Skip to content
VOE
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ሔማን በቀለ – ታይም መፅሄት የዓመቱ ምርጥ ያለው ህልመኛ ታዳጊ ሳይንቲስት

    September 4, 2024

    በዩክሬን በኩል ወደ አውሮፓ የሚደርሰው የሩሲያ የተፈጥሮ ጋዝ  ስራው እንዲቆም ተደረገ

    January 1, 2025

    በኦሮሚያ ክልል ማን፣ ምን ፈጸመ? የኢሰመኮ ሪፖርት

    August 5, 2025

    በኦሮሚያ በሌብነት ጉዳይ አናቱ ተፈርቷል፤ በ289 ሺህ ካሬ.ሜ.መሬት ላይ ማጣራት ተጀምሯል

    December 3, 2022

    የአፋር ክልል ከ፴ ዓመታት በሁዋላ በትግራይ ክልል የተወሰደበትን ኣንድ ቀበሌ “ነጻ አ ወጣሁ” አለ

    June 7, 2021
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የኢትዮጵያ መከላከያ የላቀ ደረጃ መድረሱን ያሳየ ግዙፍ ሰራዊት ተመረቀ ” ተወደደም ተጠላ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ተጽዕኖ ፈጣሪ አገር ናት”
News

የኢትዮጵያ መከላከያ የላቀ ደረጃ መድረሱን ያሳየ ግዙፍ ሰራዊት ተመረቀ ” ተወደደም ተጠላ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ተጽዕኖ ፈጣሪ አገር ናት”

Ethioreview newsEthioreview news—August 14, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

“እንባዬ ፈሰሰ” ይላሉ የስቶኮልም ነዋሪው የቀድሞ ሰራዊት አባል። ፓራኮማንዶ ሆነው ምስራቅ የዘመቱት አዛውንት ” የባህር ህይላችንን ነጩን ልብስ ስመለከተ በደስታ ሰክሬ ነበር፣ ዛሬ ቀይ ለባሾቹን ስመለከት እንባዬን መቆጣጠር አቃተኝ” ሲሉ ደስታቸውን አጋሩ። ይህ የሆነው “ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች” የሚለውን ዜና በተመለከቱበት ቅጽበት ለወዳጃቸው ነው። “ይህ ሃይል ኢትዮጵያን የባህር በር ባለቤት ያደርጋል” ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግር ያደመጡ አስታውቀዋል።

የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል  ያሠለጠናቸውን የመሠረታዊ ኮማንዶ አባላት የምርቃት መርሃ-ግብር ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ፣ ሰራዊቱን “ቀይ መለዮ ማለት ጠላቱን የሚያርበደብድ ወገኑን የሚያኮራ ነው” ሲሉ ገልጸውታል። ኢትዮጵያ አሁን ላይ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንደምትዋጋ አስታውቀው ይህ ሃይል ውጊያ ጨረሽ እንደሆነም አመክተዋል። የሰላም ሃይል መሆኑንንም ገልጸዋል።

አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በሁዋላ በሻእቢያና ወያኔ ትብብር የፈረሱትን የኢትዮጵያ አየር ሃይል፣ ባህር ሃይል፣ ካዴት ማሰልጠኛ ተቋም፣ የፓራ ኮማንዶና የልዩ ኢንተለጀንስ ማስለልጠኛ ተቋማትን መልሶ በመገንባት ኢትዮጵያ አይታው የማታውቀውን የመከላከያ ሃይል እንዲገነባ አድርገዋል። እጅግ ዘመናዊ በተባለ ደረጃ እየተዋቀረ ያለው የኢትዮጵያ መከላከያ አዳዲስ ምሁር መኮንኖችን እያፈራ ሲሆን፣ በውጭ አገርና በአገር ውስጥ በሁለተኛ ዲግሪ ደረጃ ትምህርት የቀሰሙ ተተኪ ጀነራሎችንም እያዘጋጀች መሆኑ እየተገለጸ ነው። እነዚህ ከብሄርና ከዘር እሳቤ ርቀው እየተዘጋጁ ያሉ ምሁር የጦር መኮንኖች ከነባሮቹ ልምድ በመቅሰም ላይ እንደሆኑም ታውቋል።

ኢትዮጵያ እየገነባች ያለው ሰራዊት ስፋትና ዘመናዊ መሆን ቀደም ሲል የኢትዮጵያን መከላከያ “የደርግ ” ብለው ፈርጀው ላፈረሱ ሴረኞች ስጋት እየሆነባቸውና በውስጥ ጉዳይ ገብተው እየፈተፈቱ ባለበት ወቅት ይህ ግዙፍ ሃይል መመረቁ ሌላ ስጋት እንደሚሆንባቸው ተገልጿል። አብይ አህመድ ለነዚህ ወገኖችም ሆነ ለሌሎች ” ቁርጣችሁን እወቁ” ዓይነት መልዕክት አስተላልፈዋል። ኢትዮጵያ ታላቅ አገር በመሆኗ በሚመጥናት ደረጃ መከላከያዋን እየገነባች እንደሆነ አመልክተዋል። ” አገራችን ተወደደም ተጠላም በአፍሪካ ተጽእኖ ፈጣሪ፣ ታላቅ አገር ናት” በማለት ይህን ደረጃዋን አምነው መቀበልና በደረጃቸው ማሰብ ለሚገባቸው ምክር ቢጤ ሰጥተዋል። በርካታ ኢትዮጵያዊያን ዜናውን በአድናቆት እንዳዩትም ለመረዳት ተችሏል።

More stories

ከትግራይ ከሻዕቢያ ጋር የሚዶልቱ ፣ መከላከያን የሚጋብዙ ድምጾች ይሰማሉ፤ መንግስት ዝም ብሏል

January 5, 2025

ትህነግ “የብልጽግና መንገድ እንጀምር” አለ፤ ለትግራይ ህጻናት ዕልቂት ተጠያቂው ማን ነው?

September 11, 2022

ደራርቱ የፖለቲካ መሪዎችን በእንባ ተማጸነች

March 23, 2022

6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ነጻና ፍትሃዊ ለማድረግ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ ሁኔታ እየተሰራ ነው፡-ምርጫ ቦርድ

May 10, 2021

ኢትዮጵያ እየገነባችው ያለው ሃይል ለሰላም አለኝታ እንደሆነ ያመለከቱት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ፣ በየብስ፣ በባህር፣ በአየርና በሳይበር ለሚሰነዘር ማናቸውም ጥቃት አስፈላጊውን ምላሽ መስጠት የሚችል ሁሉ አቀፍ ሰራዊት መግንባቱን፣ ወደፊትም የማዘመኑ ስራ በዚሁ እንደሚቀጥል አመልክተዋ። ይህን የሰሙ ምሁራን ” ኢትዮጵያ በዚህ አቅሟ የወደብ ባለቤት የምትሆንበት ቀን ለሌሎች ስጋት ቢሆንም ሩቅ አይደለም” ሲሉ ምልክት ማየታቸውን አስታውቀዋል። አብይ አሕመድ ” እኛ የምናደርገው የሚገባቸው ጠላቶቻችን ናችው” ሲሉ የገለጹትን በማስታወስ ኢትዮጵያ እንዳትረጋ የሚደረግበትና በብሄር ተቧድና እንድትጫረስ የሚረጨው ቅስቀሳ የዚሁ አካል እንደሆነም አመክተዋል።

“እኛ የመከላከያ ሠራዊት አመራሮች እየሠራን ያለነው ሥራ ፕሮፌሽናል ሠራዊት መገንባት ነወ፤ አሁን ላይ ከሁሉም ኢትዮጵያዊያን የተወጣጣ ህብረ ብሄራዊ ሠራዊት እየገነባን ነው፤ ብቃት ያለው ዘመኑ ያፈራውን ቴክኖሎጂ መጠቀም የሚችል ሠራዊት እያበቃን እንገኛለን፤ የዛሬ ተመራቂ ኮማንዶዎች እና አየር ወለዶች የዘመናዊነታችን ማሣያዎች ናቸው፤    ኮማንዶዎች እና አየር ወለዶች የምድር ድሮዎኖች ብቻ ሳይሆኑ በእሳት ተፈትነው ያለፉ የቁርጥ ቀን ልጆች ናቸው፤ ቀይ መለዮ ማለት ጠላቱን የሚያርበደብድ ወገኑን የሚያኮራ ነው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አመልክተዋል።

“ከፊት ለፊታችን የኢትዮጵያችን ሰንደቅ-ዓላማ፣ ከኃላችን መላው ሀገር ወዳድ ዜጋ” የሚል መርህ ያለው የኢትዮጵያ አገር መከላከያ ሰራዊት በራሱ ወገኖች፣ ፈርሶ በየጎዳናው እንዲለምን ተደርጓል። በክህደት በተኛበት ታርዷል። በዚህ ሁሉ ውስጥ አልፎ ራሱን ያጸናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የኢትዮጵያን ባንድራ ላብሶ ቃል ኪዳኑንን እንደማይበላ ምሎ ምረቃውን አተናቋል።

“እኛ ተራ ጀብደኞች አይደለንም።ስሜት በድንገቴ ዛቻ አቅል አሳጥቶ የሚነዳን ልጓም አልባነት ፈጽሞ አይዳዳንም። እኛ በሸንጋይ ሙገሳና ውዳሴ ስለተንቆለጳጰስን ደማችን የሚሞቅ፣በነገር ሽንቆጣ ስንብጠለጠል የምንቀዘቅዝ ደመ-ነፍሳዊነትም አይነካካንም። ምክንያቱም እኛዊ ማንነታችን ነፋስ በበረታ ቁጥር የሚወዛወዝ መርገጫ አልባ ሳይሆን መርህን ተመርኩዞ፣በነጠረ ግብ የቆነጀ፣የመዳረሻን ፍኖት ጠንቅቆ በተረዳ አስተዋይነት የተዋበ ስለሆነ። እኛነታችን ሲገለጥ በሞያዊ ዕውቀት የቀለመ፣ በታላቅ የሃላፊነት መንፈስ ያማረ፣በኢትዮጵያዊ ሞራልና ስነ-ምግባር ያጌጠ ማራኪ ህብረ ቀለም ጎልቶ ያንጸባርቃል” ሲሉ ከምረቃው በሁዋላ የሰራዊቱ አባላት ተቀኝተውለታል።

በምረቃው ወቅት አባትና ልጅ በብላቴ መገኘታቸውን “ግጥምጥም” ሲል ኢፒድ የሚከተለውን ዘግቧል።

ሻለቃ ካሳ አበራ ይባላሉ። በደቡብ ዕዝ የመከላከያ ሰራዊት አባል ሆነው አገራቸውን በማገልገል ላይ ይገኛሉ። በ1990 ዓ.ም የሀገር መከላከያን የተቀላቀሉት ሻለቃ ካሳ፤ በሰራዊቱ ውስጥ ሆነው አገራቸውን ለ26 ዓመታት አገልግለዋል።

የኢፕድ ዘጋቢዎች ትናንት ያገኟቸው የኮማንዶና የአየር ወለድ ዕዝ በብላቴ ኮማንዶና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከል ያሰለጠናቸውን 41ኛ ዙር ዞብል ኮርስ  መሰረታዊ  ኮማንዶዎችን፥ አየር ወለድና ልዩ ሀይል ፀረ ሽብር አባላት ምረቃ ላይ የልጃቸውን ምረቃ ሲታደሙ ነበር።

“ከአመታት በፊት የሁለት ዓመት ህጻን ልጅ ነበረኝ። ከልጄ ጋር እየኖርን ሳለን ለግዳጅ ተነስ ተባልኩ። ልጄ ከአገሬ አልበለጠብኝምና እናቴን እንድታሳድግልኝ ሰጥቼያት ለግዳጅ ወጣሁ”  የሚሉት ሻለቃ ካሳ፥ ልጃቸው የመከላከያ ሰራዊት አባል መሆኑን የሰሙትም ለግዳጅ ሶማሊያ በደለዊ እያሉ መሆኑን ይናገራሉ።

“ልጄ የእኔን የአባቱን አርአያ ተከትሎ ወታደር መሆኑ አስደስቶኛል” ሲሉም ነው ትናንት በብላቴ ለተገኙት የኢፕድ ዘጋቢዎች የተናገሩት።

ሁሌም እናቴ ለልጄ የምትመክረው  ምክር ነበራት። እሱም ምን አልባት  ጓደኞችህ በየቦታው ደክመው የሚቀሩ ከሆነ  ጽናትን፥ ጥንካሬንና አገር ወዳድነትህን ከአባትህ ውረስ የሚለው ነው። ይህ ምክር ብርታት ሆኖት ዛሬ ልጄ ወታደር ሆኗል” ይላሉ ሻለቃ ካሳ።

“አሁን ደግሞ የምድር ድሮኖች በሚል የሚታወቀው የኮማንዶ አባል ሆኖ ብዙ ፈተናዎች አልፎ በመመረቁ የተሰማኝ ደስታ ወደር የለውም” ብለውናል።

ልጅ የአባቱን ሙያ ሲወርስ ደስ ይላል የሚሉት ሻለቃ ካሳ፤ “ውትድርና የቤተሰባችን ውርስ ሆኗል ።ታላቅ ወንድሜ የቀድሞ ሠራዊት አባል ነበር። እኔም ወታደር ነኝ፣ ልጄም ወታደር ሆኗል።ይህ ውርስ የመጣውም ለአገራችን ባለን ፍቅር የሚመነጭ ነው” ሲሉም ስሜታቸውን ገልጸውልናል።

ውትድርና አድካሚ ነው፤ ለአገር መስዋዕትነት ያስከፍላል።እሱና ጓዶቹ  ይህን ተገንዘበው ለአገራቸውን ለማገልገል ዝግጁ መሆን ይኖርባቸዋል ነው ያሉት፤ ሻለቃ ካሳ።

“የአባቴንና የአጎቴን የወታደርነት ሙያ በመቀላቀሌ ደስተኛ ነኝ” የሚለው መሰረታዊ ወታደር እዮብ ካሳ ነው።

ውትድርና ትልቅ ሙያ ነው። አገር መጠበቂያ፣ የህዝብ ሰላምና ደህንነት መጠበቂያም መተዳደሪያም የሆነ ታላቅ ሙያ ነው ሲልም ነው ሃሰቡን ያጋራን።

“የኮማንዶን ውስብስብ ስልጠና አልፌና ወጣ ውረዱን ተሻግሬ ቀይ መለዮ በወታደሩ አባቴ ፌት በመልበሴ እጅግ ደስ ብሎኛል” የሚለው መሰረታዊ ወታደር እዮብ፣ አገሬና ህዝቤ የሚሰጡኝን ግዳጅ በብቃት ለመወጣት ዝግጁ ነኝ ብሏል።


👉

  

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን አጋላጭ ምክንያቶች
የኢሰመኮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ይነሳ “ምክረ አሳብ” ለፓርላማ አባላት ከውሳኔ በፊት ታደላቸው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2