Skip to content
VOE
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ሔማን በቀለ – ታይም መፅሄት የዓመቱ ምርጥ ያለው ህልመኛ ታዳጊ ሳይንቲስት

    September 4, 2024

    በዩክሬን በኩል ወደ አውሮፓ የሚደርሰው የሩሲያ የተፈጥሮ ጋዝ  ስራው እንዲቆም ተደረገ

    January 1, 2025

    በኦሮሚያ ክልል ማን፣ ምን ፈጸመ? የኢሰመኮ ሪፖርት

    August 5, 2025

    በኦሮሚያ በሌብነት ጉዳይ አናቱ ተፈርቷል፤ በ289 ሺህ ካሬ.ሜ.መሬት ላይ ማጣራት ተጀምሯል

    December 3, 2022

    የአፋር ክልል ከ፴ ዓመታት በሁዋላ በትግራይ ክልል የተወሰደበትን ኣንድ ቀበሌ “ነጻ አ ወጣሁ” አለ

    June 7, 2021
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ኢዜማ -የአንድ “ዘውግ ጠባቂ” የክልሎች ልዩ ሃይል መክሰም በጥንቃቄ የሚፈጸመ ትክክለኛ ውሳኔ ነው
News

ኢዜማ -የአንድ “ዘውግ ጠባቂ” የክልሎች ልዩ ሃይል መክሰም በጥንቃቄ የሚፈጸመ ትክክለኛ ውሳኔ ነው

Ethioreview newsEthioreview news—April 7, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ኢዜማ ያለ ቅጥ ጡንቻቸውን ያሳበጡ የክልል ልዩ ሃይሎች መክሰምና ወደ ፌደራሉ የጸጥታ መዋቅር መካተት እንዳለባቸው ሲያሳስብና በፖለቲካ የክርከር መድረክም በገሃድ የመከራከሪያ አጀንዳው አድርጎት እንደነበር በማስታወስ፣ ጥያቄው የሕዝብም እንደሆነ ጠቅሶ ነው ነው ድጋፉብ የሰጠው። ኢዜማ ውሳኔውን ሙሉ በሙሉ አግባብ እንደሆነ ሲያስታውቅ፣ ተግባራዊነቱ ግን ፈንጂ እንደማምከን ጥንቃቄ የሚሻው እንደሆነ አመላክቷል።

“ለአንድ ዘውግ ወይም ክልል ብቻ ጠባቂ ኾኖ የሚቋቋም ልዩ ኃይል ሀገር እና ሕዝብ ላይ አደጋ እንደሚፈጥር የታየው በትግራይ ክልል ታጣቂዎች ብቻ ሳይኾን በኹሉም የሀገራችን አካባቢዎች ተመሳሳይ ዝንባሌ እያስተዋልን ነው፡፡ በአስተዳደር ወሰን ይገባናል ጥያቄ መነሻ የኦሮሚያ ፣ የሶማሌ፣ የአማራ፣ የሲዳማ፣ የአፋር እና የቤንሻንጉል ልዩ ኃይሎች አንዳቸው ከሌላኛው ጋር መጋጨታቸው የአደባባይ ምሥጢር ነው” በማለት ድጋፉን የሰጠበትን ምክንያት ያብራራው ኢዜማ ይህ በዘውጌ ፖለቲካ ተቀኝቶ የተመሰረተ ሃይል ወደ ፌደራል የጸጥታ መዋቅር ሲዛወር ጥንቃቄ እንደሚያሻው የጠበቀ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

ለአንድ ዘውግ ወይም ክልል ብቻ ጠባቂ ኾኖ የሚቋቋም ልዩ ኃይል ሀገር እና ሕዝብ ላይ አደጋ እንደሚፈጥር የታየው በትግራይ ክልል ታጣቂዎች ብቻ ሳይኾን በኹሉም የሀገራችን አካባቢዎች ተመሳሳይ ዝንባሌ እያስተዋልን ነው፡፡ በአስተዳደር ወሰን ይገባናል ጥያቄ መነሻ የኦሮሚያ ፣ የሶማሌ፣ የአማራ፣ የሲዳማ፣ የአፋር እና የቤንሻንጉል ልዩ ኃይሎች አንዳቸው ከሌላኛው ጋር መጋጨታቸው የአደባባይ ምሥጢር ነው፡፡ ይህ ሁኔታ አሁንም ድረስ በአንዳንድ ክልሎች መካከል እየቀጠለ ነው፡፡ ይህም ንፁሀን ዜጎችን ከመጉዳቱም ባሻገር የሀገር ሉዓላዊነት ላይ አደጋ ደቅኗል፡፡ በመኹኑም፤ ከሕግ አግባብ ውጪ በአንድ ክልል ወይም ዘውግ ጠባቂነት የተቋቋሙ የክልል ልዩ ኃይሎች ከስመው በህጋዊ የፀጥታ መዋቅር ሥር መጠቃለላቸውን የምንደግፈው ተገቢ ውሳኔ ነው፡፡

ኢዜማ
More stories

ፑቲን የነዳጅና ጋዝ ሽያጭ በሩብል ገንዘብ ብቻ የማለታቸው ቀመር

March 30, 2022

በሀዋሳ ጉሙሩክ ጣቢያ ሁለት የቴሌኮም ማጭበርበሪያ መሳሪያዎች ተያዙ

May 18, 2021

በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ የተሰጠ መግለጫ

April 22, 2022

ትህነግ “የዘርፍከውን መልስ ተብሏል”- “አልዘረፍኩም ሳበድር የከረምኩት ነው” ብሏል

August 25, 2022

የኢዜማ ሙሉ መግለጫ

የክልል ልዩ ኃይሎችን ወደ ፌደራልና የክልል ህጋዊ የፀጥታ መዋቅር ውስጥ የማስገባት በጎ ጅምር አላስፈላጊ ውዥንብር ፈጥሮ ሌላ ሀገራዊ አደጋ እንዳይጋብዝ ጥንቃቄ ይፈልጋል!

የፌደራል መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎችን ወደ ፌደራልና የክልል ህጋዊ የፀጥታ መዋቅር ሥር እንዲጠቃለሉ ውሳኔ ማሳለፉን ከተለያዩ ምንጮች አረጋግጠናል፡፡ ትላንት መጋቢት 28 ምሽት ላይ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት የሰጠውን መግለጫም ተመልክተናል፡፡ ይህ ውሳኔ በእርግጥም ከመዘግየቱ በስተቀር ተገቢነቱ ላይ ጥያቄ ሊነሳበት አይገባም፡፡ባለፉት ጥቂት የማይባሉ ዓመታት ከሕጋዊ አሠራር ውጪ እንዲቋቋሙ የተደረጉ የክልል ልዩ ኃይሎች በፌደራል መንግሥት የፀጥታ ዕዝ ሥር እንዲገቡ መደረጉ ተገቢም ልክም ነው፡፡

ፓርቲያችን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የዘውግ ፖለቲካ ነፀብራቅ የኾኑ የክልል ልዩ ኃይሎች እየፈጠሩ ከነበረው ሀገራዊ አደጋ አንፃር ከስመው ወደ ህጋዊ የፀጥታ መዋቅር ውስጥ እንዲገቡ፤ በተለያዩ የትንታኔ ሰነዶቹ እና በምርጫ ክርክር መድረኮች ጭምር ሲሟገት እንደነበር ይታወቃል፡፡ ይህ የኢዜማ አቋም እና ስጋት ትክክለኛነት የትግራይ ክልል ልዩ ኃይሎች የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ላይ በከፈቱት ጦርነት በገሃድ ተረጋግጧል፡፡

ለአንድ ዘውግ ወይም ክልል ብቻ ጠባቂ ኾኖ የሚቋቋም ልዩ ኃይል ሀገር እና ሕዝብ ላይ አደጋ እንደሚፈጥር የታየው በትግራይ ክልል ታጣቂዎች ብቻ ሳይኾን በኹሉም የሀገራችን አካባቢዎች ተመሳሳይ ዝንባሌ እያስተዋልን ነው፡፡ በአስተዳደር ወሰን ይገባናል ጥያቄ መነሻ የኦሮሚያ ፣ የሶማሌ፣ የአማራ፣ የሲዳማ፣ የአፋር እና የቤንሻንጉል ልዩ ኃይሎች አንዳቸው ከሌላኛው ጋር መጋጨታቸው የአደባባይ ምሥጢር ነው፡፡ ይህ ሁኔታ አሁንም ድረስ በአንዳንድ ክልሎች መካከል እየቀጠለ ነው፡፡ ይህም ንፁሀን ዜጎችን ከመጉዳቱም ባሻገር የሀገር ሉዓላዊነት ላይ አደጋ ደቅኗል፡፡ በመኹኑም፤ ከሕግ አግባብ ውጪ በአንድ ክልል ወይም ዘውግ ጠባቂነት የተቋቋሙ የክልል ልዩ ኃይሎች ከስመው በህጋዊ የፀጥታ መዋቅር ሥር መጠቃለላቸውን የምንደግፈው ተገቢ ውሳኔ ነው፡፡

አፅንኦት ሰጥተን የምናሳስበው ጉዳይ ቢኖር የክልል ልዩ ኃይሎች ወደ ህጋዊ የፀጥታ መዋቅር ሥር መግባታቸውን ከልባችን የምንደግፈው ውሳኔ ሆኖ እያለ ፤ አተገባበሩ ፈንጅ የማምከን ያህል ከፍተኛ ጥንቃቄ እንደሚፈልግ ግን ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ኹሉ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡ በተለይም በሀገራችን ሥር ከሰደደው የዘውግ ፖለቲካ ጡዘት አኳያ አፈጻጻሙ በተጠና መልኩ መኾን አለበት፡፡

እንደምሳሌ የምናነሳው በቅርቡ ከአሸባሪነት መዝገብ እንዲፋቅ የተደረገው የህወሓት ቡድን በሚቆጣጠራቸው መገናኛ ብዙኃን በኩል በአሁኑ ወቅት በአማራ ክልል ሥር ያሉ አካባቢዎችን ስለማስመለስ እንደሚሠራ በስፋት እያስተጋባ ባለበት በዚህ ወቅት፤ ይህንን ውሳኔ በጥድፊያ እና በድብቅ ተግባራዊ ለማድረግ መሞከር አደገኛ ውጤት እንደሚያመጣ የፌደራል መንግሥት ሊገነዘበው ይገባል፡፡ ህወሓት የታጠቃቸውን መሣሪያዎች መፍታቱ በግልጽ ባልታወቀበት ሁኔታ የትግራይ አዋሳኝ ክልሎች ዳግም የመወረር ስጋት ቢያድረባቸው የሚያስወቅስ አይደለም ፡፡ ስለዚህም የውሳኔውን አፈጻጸም ቅደም ተከተል በተመለከተ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት ኢዜማ ያምናል፡፡

ከላይ በጠቀስነውና ይህን በመሰሉ ሌሎች ምክንያቶች የተጀመረው በጎ እርምጃ አላስፈላጊ ውጥንቅጥ ፈጥሮ ሌላ ሀገራዊ አደጋ እንዳይጋብዝ የሚከተሉት ጥንቃቄዎች እንዲደረጉ እናሳስባለን፡፡

1) መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎችን ወደ ህጋዊ የፀጥታ መዋቅር ውስጥ ለማካተት የወሰነውን ውሳኔ እስካመነበት እና ሌላ ድብቅ የፖለቲካ ሴራ ከሌለ በስተቀር፤ ውሳኔውን በድብቅ ለማስፈጸም የሚያደርገው እንቅስቃሴ አላስፈላጊ ውዥንብር እንዱሁም ግጭት ከመፍጠር ያለፈ ፋይዳ እንደሌለው መገንዘብ አለበት፡፡ ሰለሆነም ልዩ ኃይሉን ወደመደበኛነት ለመቀየር የሚከተለውን ፍኖተካርታ ደረጃ በደረጃ አካሄዱን ለህዝብ በተደጋጋሚና ግልፅ በሆነ መልኩ በተለያዩ ቋንቋዎች ማብራሪያ መሰጠት አለበት። ይህ በማህበረሰቡ ውስጥ የሚፈጠረውን ውዥንብር ከማጥፋቱም በላይ በመንግስት እና በሂደቱም ላይ ያለውን ጥርጣሬ ይቀንሳል ብለን እናምናለን።

2) የሁሉንም ክልሎች ልዩ ኃይሎች ወደ ህጋዊ የጸጥታ ተቋማት ውስጥ ማካተት የሚኖረውን ሀገራዊ ጠቀሜታ እና አፈጻጸም በተመለከተ ከኹሉም የክልል መንግሥታት ኃላፊዎች እና የፀጥታ ተቋማት ጋር ተነጋግሮ መግባባት ላይ መድረስ በቅድሚያ ሊኾን እንደሚገባ ለማስታወስ እንወዳለን፡፡

3) የጉዳዩን ሀገራዊ ፋይዳ ለሚመለከታቸው የሀገራችን የፖለቲካ ልሂቃን ከማስረዳት ጀምሮ፤ ይህንን ውሳኔ ሰበብ በማድረግ ሊሸረቡ ከሚችሉ ፖለቲካዊ ደባዎች መታቀብም በከፍተኛ ደረጃ ሊታሰብበት ይገባል፡፡ ከአንዳንድ የፖለቲካ ተዋንያን እየተሰማ እንዳለው “የአንዱን ክልል ልዩ ኃይል አፍርሶ ሌላኛውን በድብቅ የማጠናከር ሴራ” እንዳይኖር ማድረግ እንደሚገባም ውሳኔውን ለሚያስፈጽሙ የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስ አዛዦች በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

4) የክልሎች ልዩ ኃይሎች ወደ ፌደራል እና የክልል የፀጥታ መዋቅር ውስጥ በሚገቡበት ይሁን የሲቪል ማህበረሰቡን በሚቀላቀሉበት ጊዜ አስተማማኝ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርኃግብር ወይም ተሃድሶ ሊከናወን ይገባል፡፡ የክልል ልዩ ኃይሎች አባላት ወደ ህጋዊ የፀጥታ መዋቅር ዕዝ ሥር እንዲገቡ የተደረገበትን ሀገራዊ ፋይዳ ማሳወቅ፤ የሚኖራቸውን የግልፅነት ጥያቄ መመለስ እና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በተመለከተ ማስተማመኛ መስጠትም በውዥንብር ምክንያት ሊፈጠሩ የሚችሉ ተግዳሮቶችን እንደሚያስቀር መገንዘብም ከመንግሥት አካላት ይጠበቃል፡፡

5) በብልፅግና ፓርቲ ውስጥ ያለውን ሽኩቻ ከፍ ሲል ወደ መንግስት ብሎም ወደ ህዝብ ውስጥ ተሰራጭቶ ለሀገር ስጋት እንዳይፈጥር፤ የፌደራሉ መንግሥት ይህንን ውሳኔ ለማስፈጸም የሚያደርገው ተግባራዊ እንቅስቃሴ በጥድፊያ እንዲሁም በማንአለብኝነት ሳይኾን በመግባባት፤ በመተማመን እና በግልጸኝነት መንፈስ ሊኾን ይገባል፡፡ ይህን ባለማድረግ ለሚፈጠር ውዥንብር፤ ግጭት እና ውድመት የፌደራሉ መንግሥት ተጠያቂ መኾኑን ተገንዝቦ ውሳኔውን በጥንቃቄ እንዲያስፈጽም እናሳስባለን፡፡

ለኹሉም የፖለቲካ ተዋንያን በሙሉ የምናስተላልፈው መልዕክት የክልል ልዩ ኃይሎችን የፈጠረው መዋቅራዊ አሠራር ጭምር በጥልቀት እንዲታሰብበት ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ክልሎች፤ መገናኛ ብዙኀን፤ የንግድ ተቋማት፤ ባንኮች፤ የስፖርት ቡድኖች፤ የሙያ ማኅበራት፤ የምሑራን ስብስብ እና ሌሎችም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልኾኑ ተቋማት በአንድ ዘውግ ስም ተቋቁመው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተባብሮ ወደ ልማት ሳይኾን ተከፋፍሎ ወደ እርስ በእርስ ግጭት እንዲገባ እንደሚያደርጉት ለአፍታም መዘንጋት የለበትም፡፡

ይህ የዘውግ ክፍፍል ወደ ሰማያዊዎቹ የሃይማኖት ተቋማት ጭምር ገብቶ ችግር ፈጥሯል፡፡ አንድ ተቋም ለአንድ ዘውግ ጥቅም ብቻ ሲቋቋም በአንድ ሀገር ሕዝብ መካከል “እኛና እነሱ” የሚል ክፍፍል እና አሉታዊ ፉክክር በመፍጠር የግጭት መንስኤ እንደሚኾን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ የክልል ልዩ ኃይሎችም የዚሁ የዘውግ ፖለቲካ ነፀብራቅ እንደኾኑ መታወቅ አለበት፡፡ ስለዚህም፤ የዚህ ሕጋዊ እና መወቅራዊ የዘውግ ክፍፍል መነሻ ምክንያት የኾነው የዘውግ ፖለቲካ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ከሀገራችን ሊወገድ ይገባል፡፡

ፓርቲያችን ኢዜማ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንደወተወተው፤ የዘውግ ፖለቲካ ካልተወገደ ኢትዮጵያ አትድንም፡፡ ስለኾነም፤ ሀገራችን በዘላቂነት እፎይታ እንድታገኝ ከዘውግ ፖለቲካ ወደ ዜግነት ፖለቲካ መሸጋገር ምርጫ ሳይኾን ግዴታ ነው፡፡ ይህ እንዲሳካም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከፓርቲያች ጎን ቆሞ የፖለቲካ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ኢዜማ

NEWSPOLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በመላው ኢትዮጵያ መከላከያ አገርና ድንበር እንዲጠብቅ ስምሪት መቀበሉን መንግስት አስታወቀ
እንዲገለጥልን የልዩ ሃሎችን መሟሟት ከአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አካሄድ ጋር እንሳፋው!
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2