Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ታላቁ ህዳሴ ግድብ በመገባደጃ ምዕራፍ ላይ

    April 1, 2023

    የአሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችል ስራ መጀመሩን ይፋ አደረገ

    August 22, 2024

    ዶናልድ ትራምፕ በቁጥጥር ሥር ውለው በቀረበባቸው ሰላሳ አራት ክሶች ጥፋተኛ አይደለሁም አሉ

    April 6, 2023

    የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰነድ የሌላቸው የኤርትራዊ ስደተኞች መታሰራቸውን ኮነን፤ “ያለ ህጋዊ ማስረጃ የትኛው አገር መኖር ይቻላል?”

    June 4, 2023

    ቻይናዊው የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ከ9 ግብረ አበሮቻቸው ጋር የውጭ አገር ብሮች በማተምና በጥቁር ገበያ ወንጀል ታስረው ፍ/ቤት ቀረቡ

    September 5, 2023
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  law  ይግባኝ ሰሚው እነ መስከረም ይከሰሳሉ አለ
law

ይግባኝ ሰሚው እነ መስከረም ይከሰሳሉ አለ

Ethioreview newsEthioreview news—February 9, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ጠቅላይ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ በሽብር ወንጀል የተከሰሱ 27 ግለሰቦች ክሳቸው እንዲቋረጥ በስር ፍርድ ቤት የተሰጠውን ብይን ሻረ።

ጠቅላይ ፍ/ቤቱ ከ6 ወራት በፊት በአማራ ክልል ተከስቷል ከተባለው ሁከትና አመጽ ጋር ተያይዞ በእነ ዶ/ር ወንድወሰን የክስ መዝገብ ተካትተው በሽብር ወንጀል ተከሰው የነበሩና ችሎት ባለመቅረባቸው ምክንያት ክሳቸው እንዲቋረጥ የተደረጉ እነ ምሬ ወዳጆን ጨምሮ 27 ተከሳሾች ክሳቸው እንዲቋረጥ በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ብይን ነው የሻረው።

በስር ፍርድ ቤት የተሰጠውን ብይን የሻረው የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ነው።

የፍትሕ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ከአምስት ወራት በፊት ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ እና መስከረም አበራን ጨምሮ አጠቃላይ 51 ግለሰቦች ላይ የሽብር ወንጀል ክስ አቅርቦ ነበር።

More stories

ሿሿ – ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 25 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

May 20, 2023

አሸባሪ ቡድኑ በአማራና በአፋር የፈጸማቸውን ወንጀሎች የሚያጣራ ግብረ ኃይል ሥራውን ጀመረ

December 27, 2021

በአደገኛ ዕፅ ዝውውር ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ ግለሰቦች ከ2 ዓመት እስከ 12 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ

October 24, 2024

የሃጫሉ ገዳዮች የተባሉት ” ጥፋተኛ” ተባሉ

July 5, 2021

በዚህም ቀርቦ በነበረው ክስ ላይ ተከሳሾቹ ”መነሻችን አማራ መድረሻችን ኢትዮጵያ” በሚል የፖለቲካ እና የርዕዮት አላማ ለማራመድ በማሰብ፣ ሀገሪቱን እያስተዳደረ ያለውን መንግስት በተለያየ ወታደራዊ ስልት እና ስትራቴጅ በመውጋት፣ የአማራን ህዝብ ክብር እና ኩራት በወታደራዊ ኃይል መመለስ፣ የመንግስትን ኃይል በማያዳግም መልኩ መደምሰስ፣ የክልሉን ገዢ ፓርቲ ማስወገድ፣ የሀገሪቱን ማዕከላዊ ስልጣን መቆጣጠር፣ የአማራ ክልል የሚዋሰኑባቸው መንገዶችን መዝጋት፣ ህዝብን ማሸበር እና መንግስትን አስገድዶ ከስልጣን ማውረድ የሚሉ የሽብር ተግባር ድርጊቶችን ፈጽመዋል በማለት ዐቃቤ ሕግ በክሱ ላይ አስፍሯል።

በተለይም ዐቃቤ ሕግ በክሱ ላይ ተፈፅሟል ባለው የሽብር ድርጊት እንቅስቃሴ የማህበራዊ አገልግሎት መቋረጡንና አመጽ መነሳቱን ጠቅሶ÷ በዚህ የሽብር ተግባር ደግሞ አጠቃላይ 217 ሰዎች ህይወት ማለፉን፣ 297 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን እንዲሁም 1 ቢሊየን 298 ሚሊየን 346 ሺህ 276 ብር በላይ በሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል በማለት በክሱ ዝርዝር ላይ አስፍሯል።

በዚህ መልኩ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32/1/ሀ/ለ/፣ 35 እና 38፤ እና የሽብር ወንጀልን ለመቆጣጠር እና ለመከላከል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1176/2012 አንቀፅ 3 ንዑስ ቁጥር 2 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፍ የሚል ክስ በተከሳሾቹ ማቅረቡ ተጠቅሶ ዝርዝር ክስ አቅርቦባቸው ነበር።

በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሕገመንግስትና በሕገመንግስታዊ ስርዓቱ ላይ የሚፈጸሙ የወንጀል ጉዳዮችን የሚመለከተው ችሎት ክሱ ከቀረበ በኋላ ክስ ከተመሰረተባቸው አጠቃላይ 51 ተከሳሾች መካከል ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ እና መስከረም አበራን ጨምሮ 23 ተከሳሾች ችሎት ሲቀርቡ፤ ቀሪ 27 ተከሳሾች አልቀረቡም።

ይሁንና ችሎት የቀረቡት 23ቱ ተከሳሾች የተከሰሱበት ድንጋጌ ዋስትና የማያሰጥ መሆኑን ተከትሎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ተደርጓል።

ቀሪ 27 ተከሳሾች ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውን ተከትሎ ፖሊስ እንዲያቀርባቸው ዐቃቤ ሕግ ለችሎቱ ጥያቄ አቅርቦ ነበር።

በዚህ ጊዜ በማረሚያ ቤት የሚገኙ ተከሳሾች የተፋጠነ ፍትሕ ሊያገኙ እንደሚገባ ጠበቆቻቸው ገልጸው÷ ጉዳያቸው ተነጥሎ እንዲታይላቸው ጠይቀዋል።

ፍርድ ቤት ያልቀረቡ ምሬ ወዳጆን ጨምሮ 27 ተከሳሾችን በሚመለከት የፌደራል ፖሊስ ማረጋገጫ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ የሰጠ ሲሆን፣ ፖሊስ ግን ተከሳሾቹ ጫካ መግባታቸውን ገልጾ ማረጋገጫ ማቅረብ እንደማይችል መልስ ሰጥቶ ነበር።

ይህን ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ ያልቀረቡ ተከሳሾች በጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግና ካልቀረቡ ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ጠይቋል።

ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ ጫካ ከሆኑ የጋዜጣ ጥሪ ቢደረግም ተደራሽ ሊሆን አይችልም የሚለውን ግምት በመያዝ የጋዜጣ ጥሪ ማድረግ ሳያስፈልግ ክሱ ይቋረጥ በማለት ብይን ሰጥቶ ነበር።

ዐቃቤ ሕግ በስር ፍርድ ቤት የተሰጠውን ‘ክስ ይቋረጥ’ ብይንን በመቃወም ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ወንጀል ችሎት ይግባኝ ብሏል።

ይግባኝ ሰሚ ችሎቱም የግራ ቀኝ የመልስ መልስና ክርክሮችን መርምሯል።

በዛሬው ቀጠሮም ክሳቸው ይቋረጥ ተብሎ በስር ፍርድ ቤት የተሰጠው ብይን ሥነ ስርዓታዊ አይደለም በማለት ብይኑን ሽሮታል።

በታሪክ አዱኛ

law
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ታማኞችና ቀናዎችን መሾም ይቀጥላል …!
መቅደስ ዳባ – ከከፍተኛ ጥቅም ይልቅ አገራዊ ጥሪን “እሺ” ያሉ ሚኒስትር
Related posts
  • Related posts
  • More from author
law

ህገወጥ የውጭ ምንዛሪ ወንጀል የፈጸሙ 123 ተጠርጣሪዎች የባንክ ሒሳብ ታገደ

September 20, 2025
law

እነ ቀሲስ በላይ በሙስና ወንጀል ሊፈርድባቸው እንደማይገባ ጠቅሰው ያቀረቡት ይግባኝ ውድቅ ሆነ

July 26, 2025
law

የአዲስ አበባ የከንቲባ ፅ.ቤት ፕሮቶኮልን ጨምሮ 12 ተከሳሾች በሌብነት ተከሰው ተፈረደባቸው

July 23, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2