Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ታላቁ ህዳሴ ግድብ በመገባደጃ ምዕራፍ ላይ

    April 1, 2023

    የአሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችል ስራ መጀመሩን ይፋ አደረገ

    August 22, 2024

    ዶናልድ ትራምፕ በቁጥጥር ሥር ውለው በቀረበባቸው ሰላሳ አራት ክሶች ጥፋተኛ አይደለሁም አሉ

    April 6, 2023

    የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰነድ የሌላቸው የኤርትራዊ ስደተኞች መታሰራቸውን ኮነን፤ “ያለ ህጋዊ ማስረጃ የትኛው አገር መኖር ይቻላል?”

    June 4, 2023

    ቻይናዊው የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ከ9 ግብረ አበሮቻቸው ጋር የውጭ አገር ብሮች በማተምና በጥቁር ገበያ ወንጀል ታስረው ፍ/ቤት ቀረቡ

    September 5, 2023
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  ትህነግ “የዘርፍከውን መልስ ተብሏል”- “አልዘረፍኩም ሳበድር የከረምኩት ነው” ብሏል
News

ትህነግ “የዘርፍከውን መልስ ተብሏል”- “አልዘረፍኩም ሳበድር የከረምኩት ነው” ብሏል

Ethioreview newsEthioreview news—August 25, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

መቐለ ከተማ ከሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) መጋዘን ” … የትግራይ ኃይሎች መቐለ በሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን በኃይል በመግባት 12 የነዳጅ ታንከር 570,000 ሊትር ነዳጅ ዘርፈዋል ” ሲሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች የሰጡትን መግለጫ ተከትሎ አሜሪካ “የተሰረቀው ነዳጅ ጉዳይ አሳሰበኝ” ስትል ሩሲያ በቀጥታ አውግዛለች። ራሱ ድርጅቱ ዕርዳታ ማከፋፈል ሲቆም የሚደርሰው አደጋ የከፋ መሆኑንን በማመለከት ” ነዳጄን መልሱ” ብሏል። ትህነግ በበኩሉ ያበደርኩትን ነው የወሰድኩት ብሏል።

የአለም ምግብ ፕሮግራም ዝርፊያውን ካወገዘ በሁዋላ በትህነግ የተዘረፈበት 570 ሺህ ሊትር ነዳጅ እንዲመለስለት የጠየቀው ካልተመለሰ የሰብአዊ ድጋፍ ለማከናወን እንደሚፈተን አጥብቆ በማስጠንቀቅ ነው።

Hours ago, Tigrayan authorities stole 570,000 liters of fuel for @WFP operations in #Tigray! Millions will starve if we do not have fuel to deliver food. This is OUTRAGEOUS and DISGRACEFUL. We demand return of this fuel NOW.

— Cindy McCain (@WFPChief) August 24, 2022

ዋና ዳይሬክተሩ ዴቪድ ባስሊ ለሰብአዊ ድጋፍ አገልግሎት ለማዋል በመቀሌ የተቋሙ መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ የነበረውንና በትህነግ ታጣቂዎች የተዘረፈውን ነዳጅ አስመልክቶ መግለጫ አሰራጭተዋል።

More stories

“ትህነግ ከጁንታነትም ወርዶ በየጫካው ተሹለክላኪ የእህል ሌባ ሆኗል፣ ከያለበት እየታደነ ነው “ሜ/ጀ መሐመድ ተሰማ

April 7, 2021

የመ/ሰራዊትን መለያ ለብሶ ከሱዳን ወደ ወልቃይት ሊገባ የነበረ የትህነግ የሽብር ሃይል ተደመሰሰ፤ አንገታቸው የተቀላ መኮንኖች ፊልም ሊታዩ ነው

May 13, 2021

ከሱዳን የተነሳ የትህነግ ሃይል (ሳምሪ) ሳይዋጋ ሙሉ በሙሉ ተማረከ

August 11, 2021

የመንግስት ማጅራት መቺዎች ፈተና ሆነዋል – ሃላፊዋ አምነዋል

May 9, 2022

በመግለጫቸው በዝርፊያው ሳቢያ ምግብ፣የአፈር ማዳበሪያ፣ መድሃኒትና አስቸኳይ የዕርዳታ ቁሳቁሶችን ለማሰራጨት እንደማይችል፣ ጀነሬተሮችንም ማስነሳት እንደሚሳነው ዘርዝረዋል።

መንግስት ለሰብአዊ ድጋፍ ሲል አሳልፎት የነበረው የተኩስ ማቆም ውሳኔ ባለፉት ወራት በትግራይ ክልል አምስት ሚሊዮን ለሚሆኑ የሰብአዊ ድጋፍ ለማድረስ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ፈጥሮ እንደነበር አስታውሰዋል።

በድርጅቱ የመቀሌ መጋዘን በቅርቡ ከማዕከል የተጓጓዙ ከግማሽ ሚሊዮን ሊትር በላይ የያዙ አስራሁለት ታንከሮችን የተዘረፉት ረቡዕ ማለዳ ነው። የታጠቁ ሃይሎች በሃይል ገብተው ዘረፋውን እንዳካሄዱ ተረጋግጧል። አሜሪካ የነዳጅ ዝርፊያውን “አሳሰበኝ” ስትል ሩሲያ ኮንናለች። ድርጊቱ ተቀባይነት እንደሌለው በይፋ አስታውቃለች።

በትግራይ ክልል 5 ነጥብ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ  ዜጎች ለከፋ አደጋ እንደሚጋለጡ ያመለከቱት የዓለም የምግብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዘረፋውን የፈጸመው ትህነግ ነዳጁን እንዲመልስ ምክንያት አስቀምጠው አስጠንቅቀዋል።

ትህነግ “ዘርፈሃል” ከተባለ በሁዋላ ባወጣው መግለጫ ያበደረውን መውሰዱ “ሌባ” እንደማያሰኘው አመልክቶ ነዳጁን የወሰደው ለማህበረሰብ አገልግሎት እንደሆነ ዘርዝሯል። ለዓለም ምግብ ፕሮግራም ከስድስት መቶ ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ አበድረው እንደነበርም አመልክተዋል።

ትህነግ ለህዝብ አገልግሎት ሲል ነዳጁን መውሰዱን ቢገልጽም መንግስት ግን በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አማካይነት ወደ ትግራይ ክልል የሚገባው ሰብዓዊ ዕርዳታ ለታለመለት ዓላማ እየዋለ ስለመሆኑ ማስተማመኛ ይሰጠኝ ሲል ጥያቄውን አስፍቶ አቅርቧል። ትህነግ ነዳጁን የዘረፈውም ለጀመረው ጦርነት ዝግጅትና ማከናወኛ እንደሆነ አመልክቷል።

በቆቦና በአካባቢው ለከፈቱት ጥቃት ማስፈጸሚያ እንዲሆን ነዳጁን መዘረፉ ብቻ ሳይሆን ዝርፊያውን ለማስቆም የሞከሩ የሰብዓዊ እርዳታ ባለሙያዎችን አስሮ እንደነበር ሪፖርት እንደደረሰው ጠቅሶ  የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት በመግለጫው ይፋ አድርጓል።

ትህነግ በመግለጫው ለትግራይ ዕርዳታ ፈላጊዎች የሚሆን ነዳጅ ለዓለም ምግብ ድርጅት ማበደራቸውን ድርጅቱም እንደሚመለስ ስምምነት እንደነበር አመልክቷል። በዚህም ምክንያት ሌባ ሊባል እንደማይችል ሞግቷል።

መከላከያ ትግራይን ለቆ ሲወጣ የነበረ ክምችት፣ መንግስት ለዕርዳታ በሚል ከሚልከውና በወረራው ንግስት ወቅት ትህነግ ዘርፎ ወደ ትግራይ ያዘዋወረው፣ እንዲሁም ልክ መሳሪያ በተለያዩ ሰዋራ ቦታዎች እንደሚቀበረው ሁሉ ነዳጅም በተመሳሳይ ከመሬት በታች ለረዥም ጊዜያት ይከማች እንደነበር፣ ከሁሉም በላይ የገሪቱ ትልቁ የነዳጅ ዲፖ የሚገኘው እዛ ስለሆነ ዕርዳታ ለማዳረስ ትህነግ የሚያቀርበውን የነዳጅ ጥያቄ መንግስት ሳይቀበል መቅረቱ ይታወሳል። ይህን የሚያውቀው የዓለም የምግብ ድርጅትም ሆነ ሌሎች ድርጅቶች መንግስትን ከመኮነን ውጭ በትግራይ ያለውን ነዳጅ ስለመጠቀም በይፋ ተናግረው አያውቁም።

የዘርፊያው ዜና ይፋ መሆኑን ተከትሎ ትህነግ 600 ሺህ ሊትር ነዳጅ ማበደሩን ይፋ ማድረጉ “አከማችቷል” በሚል የሚቀርበበትንና ሲያስተባብል የነበረውን ጉዳይ ባደባባይ ቅጥፈት እንደሆነ የሚያጋልጥ መሆኑ እየተነገረ ነው።

ዜናውና የትህነግ መልስ በነዳጅ ችግር ምክንያት እርዳታ ማከፋፈል አልተቻለም በሚል የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርና የትህነግ አባል ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ሲያቀርቡ የነበረውን ስሞታም የሚያቆሽሽ እንደሆነ ተያያዞ እየተጠቆመ ነው።

አሜሪካ ትህነግ ምንም ሲፈጽም “አሳስቦኛል” ከማለት ውጭ ሌላ ቃል መተቀም ስለማትወድ “ የነዳጅ መዘረፍ ጉዳይ አሳስቦኛል” ስትል መግለጫ አውጥታለች። ሩሲያ በበኩሏ ድርጊቱን ሙሉ በሙሉ ተቃውማለች።

ትህነግ በዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን ውስጥ የነበረ 570 ሺህ ሊትር ነዳጅ መዝረፉ አስነዋሪና ተቀባይነት የሌለው ተግባር መሆኑን በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን መናገራቸውን ኢዜአ አስታውቋል።

በመቀሌ በሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን ውስጥ የነበረ 12 ታንከር ወይም 570 ሺህ ሊትር ነዳጅ በህወሃት መዘረፉን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፈን ዱጃሪክ መግለጻቸው ይታወቃል።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቤስሌይ ህወሃት የዘረፈውን ነዳጅ በአፋጣኝ እንዲመልስ የጠየቁ ሲሆን፤ በነዳጁ መዘረፍ ምክንያት የሰብዓዊ ርዳታዎችን ለማሳለጥ እንቸገራለን ብለዋል።

በዚህ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን፤ በመጋዘኑ ውስጥ የነበረው የምግብና የነዳጅ ክምችት በአስችጋሪ ሁኔታ ለነበሩ ዜጎች ሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል እንደነበር ጠቅሰዋል።

በሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ችግር ሰለባ ለሆኑ የትግራይ ማህበረሰብ መድረስ የነበረበት እርዳታ በሽብር ቡድኑ መዘረፉ ተቀባይነት የሌለውና አስነዋሪ ተግባር ነው ብለዋል።

ዘራፊዎቹ ነውረኛ ድረጊታቸውን ክደው ከተወሰነ ጊዜ በኋላ የትግራይ ህዝብ ለችግር ተዳርጓል የሚል የተለመደ ልፈፋቸውን እንደሚቀጥሉና የህዝብ ተቆርቋሪ ለመምሰል እንደሚሞክሩም ነው የገለጹት። በትህነግ የሽብር ቡድን የተፈጸመውን ዝርፊያ የትኛውም የዓለም ማህበረሰብ የማይደግፈው ድርጊት ነው ብለዋል።

የተፈጸመውን ድርጊት ማውገዝ እንደሚገባ ጠቅሰው፤ አንዳንድ ድርጊቱን በዝምታ የሚያልፉ አካላትም እውነታው በገሃድ መውጣቱ እንደማይቀር ማወቅ አለባቸው ማለታቸውን የኢዜአ መረጃ ያስረዳል።

“አብረው ሲሰሩ ነበር ምን አጣላቸው” ሲሉ የጠየቁም እጅግ በርካታ ናቸው። መንግስት ድርጊቱን “የጦር ወንጀል ነው” በሚል በትግራይ ዕርዳታ ለሌላ ተግባር ስለሚውል ሙሉ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቋል። በተጨማሪም በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አማካይነት ወደ ትግራይ ክልል የሚገባው ሰብዓዊ ዕርዳታ ለታለመለት ዓላማ እየዋለ ስለመሆኑ ማስተማመኛ እንዲሰጠው ጥያቄ አቅርቧል።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ወደ ትግራይ ክልል ሊያስገባ የነበረው አደገኛ ዕፅ ተያዘ
ትህነግ ማንነቱን ለዓለም አጋልጧል፤ በጦር ወንጅልነት ሊጠየቅ ይገባል
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2