ዳኛው በኮሮና ቫይረስ ተጠቅተው በማግለያ ክፍል እንዲቆዩ በመደራገቸው ምክንያት በእነ ጌታቸው አሰፋ ክስ መዝገብ ላይ ሊሰጥ የነበረው ብይን ለሌላ ጊዜ ተሸጋገረ
በእነ ጌታቸው አሰፋ መዝገብ ላይ ዳኞች ተሟልተው ባለመገኘታቸው ምክንያት ተከሳሾች ባነሱት የዋስትና ጥያቄ ላይ ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ።
በቀድሞው የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ጌታቸው አሰፋ፣ ያሬድ ዘሪሁንና ሌሎች 24 ተከሳሾች ላይ እንደየጥፋተቸው በፈፀሙት ወንጀል እንዲከላከሉ ብይን የተሰጠ መሆኑ ይታወቃል ።
ሆኖም ተከሳሾቹ በዋስ ወጥተን ክሳችን አንከታተል ብለው ፍርድ ቤቱን ቢጠይቁም ዐቃቤ ህግ ዋስትናውን በፅሁፍ መልስ ልስጥበት በማለቱ ምክንያት ለታህሳስ 06/2014 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶ በዚሁ ተለዋጭ ቀጠሮ ዐቃቤ ህግ በዋስትና ጥያቄው ላይ የፅሁፍ መልስ መስጠቱ የሚታወስ ነው ።
አንደኛው የችሎት ዳኛ በገጠማቸው የግል ችግር ምክንያት ባለመገኛታቸው ችሎቱ ለታህሳስ 12/2014 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ቢሰጥም አንደኛው ዳኛ ከዚህ በፊት በተከሳሾች ላይ በተሰጠው ብይንና ፍርድ ላይ አብዛኞቹን ቢስማሙበትም 5ኛ ክስን በተመለከተ በ2ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች ላይ በአብላጫ ድምፅ ተበልጠው በልዩነት ያልተስማሙ መሆኑን መግለፃቸው ይታወሳል። ስለሆነም በችሎቱ ይህ ዳኛ ባልተስማማሁበት ክስ ላይ ብይን ልሰጥ አልችልም በማለታቸው ጉዳዩን መርምሮና አይቶ ብይን መስጠት እንዲቻል ለታህሳስ 19/2014 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶ እንደነበር መግለጻችን የሚታወስ ነው፡፡ ይሁንና በዚህም ቀጠሮ ከችሎቱ ዳኞች መካከል አንዱ በኮሮና ቫይረስ ተጠቅተው በማግለያ ክፍል እንዲቆዩ በመደራገቸው እና ችሎቱን በአንድ ዳኛ ብቻ ማስኬድ የማይቻል መሆኑን በመግለጽ በችሎቱ የተገኙት የችሎቱ መሐል ዳኛ መዝገቡን ለታህሳስ 27/2014 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተውበታል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር።… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች


