል፣”ተከፋይ ቅጥረ ነፍሰ ገዳይ” መሆኑንን፣ በገንዘብ እየተዋዋለ በክፍያ ጭፍጨፋ እንደሚፈጽም፣ ዓላማና ግብ የሌለው የትህነግ አገልጋይ እንደሆነ በቅርብ የሚያውቁት እያጋለጡ ነው። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ የኦሮሚያ ፕሬዚዳንትም ሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ሆን ብለው ግድያውን እንደሚያከናውኑት በማስመሰል የሚራባው የፈጠራ ትንተና የምስኪኑን አማራ ስቃይ ያበዛው ካልሆነ በቀር የሚፈይደው አንዳችም ጉዳይ እንደሌለ መረዳት አስፈላጊ ይሆናል።

አንድ ቦታ አንድ ድርጊት ሲፈጸም በቅጽበት ቪዲዮ ተቀርጾ የሚላክላቸው አካላት፣ አንድ ፖሊስ ሰው ሲገል ራሱን ቀርጾ ለምን እንደሚልክላቸው፣ ቤት ሲያቃጥል ራሱን ቪዲዮና ፎቶ አንስቶ ምን እንዲደረግ እንደሚልክላቸው በቅጡ መረዳት ወይም መጠየቅ አግባብ ይሆናል። አለያ ዝም ብሎ የቀረበን ሁሉ መዋጥ ትርፉ ጉዳት ብቻ ነው።

በእርግጥ ይህ ግድያ መደጋገሙና በቁጥጥር ስር ሊውል አለመቻሉ በጉልህ ሊነሳ የሚገባው ጉዳይ እንደሆነ ይታመናል። የአካባቢው አስተዳደር ወይም የክልሉ መንግስት ሰፊ ቁጥር ያለው ልዩ ሃይል አሰማርቶ ወይም ነዋሪዎችን አስታጥቆ ራሳቸውን እንዲጠብቁ የማያደርግበት ምክንያት አስቸኳይ ምላሽ ያሸዋል።

የኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው “ሸኔ” ከህወሓት ጋር አንድ መሆኑን ካወጀ ለኃላ የብሄር ግጭት ለማስነሳት የተለያዩ አካባቢዎች ጥቃት እየፈፀመ ነው ሲሉ ተናግረዋል። “ሸኔ” ባለፉት ሶስት ቀናትም ኪረሙ ወረዳ ላይ ጥቃት መፈፀሙንና ንፁሃን መገደላቸውን አስታውቀዋል።

በተጨማሪ ከሌላ አካባቢ የመጣ ሳይሆን ፤ በዛው አካባቢ የሚንቀሳቀስ የ “ሸኔ” ተፃራሪ “ፅንፈኛ” ቡድን አለ ያሉ ሲሆን የሚሰራው ድርጊት ከ “ሸኔ” ጋር እንደሚመሳሰል፣ አብሮ የሚኖረውን ማህበረሰብ ለይቶ በማጥቃት የፖለቲካ አጀንዳ ለማግኘት የሚንቀሳቀስ የ “ሽፍታ” ቡድን መሆኑንን አመልክተዋል። ለኢቲቪ በሰጡት ቃል ደግሞ ይህ የ “የሸፍታ” ቡድን የአማርኛ ተናጋሪ ሃይል እንዳለው ገልፀዋል። ይህ አዲስ መረጃ አደገኛና ሊጤን የሚገባው ነው።

“ሁለቱ አካላት ናቸው በንፁሃን ላይ ጥቃት ያደረሱት” የሚሉት አቶ ኃይሉ፣ ከሰሞኑ በነበረው ጥቃት 15 ሰዎች መገደላቸውን ይፋ አድርገዋል፤ ድርጊቱ የተፈጸመው የብሄር ግጭት ለመቀስቀስ ታስቦ እንደነበር ተናግረዋል። እዚህ ላይ አማርኛ ተናጋሪዎቹ እነማን ናቸው? እዛው አካባቢ የሚኖሩ ሰፋሪዎች፣ ወይስ እዛው አካባቢ የሚኖሩ የሌላ ብሄር አባላት፣ ወይስ አማርኛ አቀላጥፈው የሚናገሩ … ልብ ያለው አክቲቪስት ይን መርምሮ ያጋልታል። ክቀጥረኛነትና ከኪስ ማደለብ የዘለለ እምነት ያለው መረጃ አስተላላፊ እነዚህን ክፍሎች መርመሮ ይደርስባቸዋል እንጂ ቁጭ ብሎ ሲሳደብና ተጨማሪ ሽብር ሲያመርት ውሎ አያመሽም።

” የሰሞኑን ጥቃት ማንነት መሰረት አድርጎ ተፈፀመ የሚለውም ሊስተካከል ይገባል ” ሲሉም የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊው አቶ ኃይሉ አዱኛ ገልጸዋል። ይህ ያልጠራ መረጃ ስጋት የሚያዳብር ሲሆን፣ እስካሁን ባለው መረጃ በተመሳሳይ አካባቢ ሰፊ ቁጥር ያላቸው የሌላ ብሄር ሰፋሪዎች ጥቃት ሲደርስባቸው አለመሰማቱ፣ ቀደም ሲል በመንደር ተደራጅተው በደንብ የታጠቁ መሆናቸው ከስጋት ነጻ እንዳደረጋቸው ያስታወቁት ክፍሎች ሌሎችም ሳይውል ሳያድር ሊታጠቁና ራሳቸውን መከላከል እንዲችሉ ሊደረግ እንደሚገባና በአገር ደረጃ አቅጣጫ ተቀምጦ በአስቸኳይ ወደ ተግባር እንዲገባ አመላክተዋል። ጉዳዩ ያለው እዚህ ላይ ነው። ግፊቱና ጫናውም ሊጠብቅ የሚገባው እዚሁ ነጥብ ላይ ነው። ሌሎች ሰፋሪዎች ተደራጅተው ከታጠቁ ለምን አማራ ተደራጅቶ ራሱን እንዲጠብቅ አይታጠቅም?

መንግስት እያንዳንዱን ቀበሌና መንደር መጠበቅ ስለማይቻለው፣ ህዝቡን አደራጅቶ የራሳቸው ዋስትና ራሳቸው እንዲሆኑ ማድረግ እንደሚገባው በተደጋጋሚ መገለጹና የኦሮሚያ ክልልም ወደዚህ አማራጭ እንደሚሄድ ከወር በፊት ማስታወቁ አይዘነጋም። ግን መቼ? ክልሉ ራሱንም አካባብውንም፣ የታች አመራሩንም ሊመረምር ይገባል።

FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ኮንስበርግ አምስት ገድሎ ሁለት ያቆሰለው ዴንማርካዊ ሃይማኖት ከአክራሪነት ጋር እየተያያዘ ነው
ብሔራዊ ባንክ የጣለውን የብድር ዕግድ በከፊል አነሳ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
EDITORIA

መንግስት – ማህበራዊ ሚዲያ አይጋልብህ!

August 24, 2024
EDITORIA

አደዋ መንፈስ ነው ይጋባብን!!

March 2, 2024
EDITORIA

የኢሳያስ መንግስት ለኤርትራንና ኢትዮጵያ ህዝብ አብሮነት ጥንቃቄ ያድርግ!!

May 2, 2023
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2