Skip to content
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
  • News
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    Western Pressure on Ethiopia Intended to See Weak Gov’t, Nation – Scholars

    July 10, 20210

    Journalist demands UNWFP to tell truth about missing trucks

    October 3, 20210

    ብርሃኑ ባይህ እና አዲስ ተድላ ምህረት ሊደረግላቸው ይችላል ተባለ

    December 19, 20200

    አብንና ባልደራስ ከተሸነፉ ” ውጤቱን አንቀበልም” ሊሉ የሚችሉ ፓርቲዎች እንደሚሆኑ ዲፕሎማቶች ገለጹ

    May 23, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1866
  • Design
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ሚስጥራዊ የቻይና ፖሊስ ጣቢያዎች በአሜሪካ ተገኙ

    December 19, 20240

    ሦስተኛው ዕድል እንዳይባክን … !

    May 21, 20220

    “Why I decided to extend my time at the club”

    May 24, 20230

    የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ዋና የጦሩ መሪ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለመንግስት እጁን ሰጠ

    February 24, 20220

    “Ethiopia’s success reflects a new alternative for Africa’s development”

    January 29, 20240
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • Video
    video

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለፓርላማ የሰጡት ማብራሪያ

    July 4, 2024
    video

    የህብታቸውን ምንጭ የሚያውቁ አይሰጉም! ማብራሪያ

    June 22, 2024
    video

    የሀገር አቀፍ የምክክር ሂደት ይፋዊ የማስጀመሪያ ሥነ ስርዓት

    June 4, 2024
    video

    የምክክር ሂደት ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር

    June 4, 2024
    Prev Next Showing 1 Of 5
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • News
  • Design
  • Video
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  በሞባይል ገንዘብ አገልግሎት በሚንቀሳቀስ የገንዘብ መጠን ላይ በድጋሚ ገደብ ሊጣል ነው 
News

በሞባይል ገንዘብ አገልግሎት በሚንቀሳቀስ የገንዘብ መጠን ላይ በድጋሚ ገደብ ሊጣል ነው 

Ethioreview newsEthioreview news—March 5, 20230
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሞባይል ገንዘብ አገልግሎት በቀን ውስጥ ማንቀሳቀስ የሚቻለው የገንዘብ መጠን ላይ ያነሳውን ገደብ በድጋሚ የሚጥል መመሪያ አዘጋጀ። ረቂቅ መመሪያው የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት የሚጠቀሙ ደንበኞች በአካውንታቸው ውስጥ መያዝ የሚችሉትን የገንዘብ መጠን ከ100 እስከ 233 በመቶ አሳድጓል። 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያዘጋጀው ይህ ረቂቅ የክፍያ መፈጸሚያ ሰነድ አውጪነት ፈቃድ አሰጣጥ ረቂቅ መመሪያ ከመጋቢት 2012 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ላይ ያለውን መመሪያ እና ማሻሻያዎቹን የሚተካ ነው። አሁን በስራ ላይ ያለው መመሪያ፤ በፋይናንስ ተቋማት ብቻ ተገድቦ የነበረውን የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ዘርፍ “ለፋይናንስ ቴክኖሎጂ ተቋማት” (Fintech) የከፈተ ነበር። 

ይህ መመሪያ ከወጣ በኋላ መንግስታዊው የቴሌኮም አቅራቢ ድርጅት ኢትዮ ቴሌኮም፤ በዘርፉ የመጀመሪያ የሆነውን ፈቃድ በማግኘት  የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ስራን ጀምሯል። “ቴሌ ብር” በተሰኘ ስያሜ በግንቦት 2013 ዓ.ም የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ኢትዮ ቴሌኮም፤ እስከ 2015 የመጀመሪያ አጋማሽ ድረስ ብቻ አገልግሎቱን የሚጠቀሙ 27.2 ሚሊዮን ደንበኞችን አፍርቷል።

ከግሉ ዘርፍ የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ለመስጠት ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በማግኘት ቀዳሚ የሆነው “ካቻ ዲጂታል ፋይናንሺያል ሰርቪስስ” የተሰኘው ድርጅት ነው። “ካቻ” በሚል ስያሜ ለሚጠራው አገልግሎቱ ባለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ፈቃድ ያገኘው ድርጅቱ፤ ወደ ስራ ለመግባት በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታውቋል። በብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ካገኙት ከእነዚህ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ ተቋማት በተጨማሪ የንግድ ባንኮችም የሞባይል ገንዘብ አገልግሎትን ለደንበኞቻቸው እየሰጡ ይገኛሉ።  

More stories

በመተከልና ሌሎች አካባቢዎች ተፈጥረው በነበሩ ግጭቶች የሱዳንና የግብፅ እጅ እንዳለበት ተገለጸ

March 5, 2021

የመከላከያን ጨምሮ የአሜሪካንን ሚስጢር “ለትውልድ አገሩ አቀብሏል” የተባለው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ” ብሄራዊ ጀግና” እየተባለ ነው

October 1, 2023

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ወይም ሞት እያለ ነው

March 22, 2022

“የኢትዮጵያ አምላክ እንደ ወትሮው ከእኛ ጋር ነበር ” ዐቢይ አህመድ ወደ ቢሮ መመለሳቸውን ገለጹ

December 8, 2021

እነዚህ ተቋማት የሚሰጡትን የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ለመምራት የዛሬ ሶስት ዓመት ገደማ የወጣው የመጀመሪያው መመሪያ፤     ደንበኞችን በሶስት ደረጃዎች ከፋፍሏቸው ነበር። ተጠቃሚዎች በተለያዩ ደረጃዎች ላይ የሚቀመጡት፤ አገልግሎቱን ለመጠቀም “አካውንት” ሲከፍቱ ስለራሳቸው የሞሉትን መረጃ መሰረት በማድረግ ነው።

“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያነጋገረቻቸው አንድ የብሔራዊ ባንክ ኃላፊ፤ በተለያዩ ደረጃዎች ላይ በሚቀመጡ ደንበኞች መካከል ያለው ዋነኛው ልዩነት “የመታወቂያ መኖር እና አለመኖር” መሆኑን ይገልጻሉ። መታወቂያ የሌላቸው ደንበኞች “ደረጃ አንድ” ምድብ ላይ በመሆን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ኃላፊው ያስረዳሉ። ይህ አሰራር የተዘረጋው የፋይናንስ ተደራሽነት ለማስፋት በሚል እንደሆነም አክለዋል።  

አሁን በስራ ላይ ባለው መመሪያ መሰረት፤ በ“ደረጃ አንድ” ላይ የሚቀመጡ ደንበኞች የሞባይል ገንዘብ አገልግሎትን ለማግኘት ስማቸውን፣ የልደት ቀናቸውን፣ የመኖሪያ አድራሻቸው፣ ስልክ ቁጥራቸውን መሙላት የሚኖርባቸው ሲሆን የቅርብ ጊዜ ፎቶግራፍ ማቅረብም ይጠበቅባቸዋል። በዚህ ደረጃ የሚመደቡ ደንበኞች የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ለመጠቀም ምዝገባ የሚያከናውኑት፤ ቀድሟቸው በተመዘገበ ደንበኛ በኩል ነው።

“ደረጃ ሁለት” ላይ የሚቀመጡ ደንበኞች በአንጻሩ ከሚያሟሏቸው ግላዊ መረጃዎች በተጨማሪ መታወቂያቸውን ያቀርባሉ። የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆንም በሌላ ደንበኛ በኩል ማለፍ አይጠበቅባቸውም። “ደረጃ ሶስት” የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን የሚፈልጉ ተቋማትን በዋነኛነት የሚመለከት ነው። በዚህ ደረጃ የሚመደቡ ደንበኞች ተቋሙ የሚገኝበትን አድራሻ እንዲያቀርቡ በተጨማሪነት ይጠየቃሉ። 

በሶስት ተከፍሎ የነበረው የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ምደባ፤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አማካኝነት በየካቲት 2014 ዓ.ም. በተሻሻለው መመሪያ ወደ ሁለት ዝቅ እንዲል ተደርጓል። ይህ የመመሪያ ማሻሻያ ደንበኞች በቀን ውስጥ ማዘዋወር በሚችሉት የገንዘብ መጠን ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ እንዲነሳ አድርጎ ነበር። ከሁለት ሳምንት በፊት ለባለድርሻ አካላት የተሰራጨው አዲሱ ረቂቅ መመሪያ ግን ዕለታዊ የገንዘብ ዝውውር መጠን ላይ በድጋሚ ገደብ የጣለ ሆኗል።  

በኢትዮጵያ በብሔራዊ ባንክ የክፍያ እና የሂሳብ ማወራረጃ ሥርዓት ተጠባባቂ ዳሬክተር አቶ ሰለሞን ዳምጠው ተፈርሞ የተሰራጨው ይኸው ረቂቅ መመሪያ፤ የ“ደረጃ አንድ” ደንበኞች በአንድ ቀን ውስጥ ከ20 ሺህ ብር በላይ ማዘዋወር እንደማይችሉ አስፍሯል። በዚህ ደረጃ የተቀመጡ ደንበኞች፤ በአካውንታቸው ውስጥ መያዝ የሚችሉት የገንዘብ መጠን ከአምስት ሺህ ወደ 10 ሺህ ብር ከፍ እንዲልም ተደርጓል።

አዲሱ ረቂቅ መመሪያ በ“ደረጃ ሁለት” የተመደቡ ደንበኞች በቀን ውስጥ ማዘዋወር የሚችሉት የገንዘብ መጠን እስከ 300 ሺህ ብር ድረስ    መሆኑን አስቀምጧል። መመሪያው በዚህ ምድብ ያሉ ደንበኞች በአካውንታቸው ውስጥ መያዝ የሚችሉት የገንዘብ መጠን በ70 ሺህ ጨምሮ 100 ሺህ ብር አድርሶታል። ባለፈው ዓመት ተነስቶ የነበረው ገደብ በአዲሱ መመሪያ በድጋሚ እንዲጣል የታቀደው በሁለት ዋነኛ ምክንያቶች መሆኑን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያነጋገረቻቸው የብሔራዊ ባንክ ኃላፊ ገልጸዋል።

የመጀመሪያው ምክንያት ከገንዘብ ፖሊሲ ቁጥጥር ጋር የተያያዘ ነው። በሞባይል ገንዘብ አገልግሎት የሚንቀሳቀሰው ብር በባንክ ውስጥ የሚቀመጥ እና እንደ ብድር ላሉ ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎቶች የማይውል መሆኑ ገደቡ እንዲጣል ምክንያት መሆኑንም ያስረዳሉ። “ይህ ገንዘብ ገደብ የማይቀመጥለት ከሆነ፤ እዚህ ቦታ ላይ ተጠራቅሞ ለሌሎች አገልግሎቶች እንዳይውል ያደርገዋል” የሚሉት ኃላፊው፤ ይህ አይነቱ አካሄድ በገንዘብ ፖሊሲው ላይ መዛባትን ሊያስከትል እንደሚችል አብራርተዋል። 

የብሔራዊ ባንክ ኃላፊው በሁለተኛነት የጠቀሱት ምክንያት “በዲጂታል መንገድ” የሚዘዋወረው ገንዘብ ለዘረፋ የመጋለጥ እድል ያለው መሆኑን ነው። አብዛኛው ማህበረሰብ ጋር ያለው የዲጂታል ግንዛቤ “አነስተኛ” መሆኑን የሚያነሱት ኃላፊው፤ “ይህንን አደጋ ለመቀነስ የመጠን ገደብ የማይቀመጥበት ከሆነ በቀላሉ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ ለመጭበርበር ወይም ለስርቆት እንዲዳረግ ያደርጋል” ብለዋል። ይህንን አይነቱን ገደብ ማስቀመጥ “በሁሉም አገራት” ውስጥ የሚተገበር እና “ዓለም አቀፍ ልምምድ” ያለው መሆኑንም ጠቁመዋል። 

በአዲሱ ረቂቅ መመሪያ የገደብ አሰራር ተግባራዊ እንደሚደረግ ቢገለጽም፤ ከብሔራዊ ባንክ በሚሰጥ “የተለየ ፈቃድ” ከገደቡ በላይ የሆነ ገንዘብ ማስተላለፍ የሚቻልበት መንገድ እንዳለ አስቀምጧል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ይህንን ፈቃድ ለሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ሰጪው የሚፈቅደው፤ ወደ አገር ውስጥ ለሚመጣ ውጭ ምንዛሬ፣ እንዲሁም ለደመወዝ እና ታክስ ክፍያዎች መሆኑ በረቂቅ መመሪያው ላይ ሰፍሯል። 

ዜናው (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) በአማኑኤል ይልቃል

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

Ethioreview news

A journalist

የ”ጋላ ጠገበ” ፖለቲካ ባዶ ጉራ
How Many More Governments Will American-Trained Soldiers Overthrow?
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 20260
Load more
Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 20260
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 20260
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 20260
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedbusinesshotarchivetips
    © Copyright 2026, All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2
    • Home Demo news