Skip to content
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
  • News
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    Western Pressure on Ethiopia Intended to See Weak Gov’t, Nation – Scholars

    July 10, 20210

    Journalist demands UNWFP to tell truth about missing trucks

    October 3, 20210

    ብርሃኑ ባይህ እና አዲስ ተድላ ምህረት ሊደረግላቸው ይችላል ተባለ

    December 19, 20200

    አብንና ባልደራስ ከተሸነፉ ” ውጤቱን አንቀበልም” ሊሉ የሚችሉ ፓርቲዎች እንደሚሆኑ ዲፕሎማቶች ገለጹ

    May 23, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1866
  • Design
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ሚስጥራዊ የቻይና ፖሊስ ጣቢያዎች በአሜሪካ ተገኙ

    December 19, 20240

    ሦስተኛው ዕድል እንዳይባክን … !

    May 21, 20220

    “Why I decided to extend my time at the club”

    May 24, 20230

    የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ዋና የጦሩ መሪ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለመንግስት እጁን ሰጠ

    February 24, 20220

    “Ethiopia’s success reflects a new alternative for Africa’s development”

    January 29, 20240
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • Video
    video

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለፓርላማ የሰጡት ማብራሪያ

    July 4, 2024
    video

    የህብታቸውን ምንጭ የሚያውቁ አይሰጉም! ማብራሪያ

    June 22, 2024
    video

    የሀገር አቀፍ የምክክር ሂደት ይፋዊ የማስጀመሪያ ሥነ ስርዓት

    June 4, 2024
    video

    የምክክር ሂደት ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር

    June 4, 2024
    Prev Next Showing 1 Of 5
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • News
  • Design
  • Video
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  ፍራንኮ ቫሉታ ቢፈቀድም የዋጋ ንረቱን አልቀነሰም፤ ለምን?
NewsSOCIETY

ፍራንኮ ቫሉታ ቢፈቀድም የዋጋ ንረቱን አልቀነሰም፤ ለምን?

Ethioreview newsEthioreview news—May 3, 20230
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በፍራንኮ ቫሉታ ዋና የሚባሉ የምግብ ምርቶች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ ቢፈቀድም የዋጋ ንረቱን እንድተሰቀለ ነው። ባለሙያዎች የሚሉትና የሚሰጡት ዓለም ዓቀፍ ዕውነታን የተንተራሰ ምክንያት እንዳለ ሆኖ ሌብነቱም ትልቅ አስተዋጾ እንዳለው ይሰማል። ሌብነቱ ከምንዛሬ አጠባ ጀምሮ ትርፍ ማጋበስ፣ እንዲሁም ሆን ተብሎ ህዝብ ምሬት ውስጥ እንዲገባና እንዲያምጽ የማስገደጃ መሳሪያ እየተደረገ መሆኑንን የሚገልጹ አሉ።

በሁሉም መስክ ሴራ የሚንጣት ኢትዮጵያ አሁን ላይ ካሉት ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎች ጋር ተዳምሮ ፣ ከውጭ የሚገባውን ብቻ ሳይሆን የአገር ውስጥ ምርትን ሳይቀር መደበቅ፣ ማጭበርበር እንዲሁም በህገወጥ ወደ ጎረቤት አገር ማስረግ፣ ኮንትሮባንድ ላይ ማተኮር ለኑሮ ውድነቱ ቅድሚያ የሚይዙ እውነታዎች ናቸው።

የነዳጅ ድጎማ ላይ ሳይቀር በርብርብ ሲካሄድ የነበረውን ዝርፊያ ለማስቆም መንግስት የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ሲዘረጋ የተሰማው ጩኸትና ጩኸቱ እንዲስተጋባ የተደረገበት አውድ አንድ ማሳያ ነው። ይህንኑ ጩኸት እየተቀባበሉ ያሰራጩት ሚዲያዎች ዝርፊያውን እንዳላየ ከማለፍ ውጭ” ህዝብ ተሰቃየ” በሚል ድጎማው ህዝብን እንዲጠቅም አለመስራታቸው ሴራው ምን ያህል የተደራጀ እንደሆነ ያሳያል ሲሉ ሰሞኑንን አስተያየት የሰጡ አሉ።

ይህን እንደምሳሌ የሚያነሱ ከሙያዊ ትንተናው በሌላ ጎኑ ህዝብ ለራሱ ህልውና ሲል በችጋር ሊጨርሱት የተነሱ ስግብግቦች ወደ ቀልባቸው እንዲመለሱ በተለያየ ጊዜ በተደረጉ ምክክሮች ተጠይቋል። ለአሁን አዲስ ዘመን ይህን ብሏል ከታች ያንብቡ።

More stories

አዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ ትግበራ መስከረም 1 ሊጀምር ነው

September 6, 2024

የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ማንበብና መጻፍ ለማይችሉ ዲግሪ እንደሚሰጡ ተገለጸ

February 4, 2021

አማራ ክልል “ተወረሩ” ያላቸውን ስፍራዎች እያስለቀቀና እያጸዳ መሆኑንን አስታወቀ

July 16, 2021

ይናገር ደሴ “እየተዶለተብንና እየተቀመመልን ያለው ኢትዮጵያን የመበተን ሴራ ጉዳይ ለእኛ ኢትዮጵያውያን አዲስ ነገር አይደለም”

May 18, 2021

መንግሥት በምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ምርቶች ላይ እየተስተዋለ ያለውን የዋጋ ንረት ለማርገብ የተለያዩ የመፍትሔ አማራጮችን እየወሰደ ነው። በተለይም ከውጭ የሚገቡ እንደ ፓስታ፤ ማካሮኒ፤ ዱቄትና የሕፃናት ምግቦች፣ የምግብ ዘይትና የመሳሰሉት ምርቶች ላይ የነበረውን ታክስ በማንሳት ከታክስ ነፃ ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ በፍራንኮ ቫሉታ በኩል መፍቀዱ ይታወሳል።

ይሁን እንጂ የእነዚህ ምግቦች ዋጋ አሁን ላይ በከፍተኛ ደረጃ ጨምሮ ለኅብረተሰቡ ፈታኝ ሆነው እየተስተዋሉ ነው። ይህ ለምን ሆነ፤ እያጋጠመ ያለውን የዋጋ ንረት ለመግታት የመፍትሔ እርምጃዎች  እንደሚያስፈልጉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ሀሳባቸውን ያጋራሉ።

የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ዶክተር ዳዊት ሀዬሶ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ መንግሥት በፍራንኮ ቫሉታ አማካኝነት እንደ ፓስታ፤ ማካሮኒ፣ ዱቄት፤ የሕፃናት ምግብና መሰል የፍጆታ ምርቶች ከታክስ ነፃ እንዲገቡ ፈቅዷል። አብዛኛዎቹ ምርቶች ከውጭ የሚገቡ እንደ መሆናቸው መጠን ከታክስ ነፃ ሆነው እንዲገቡ በፍራንኮ ቫሉታ በኩል ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል። ነገር ግን በነፃ እንዲገቡ ቢደረጉም ዋጋቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። ለዚህ ደግሞ ምርቶቹ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡት በውጭ ምንዛሬ አማካኝነት ከመሆኑ አንጻር የአገር ውስጥ የዋጋ ግሽበት ብቻ ሳይሆን የምርቶቹን ዋጋ መናር የሚጎዳው ከውጭ የመጣ የዋጋ ግሽበት( imported inflation) የሚባል በመሆኑ በምርቶቹ ዋጋ ላይ ጫና አሳድሯል ይላሉ።

የምርቶቹ በሚፈለገው መጠን ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡና ዋጋቸው እንዳይቀንስ ያደረገው አንዱ ምክንያት ከምንዛሪ ጋር የተያያዘ ነው የሚሉት የምጣኔ ሀብት ባለሙያው፤ የማካሮኒ፣ ፓስታና ዱቄት ምርቶች በብዛትና በስፋት በግብዓትነት የሚጠቀሙት ስንዴን ነው። ስንዴን በብዛት የሚያመርቱት አገሮች በተለምዶ የዳቦ ቅርጫት የሚባሉት ሩሲያና ዩክሬን ናቸው፤ ነገር ግን አገራቱ በጦርነት ውስጥ ያሉ በመሆናቸው የግብዓት እጥረት ተፈጥሯል። የግብዓት አቅርቦት እጥረት ደግሞ አንዱ ለዋጋ ንረት ምክንያት ይሆናል። ይህም የምርቶቹ ዋጋ በሚፈለገው ልክ እንዳይቀንስና እንዳይረጋጋ አድርጎታል ነው ያሉት።

በሌላ በኩልም ምርቶቹ አገር ውስጥ እየገቡ ቢሆንም አገር ውስጥ ያለው የሰላም እጦትና አለመረጋጋት ምርቶቹን በማቅረብ ሂደት ውስጥ ዋጋቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። የጉልበት ዋጋ (labor coast) ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣበት ሂደት አለ። ይህም ያላደጉ አገሮችን ብዙ ጊዜ ዋጋቸው የሚተመነው በጉልበት ነው። በአሁኑ ወቅት ላይ ቁርስ፣ ምሳና እራት፣ እየጨመረ ከመሄዱ አንጻር የጉልበት ዋጋ መጨመሩ ዋጋቸው በተፈለገው መንገድ እንዳይሆን አድርጓል። ከትራንስፖርት ጋር የተያያዘው ዋጋ የጨመረበት ሁኔታ ስላለ ለምርቶቹ የዋጋ መናር አሉታዊ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን የምጣኔ ሀብት ባለሙያው በምክንያትነት ያነሳሉ።

ዶክተር ዳዊት እንደሚሉት፤ የገበያ ዋጋ የሚባሉት በአገር ውስጥም ተጨባጭ በሆነ መንገድ ጭማሬ ከማሳየት አንጻር በፊት ከነበረበት ሁኔታ ዋጋው ያልቀነሰበት ሁኔታ እየተስተዋለ ነው። ነገር ግን በፍራንኮ ቫሉታ አማካኝነት ከታክስ ነፃ ባይገቡ ኖሮ ዋጋው ምን ያህል ይንር ነበር ብሎ ማሰብም ተገቢ ነው። ፍራንኮ ቫሉታ ባይፈቀድ የምርቶቹ ዋጋ አሁን ካለው በላይ ከ25 እስከ 50 በመቶ ጭማሪ እንደሚያሳይ መገመት ይቻላል።

ከዚህ አኳያ በተወሰነ መልኩም የዋጋ ማረጋጋት አስተዋጽኦ እንዳለው መገመት ያስችላል። ለምሳሌ ከጎረቤት ስንዴን በስፋት ወደ ውጭ ገበያ ከሚያቀርቡ እንደ ግብጽና ሱዳን የመሳሰሉ አገራት ጋር ሲነጻጸር የስንዴ ዋጋ ሲታይ  በእነዚህ አገራት ላይ ዜጎቻቸው መግዛት የማይችሉበት ደረጃ ደርሰዋል። በኢትዮጵያ የተፈቀደው ፍራንኮ ቫሉታም በተወሰነ መልኩም ቢሆን የምርቶቹ ዋጋ ከዚያም በላይ የናረ እንዳይሆን እገዛ እንዳለው ገልጸዋል።

በፍራንኮ ቫሉታ ከታክስ ነፃ በሆነ መልኩ መግባታቸው መልካም ነገር ነው የሚሉት ሌላኛው የፋይናንስና የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ኃይለመስቀል ጓዙ፤ ነጋዴው ማህበረሰብ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን የሚገዛው በጥቁር ገበያ በሚያገኘው ምንዛሬ ነው። ይህም ማለት በባንክ ያለው የአንድ ዶላር ምንዛሬ 54 ቢሆንም እነሱ አንድን ዶላር ከመቶ ብር በላይ ገዝተው ዕቃዎችን የሚያስገቡ ነጋዴዎች ይኖራሉ። ይህም ለእነዚህ ምርቶች ዋጋ መናር አንዱ ምክንያት ነው። በሌላ በኩልም ዕቃዎቹ የሚጓጓዙበት ዋጋ መጨመሩም ሌላኛው ለዋጋቸው መናር ምክንያት መሆኑን ጠቅሰዋል።

አቶ ኃይለመስቀል፤ የምርቶቹ ከታክስ ነፃ መደረግ በተወሰነ መልኩ የዋጋ ንረቱን መቀነስ ቢያስችልም ሙሉ በሙሉ ግን ዋጋውን መቀነስ አይችልም። ምክንያቱም ምርቶቹን ከታክስ ነፃ በሆነ መንገድ እንዲያስገባ የተፈቀደለት አካል ምርቶቹን ለማስገባት ምንዛሬ በጥቁር ገበያ ሊገዛ ይችላል። የጥቁር ገበያ ዋጋን አስቦ የሚደረግ ግብይት ሊኖር ስለሚችል የምርቶቹ ዋጋ የሚጨምርበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል። በፍራንኮ ቫሉታ አማካኝነተ ከታክስ ነፃ ሆነው ገቡ ማለት ገበያውን አረጋጋ ማለት አይደለም ይላሉ።

የምርቶቹን ዋጋ በሚገባ ለማረጋጋት የአቅራቢውና የፈላጊው መጠን መመጣጠን መቻል አለበት ያሉት አቶ ኃይለመስቀል፤ ይህ ካልሆነ ግን በራሱ ጊዜ የገበያ ዋጋውን እንዲንር ያደርገዋል። በተጨማሪም በዓለም ላይ ያለው የገበያ ሁኔታ ዋጋ እንዲጨምር አድርጓል። መንግሥት በዋጋው ላይ ጣልቃ መግባት የሚችልበት አግባብ ካለ ምርቶቹ የሚገቡበትና የሚሸጡበት ዋጋ መታወቅ አለበት ብለዋል።

በምርቶቹ ዋጋ ንረት ላይ ዋና መፍትሔው ከውጭ የሚገቡ የምግብ ሸቀጦችን በአገር ውስጥ ማምረት መቻል ነው የሚሉት የምጣኔ ሀብት ባለሙያው፤ ዩክሬንና ሩሲያ ላይ ያለው መሬት ኢትዮጵያ ውስጥ አለ። እናም መካናይዝድ የሆነ የእርሻ ልማት መሥራት ያስፈልጋል። የተትረፈረፈ ምርትን ማምረት መቻል ዋናው የዋጋ ንረቱ መፍትሔ ነው። ይህ ሲሆን ዶላር በጥቁር ገበያ ገዝቶ ከውጭ የማስገባቱ ሁኔታ ይቀራል።

አገር ውስጥ ምርትን መተካት ከተቻለ የውጭ ምንዛሬ እንደ ችግር አይነሳም፤ የአገር ውስጥ ገበያን በሚገባ ማረጋጋት ያስችላል። ታዲያ ይህ እንዲሆንና ምርትን ለማምረት ወሳኙ የሰላምና ደህንነቱ የተረጋገጠ አገር መገንባት ያስፈልጋል። የሰላም ዕጦት ገበያው እንዳይረጋጋ ያደርገዋል ።

እንደ አገር የተረጋጋ ሰላም ወሳኝ ነው። የሰላም እጦት ለዋጋ መናር ትልቅ ተጽዕኖ ስለሚያሳድር የተረጋጋ ሰላም እንዲኖር በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ እየታየ ባለው ከፍተኛ የዋጋ ንረት ሳቢያ እንደ ስኳር፣ የምግብ ዘይት፣ ስንዴ፣ ፓስታና ማካሮኒና የመሳሰሉ መሠረታዊ ምርቶች ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ በነሐሴ ወር 2013 ዓ.ም. መፈቀዱ ይታወሳል።

ሞገስ ተስፋ

አዲስ ዘመን ሚያዚያ 25/2015 

NEWSSOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

Ethioreview news

A journalist

መተከል – ታጠቀው ጫካ የነበሩ “ዱር በቃን” ብለው ከነትጥቃቸው ገቡ
የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ለ7 ቀናት ተኩስ ለማቆም ተስማሙ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 20260
Load more
Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 20260
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 20260
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 20260
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedbusinesshotarchivetips
    © Copyright 2026, All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2
    • Home Demo news