ትግራይ ውስጥ ተቀስቅሶ ወደ ሌሎች ክልሎች በተስፋፋው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት “በሺዎች የሚቆጠሩ” የኢትዮጵያ ልጆች ሞተዋል። በመልሶ ማጥቃሩ በተለይ የትግራይ ተዋጊዎች ላይ ክፉኛ ሰብአዊ ጉዳት መድረሱ በየአቅጣጫው ሲገለጽ ቆይቷል። ከሰላም ስምምነቱ በሁዋላ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ቢልም ይህ ከመሆኑ በፊት ሶስት ልጆቻቸውን ያጡ እናት በአሰቃቂ ሁኔታ ራሳቸውን ማጥፋታቸውን ዘጽዓት በሚል ስያሜ የሚታወቀው የትህነግ ደጋፊ በትግርኛ ጽፏል።
ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ከባድ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸውና ዘላቂ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸዉ የክልሉ ባለስልጣናት ማስታወቃቸውን ጠቅሶ የመርዶ አዋጅ እንደሚካሄድ የዘገበው ዶቼ ቨለ ሬድዮ ሬዲዮ ነው።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር እንዳስታወቀዉ በጦርነቱ ለሞቱ የቀድሞ የትግራይ ሐይሎች አባላት፣ ቤተሰቦቻቸው በቅርቡ በይፋ መርዶ ይነገራቸዋል።
በመቐለ ከተማ የትግራይ የጦር ጉዳተኞች ማእከል ስራ ባስጀመሩበት ወቅት ንግግር ያደረጉ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ፣ ቁጥሩን በትክክል ባይጠቅሱም “በሺዎች የሚቆጠሩ” ያልዋቸው የቀድሞ የትግራይ ሐይሎች አባላት በሁለት ዓመቱ ጦርነት መሞታቸውን አረጋግጠዋል። የሟች ቤተሰቦችን ከማርዳት በተጨማሪ መስተዳድራቸዉ ድጋፍ እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።
ዘፀዓት በትግርኛ ፅፎት ሌሎች ኢትዮጵያውን እንዲያውቁት የትግርኛውን ጽሁፍ በማያያዝ ወደ አማርኛ በመለሰ ጽሁፍ በርካቶችን ያሳዘነ መረጃ ይፋ ሆኗል። “ሶስት ልጆቼን ካጣሁ እኔ ምን አለኝ” በሚል ነው እኚህ እናት ራሳቸውን በገመድ ያጠፉት። ሙሉውን ትርጉም ያንብቡ
ከሶስት ቀናት በፊት የሶስት ልጆችዋ መርዶ የተነገራት እናት ከደቂቃዎች በኋላ እኔስ ምን አለኝ በማለት ራስዋ በገመድ አጥፍታለች። የስነ ስርአት ቀብርዋ በስንቃጣ አብነቃ የሚባል ቦታ እንደተፈፀመ አረጋግጫለሁ ። ይህቺ እናት የራስዋ እንደባይቃ በድንጋጤ ሓዘን በርትቶ ራስዋ አጥፍታለች ልብ የሚሰብር ነው።
ይህ በስነስርዓት ተነግሮ የሁሉም ብሔራዊ ሓዘን ታውጆ አጥኒ ኮሚቴ ተደርጎ ካልተነገረ የህዝብ ሓዘን ከባድ ይሆናል ። መፅናናትን ለመላው የተሰው ቤተሰቦች
ህይወቱ እንደ እቃ የተጫወቱበት የቀለዱበት የትግራይ ወጣቶች መስዋዕትነት ህዝብ መበደል አልነበረባቸውም ። መስዋዕትነት እንዲህ ርካሽ ማድረግ አልነበረባቸውም ። ቢያንስ በስነስርዓት መናገር ነበረባቸው መድከም አልነበረባቸውም ። መርዶ ለመንገር ገንዘብ መክፈል አልነበረባቸውም ፤ በእውነት ነውር ነው ።
ይህ ታሪክ ልብ ይነካል። ጦርነት ክፉ ነው። ባህላዊ ጨዋታችን ነው ያሉት እነ አሉላ ሰለሞን በውጪ አለም እየተምነሸነሹ ነው። የፃድቃን ልጆች ውጪ ናቸው። አብዛኛው ወያኔ ዘመድ አዝማዱ ውጪ ነው። በጦርነት ሟቹ ግን የደሃ ልጅ ነው። አሁንም የጦርነት አዙሪት ላይ ነን። ያሳዝናል
ይህ አሳዛኝ መረጃ ዛሬ ላይ ለሁሉም ወገን የሚያስተምር ነው። ውጭ አገር ተቀምጠው የደሃ ልጅ የሚማግዱ “በቃችሁ” ሊባሉ ይገባል። እስከመቼ ነው በንጹሃን ደምና ሞት የሚነገደው? የትግራይ ሃዘንና ገጠመኝ ለሌሎች ሁሉ ትምህርት ሊሆን ሲገባ ወደ ሌላ ኪሳራና ሞት መሸጋገር ነገ የሌሎች እናቶች በተመሳሳይ ራሳቸውን ሲያጠፉ፣ በሃዘን ሲቆራመዱ፣ ረጂና ጧሪ አጥተው አመድ ስር ሲንደፋደፉ ከማየት የዘለለ ውጤት አይስገኝም።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም።… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች







