በርካታ መጠን ያላቸው የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያን በማስፋፋት ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ። ተጠርጣሪዎቹ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል።
የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ኪያ ዦንግን ጨምሮ ዘጠኝ የውጭ ሀገራት ዜጎች እና ሶስት ኢትዮጵውያን ተጠርጣሪዎች ናቸው ፍርድ ቤት የቀረቡት።
መርማሪ ፖሊስ ግለሰቦቹ በርካታ መጠን ያላቸው የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያን በማስፋፋት ወንጀል መጠርጠራቸውን ለችሎቱ አስረድቷል፡፡
በቁጥጥር ስር በዋሉበት ወቅትም የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች የሚታተሙባቸው ማተሚያ ማሽኖችና ለግብዓት የሚያገለግሉ ኬሚካሎች እንዲሁም በርካታ ዩሮ፣ የአሜሪካ ዶላርና የሌሎች ሀገራት ገንዘቦች መያዙን ፖሊስ ጠቅሷል።
ተጠርጣሪዎቹ ላይ የተጀመሩ ሰፊ የምርመራ ስራዎችን አከናውኖ እና የተናጠል ተሳትፏቸውን ለይቶ ለመቅረብም የ14 ቀን ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል። ከአራተኛ ተጠርጣሪ ውጪ ያሉ ግለሰቦች ከወንጀል ድርጊቱ ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው ገልጸዋል።
በተጨማሪም የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች የግለሰቦቹ የወንጀል ተሳትፎ ባልተገለጸበት ሁኔታ ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ሊሰጥ አይገባም ሲሉ ተከራክረዋል።
የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ኪያ ዦንግን የተባሉት ግለሰብ በበኩላቸው÷ የተገኘው የውጭ ሀገራት ገንዘብ ማተሚያ በእርሳቸው ቤትና ቢሮ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የወንጀል ድርጊቱ የሚገናኘው ከእርሳቸው ጋር ብቻ መሆኑን ገልጸው÷ ሌሎች ተጠርጣሪዎች ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው ለችሎቹ አብራርተዋል።
መርማሪ ፖሊስ በበኩሉ÷ ተሳትፏቸው አልተገለጸም ተብሎ የተነሳውን መከራከሪያ በሚመለከት በቀጣይ ተሳትፏቸውን ለይቶ በስፋት ምርመራውን አከናውኖ እንደሚቀርብ ገልጾ መልስ ሰጥቷል።
የግራ ቀኙን ክርክር የተከታተለው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ተጨማሪ የማጣሪያ ምርመራ መደረግ እንዳለበት በማመን የተጠርጣሪዎቹን የዋስትና ጥያቄ ለጊዜው ውድቅ አድርጎታል።
ፖሊስ በቀጣይ ቀጠሮ የተጠርጣሪዎችን የወንጀል ተሳትፎ ለይቶ እንዲያቀርብ ከነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የሚታሰብ የ12 ቀን የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።
በሌላ በኩል ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹ ከቤተሰብ ጋር እንዲገናኙ እና ሕክምና ማግኘት የሚፈልጉም ሕክምና እንዲያገኙ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
በታሪክ አዱኛ FBC
- Egypt and Eritrea Ink Maritime and Security Deals: What It Means for EthiopiaVOE NEWS CAIRO — Egyptian President Abdel Fattah el-Sisi and visiting Eritrean President Isaias Afwerki have agreed to launch… Read more: Egypt and Eritrea Ink Maritime and Security Deals: What It Means for Ethiopia
- ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed GroupsVOA NEWS – The Ogaden National Liberation Front (ONLF) categorically rejects claims of affiliation with armed groups and reaffirms… Read more: ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed Groups
- Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETVIn an incisive broadcast on EBC English analyzing the architectural shifts of Ethiopia’s 7th General Election, renowned scholar Professor… Read more: Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETV
- Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science”VOE June 06, 2026 – Although genetic engineering is a relatively new field of science—spanning no more than 40… Read more: Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science”
- ዶ/ር ጆቴ ታፈሰ- መድኃኒት አልባ ሕመሞችን በሳይንስ መፈወስሰዎችን – ከሞት አፋፍ መመለስቪኦኢ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም – የዘረ መል ምህንድስና (Genetic Engineering) ዕድሜው ከ40 ዓመታት የማይበልጥ አዲስ የሳይንስ ዘርፍ… Read more: ዶ/ር ጆቴ ታፈሰ- መድኃኒት አልባ ሕመሞችን በሳይንስ መፈወስሰዎችን – ከሞት አፋፍ መመለስ







