Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ታላቁ ህዳሴ ግድብ በመገባደጃ ምዕራፍ ላይ

    April 1, 2023

    የአሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችል ስራ መጀመሩን ይፋ አደረገ

    August 22, 2024

    ዶናልድ ትራምፕ በቁጥጥር ሥር ውለው በቀረበባቸው ሰላሳ አራት ክሶች ጥፋተኛ አይደለሁም አሉ

    April 6, 2023

    የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰነድ የሌላቸው የኤርትራዊ ስደተኞች መታሰራቸውን ኮነን፤ “ያለ ህጋዊ ማስረጃ የትኛው አገር መኖር ይቻላል?”

    June 4, 2023

    ቻይናዊው የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ከ9 ግብረ አበሮቻቸው ጋር የውጭ አገር ብሮች በማተምና በጥቁር ገበያ ወንጀል ታስረው ፍ/ቤት ቀረቡ

    September 5, 2023
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  law  መሰየም በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ
law

መሰየም በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ

Ethioreview newsEthioreview news—June 25, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አንድ የወንጀል ቅጣት በተለያዩ ሁኔታዎች (በምሕረት ወይም ይቅርታ) የተነሳ ቀሪ ሊሆን ይችላል፡፡ የሰዎች የቀደመ የወንጀል ታሪክ በቀጣይ ህይወታቸው ወይም ኑሯቸው ላይ የሚያስከትለው አሉታዊ ተጽዕኖ ቀላል የሚባል አይደለም፡፡ በመሆኑም ቀድሞ በወንጀል ተቀጥቶ ቅጣቱን የጨረሰ ማንኛውም ሰው ታሪኩ የሚፋቅለት በወንጀል ሕጉ እና በወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ በተቀመጡት ድንጋጌዎች መሰረት አቤቱታውን አቅርቦ የወንጀል ቅጣቱን ጥሎበት በነበረው ፍርድ ቤት ሲሰየም ነው፡፡ መሰየም በወንጀል ሕጋችን የተካተተ ፅንሰ ሀሳብ ቢሆንም ቃሉ፣ በሕጉ ያለው ትርጓሜም ሆነ ዝርዝር ሁኔታው በማህበረሰባችን እምብዛም የተለመደ አይደለም፡፡ በዚህ የግንዛቤ ክፍትት ምክንያት በስፋት ሲጠቀምበት አይስተዋልም፡፡ ስለሆነም በዚህ አጭር ጽሁፍ ለማህበረሰቡ መሰየምን አስመልክቶ ግንዛቤ ማስጨበጥን ዓላማ አድርጎ የተዘጋጀ ሲሆን የመሰየም ምንነት፣ ውጤቱን እና የሚፈፀምበትን ዝርዝር ሁኔታ እንዲሁም የመሰየም ውሳኔ መሻር የምንመለከት ይሆናል፡፡

የመሰየም ምንነት

መሰየም የሚለው ቃል ቀጥተኛ ትርጉም ስም መስጠት ወይም ስም ማውጣት መሆኑን በተለያዩ መዝገበ ቃላት እናገኘዋለን፡፡ ይህ ግን ሕጉ ማለት የፈለገውን በቀላሉ ለመረዳት የሚያስችል ላይሆን ይችላል፡፡ ከዚህ ይልቅ የወንጀል ሕጉ በእንግሊዝኛ ቅጂው የተጠቀመው “Reinstatement” የሚለው ቃል የተሻለ አመላካች ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ብላክስ ሎው መዝገበ ቃላት (Black’s law dictionary) በ8ኛ እትም “Reinstatement” የሚለውን ቃል “To place again in a former state, condition, or office; to restore to a state or position from which the object or person had been removed.” በሚል ትርጓሜ ሰጥቶታል፡፡ ይህን ትርጓሜ ወደ አማርኛ ስንመልሰው በአጭሩ አንድን ነገር ወይም ሰው ቀድሞ ወደነበረበት ሁኔታ መመለስ ማለት ነው፡፡ ከዚህ በመነሳትም ህጉ በዚህ ክፍል የሚገልፀው ቀድሞ ወደ ነበረበት ሁኔታ ስለመመለስ መሆኑን ጠቋሚ ነው፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 232(1) መሰየም የተወሰነበትን ቅጣት የፈፀመ ወይም ቅጣቱ በይርጋ ወይም በይቅርታ የቀረለት ወይም ፍርዱ ወይም የቅጣቱ አፈፃፀም ያታገደለት ወይም በአመክሮ የተለቀቀ ማንኛውም ጥፋተኛ በሕጉ የተቀመጡትን ግዴታዎች በመፈፀም ከመቀጣቱ በፊት የነበረውን ንፁህ ስም እንዲመለስለትና ፍርድ እንዲሰረዝለት የሚጠይቅበት ሂደት ስለመሆኑ ይገልፃል፡፡ መሰየም የሚገኘው በመልካም ሥራ ነው ፡፡ እንደ መብት በይገባኛል የሚጠየቅ አይደለም፡፡ መሰየም በቀድሞው ጥፋተኛ (ፍርደኛ) በግሉ ወይም እንደነገሩ ሁኔታ በሕጋዊ ወኪሉ ወይም በቅርብ ዘመዱ ጠያቂነት የሚቀርብና በፍ/ቤት መወሰን ያለበት ጉዳይ ነው፡፡

More stories

ሿሿ – ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 25 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

May 20, 2023

አሸባሪ ቡድኑ በአማራና በአፋር የፈጸማቸውን ወንጀሎች የሚያጣራ ግብረ ኃይል ሥራውን ጀመረ

December 27, 2021

በአደገኛ ዕፅ ዝውውር ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ ግለሰቦች ከ2 ዓመት እስከ 12 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ

October 24, 2024

የሃጫሉ ገዳዮች የተባሉት ” ጥፋተኛ” ተባሉ

July 5, 2021

ለመሰየም የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች

መሰየም በዘፈቀደ የሚከናወን ሳይሆን ቅድመ ሁኔታዎች ያሉት ስለመሆኑ በአንቀጽ 233 ተደንግጓል፡፡ አንድ ፍርደኛ መሰየም የሚችለው፡-

ሀ. የተወሰነበትን ቅጣት የፈጸመ ወይም ቅጣቱ በይርጋ ወይም በይቅርታ የቀረለት ወይም ፍርዱ ወይም የቅጣቱ አፈፃፀም የታገደለት ወይም በአመክሮ የተለቀቀ ሰው ሊሆን ይገባል፣

ለ. የተወሰነበት ቅጣት ፅኑ እስራት፣ እስከመጨረሻው ከሀገር መውጣት ወይም የንብረት መወረስ ከሆነ ቅጣቱ ከተፈፀመ ወይም በይርጋ ከታገደበት ቀን አንስቶ፣ ቅጣቱ በይቅርታ ምክንያት ተሽሮ ከሆነ ተቀጪው ከተለቀቀበት ቀን ጀምሮ፣ ተቀጪው ቅጣቱ ታግዶለት ወይም በአመክሮ ተፈትቶ የፈተናውን ጊዜ በሰላም ጨርሶ ከሆነ ቅጣቱ ከታገደበት ወይም በአመክሮ ከተፈታ ቀን ጀምሮ ቢያንስ አምስት ዓመት ያለፈ እንደሆነ በሌላው ሁኔታ ግን ቢያንስ ሁለት አመት የሆነ መሆን፣

ሐ. በተጠቀሰው የአምስት ወይም የሁለት አመት ጊዜ ውስጥ በመልካም ጠባይ የተመራ መሆንና በማናቸውም በእስራት የሚያስቀጣ ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ አለመገኘት፣

መ. የተወሰነበት ተጨማሪ ቅጣት ካለ ይህ ቅጣት ፈፅሞ መገኘት፣

ሠ. የተለቀቀው ተቀጪ የራሱ ችሎታና የጊዜው ሁኔታ በሚፈቅድለት መጠንና እራሱ ሊፈፅመው ይገባዋል ተብሎ በሚገመትበት ሁኔታ በፍርድ የተወሰነበትን ካሳ፣ የዳኝነት ማንኛውንም አይነት ኪሳራ በሚገባ አጠናቆ ከፍሎ መገኛት ይጠበቅበታል፡፡

በፊደል (ሀ) ላይ ከተመለከተው ጊዜ ጋር በተያዘ ቅጣቱ የታገደው በይርጋ ከሆነ ግለሰቡ ቅጣቱን ፈፅሞ ቢሆን ኖሮ ቅጣቱ ያበቃ ከነበረበት ጊዜ ከማለፉ በፊት ሊሰየም እንደማይችል ከአንቀፅ 234 (1) ንባብ መረዳት የሚቻል ነው፡፡ ይህን በምሳሌ ለማስረዳት ያህል በአንቀፅ 224(1)(ለ) ሥር ከአስር ዓመት በላይ ለሆነ የነፃነት የሚያሳጣ ቅጣት የይርጋ ጊዜ ሀያ አመት ነው፡፡ አንድ ጥፋተኛ የተባለ ሰው የተፈረደበት ሀያ አምስት አመት ቢሆን የይርጋ ጊዜው በአንቀፅ 225 መሰረት ፍርዱ የመጨረሻ ሆኖ ተፈፃሚ መሆን ከሚችልበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር በመሆኑ ቅጣቱ ተፈፅሞ ቢሆን ኖሮ ከይርጋ በፊት አይጠናቀቅም፡፡ በዚህ ጊዜ ቅጣቱ በይርጋ የሚታገድ ቢሆን እንኳን ቅጣት ቢፈፀም ሊጠናቀቅ ከሚችልበት ቀን በፊት ፍርደኛው ሊሰየም አይችልም፡፡

በተጨማሪ መሰየም ለአካለመጠን ያልደረሰ ልጅ ላይ በሚወሰኑ የጥንቃቄ እርምጃዎች ላይ ተፈፃሚ የሚሆን ነው፡፡ እንደሚታወቀው በወንጀል ህጉ አካለመጠን ያልደረሰ ልጅ የሚባለው ዘጠኝ እና በአስራ አምስት አመት መካከል ያለ ልጅን የሚወክል ነው፡፡ በዚህ እድሜ ክልል የሚገኙ ልጆች ለአካለመጠን ያልደረሱ በመሆናቸው የሚወሰንባቸው የእርምት እርምጃ በአዋቂ አጥፊዎች ላይ ከሚወሰነው ቅጣት የሚለይ ስለመሆኑ አንቀፅ 157 እና ተከታዮቹ ተመልክተዋ ይገኛሉ፡፡

አካለመጠን ባልደረሰ ልጅ ላይ የሚወሰኑ የእርምት እርምጃዎች ወደ ህክምና ተቋም መላክ፣ ቁጥጥር በማድረግ ትምህርት እንዲሰጠው ማድረግ፣ ተግሳፅና ወቀሳ፣ በትምህርት ቤት ወይም በመኖሪያ ቤት ተወስኖ እንዲቆይ ማድረግ፣ ወደ ጠባይ ማረሚያ ተቋም መላክ፣ አለፍ ሲልም ወንጀሉ ከባድ ሲሆን እስራትም የሚጨምር ነው፡፡ ከእስራት ቅጣቱ በስተቀር የሚወሰኑ የጥንቃቄ እርምጃዎችና ሌሎች ቅጣቶች ቅጣት በተፈፀመ በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ ለማሰየም የሚያስችሉ ሁኔታዎች ሲሟሉ ሊሰየም እንደሚችል በአንቀፅ 175 ሥር ተደንግጓል፡፡ አካለመጠን ያልደረሰው ልጅ የሚሰየመው እራሱ ወይም በእርሱ ላይ በሕግ ስልጣን ያላቸው ሰዎች ሲጠይቁ ይሆናል፡፡

በሌላ በኩል ስሙ እንዲታደስለት የሚጠይቀው ተቀጪ በህዝባዊ፣ በወታደራዊ ወይም በማህበራዊ አገልግሎት መስክ የሚያስመሰግን ልዩ አስተዋፅኦ ያበረከተ እንደሆነ ለመሰየም የተወሰነው ጊዜ ከማለፉ በፊት መሰየም ሊፈቀድት እንደሚችል በአንቀፅ 234 (2) ተደንግጓል፡፡ ይህ የተለየ ማህራዊ፣ ህዝባዊ ወይም ወታራዊ አበርክቶ በሕጉ የተብራራ ባለመሆኑ እንደየ ሁኔታው በፍርድ ቤት የሚመዘን ይሆናል ማለት ነው፡፡

ፍርደኛው ለመሰየም የሚያቀርበው ጥያቄ ከላይ የተቀመጡትን ቅድመ ሁኔታዎች ያላሟላ ከሆን ወይም ፍርድ ቤቱ ለመሰየም የቀረበው ጥያቄ በቂ አይደለም ብሎ ካመነ የመሰየም ጥያቄውን አለመቀበል ይችላል፡፡ ይህ በሆነ ጊዜም መሰየም የጠየቀው ፍርደኛ በድጋሚ መሰየም ጥያቄ ማቅረብ የሚችል ቢሆንም ሁለት አመት እሲኪያልፍ መጠበቅ አለበት (አንቀጽ 236) ፡፡

የመሰየም ውጤት

አንድ ተቀጪ የመሰየም ጥያቄ አቅርቦ ጥያቄውን ፍርድ ቤቱ ከተቀበለው እና ከሰየመው መሰየሙ የሚያስከትላቸው ውጤቶች በወንጀል ህግ አንቀጽ 235 ንዑስ አንቀጽ ከ1-3 ተመልክተዋል፡፡ እነርሱም፡-

 ተቀጪው ከተሰየመበት ጊዜ ጀምሮ ተወስኖበት ከነበረው ከመብት፣ ከማዕረግ ወይም የችሎታ ማጣቱ ቀርቶለት ህዝባዊ መብቱንና ቤተሰብ ማስተዳደርና የሙያ ሥራ የመሥራት መብቱን እንደገና ለመያዝ ችሎታ ይኖረዋል፣

እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ሙያዊ ሥራውን የመስራት መብቱን እንደገና ለመያዝ ችሎታ ያገኛል ሲባል ፍርደኛው ተቀጥሮ የሚሰራ ከሆነ የቀድሞ ቀጣሪው ጋር እንደመብት ይመለሳል ማለት ሳይሆን የተወሰነበት ፍርድ በሙያው የመስራትን መብት ነፍጎት ከሆነ ቀድሞ በነበረው ሙያ የመስራት መብት ያገኛል ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ የጥብቅና ፈቃድ ለማግኘት ከወንጀል ጥፋኝነት ነፃ መሆን የሚጠይቅ እንደመሆኑ የወንጀል ሪከርዱ እስካለ ድረስ ፈቃዱን ሊያገኝ አይችልም፡፡ ከተሰየመ ግን ይህ የቀድሞ ጥፋኝት ሪከርድ ቀሪ ስለሚሆን የጥብቅና ፈቃዱን የማግኘት መብት ይሰጠዋል፡፡

 የቅጣቱ ፍርድ ከወንጀለኞች መዝገብ ላይ ይፋቅለታል፣ ለወደፊትም እንዳልተፈረደበት ይቆጠራል፣

በመሰየም የተሠረዘውን ቅጣት አንስቶ ተቀጪውን መውቀስ ወቃሹን በስም ማጥፋት ወንጀል ያስቀጣል፣ ለሕዝብ ጥቅም የተደረገ ነው ብሎ መከላከልም አይቻልም፡፡ ይህ ማለት ፍርደኛው ሌላ ወንጀል ፈፅሞ ቢገኝ እንኳን ዐቃቤ ሕግ ግለሰቡ አስቀድሞ የተሰየመበትን ፍርድ በሪከርድነት ሊያቀርብበት አይችልም ማለት ነው፡፡

የመሰየም ውሳኔ መሻር

አንድ ፍርደኛ ከተሰየመ በኋላ በኋላ የሚያሳየው ባህሪ መሰየሙ እንዲሰረዝበት የሚያደርግ ሊሆን ይችላል፡፡ ይኸውም እንዲሰየም ከተፈቀደለት በኋላ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ በሞት ወይም በፅኑ እስራት እንዲቀጣ የመጨረሻ ፍርድ ከተሰጠበት አስቀድሞ እንዲሰየም የተሰጠው ውሳኔ ይሰረዛል፣ በድጋሚም እንዲሰየም አይፈቀድለትም (አንቀጽ 237)፡፡ ፅኑ እስራት የሚወሰነው ከባድ ወንጀል ባደረጉ እና ለህብረተሰቡ አደገኛ በሆኑ ወንጀለኞች ላይ ሲሆን ይህም ከአንድ ዓመት እስከ ሀያ አምስት ዓመት የሚደርስ እንደሆነ በወንጀል ሕጉ አንቀፅ 108 ላይ ተደንጎ ይገኛል፡፡

በአጠቃላይ መሰየም በሕጉ የተሰጠው ትርጓሜ እና ለመሰየም የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች ከላይ የተመለከቱት ሲሆኑ በወንጀል ጥፋኝነት የተወሰነባቸው እና ከላይ በሕጉ መሰረት ለማሰየም የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን የሚያሟሉ ፍርደኞች በማሰየም የቀድሞ ጥፋተኝነት ሪከርድ በማሰረዝ መልካም ስማቸውን እንዲላበሱ ሊጠቀሙበት ይገባል፡፡

Via ministry of justice  በንቃተ ህግ፤ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት

law
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
OFC- The finals of Fanos armed forces should be punished
የአማራ ክልል የሰላም ኮንፍ አስር ነጥቦችን አስቀምጦ ተጠቃለለ፤ የሰላም ድርድር ዋናው ነው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
law

ህገወጥ የውጭ ምንዛሪ ወንጀል የፈጸሙ 123 ተጠርጣሪዎች የባንክ ሒሳብ ታገደ

September 20, 2025
law

እነ ቀሲስ በላይ በሙስና ወንጀል ሊፈርድባቸው እንደማይገባ ጠቅሰው ያቀረቡት ይግባኝ ውድቅ ሆነ

July 26, 2025
law

የአዲስ አበባ የከንቲባ ፅ.ቤት ፕሮቶኮልን ጨምሮ 12 ተከሳሾች በሌብነት ተከሰው ተፈረደባቸው

July 23, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2