የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በበኩሉ ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልጾ፣የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንም በዚያው በኩል እየተሳተፈች መሆኑን አብራርቷል፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የ2016 ዓ.ም የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መጠናቀቅን በማስመልከት ባወጣው መግለጫ በምክክር ኮሚሽኑ ላይ ቅሬታ እንዳለው አሳውቆ ነበር፡፡
ቅዱስ ሲኖዶሱ “የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት አዋጅ አኳያ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ ሁኔታ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክርና በውይይት ለመፍታት የተቋቋመ መሆኑን” ጉባኤው መረዳቱን ገልጾ ቤተክርስቲያኒቱ በኮሚሽኑ በኩል በይፋ የቀረበ የተሳትፎ ጥሪ እንዳልተደረገላት በመግለጽ በሂደቱ ቅር መሰኟቷንና ከዚህም በመነሳት “የቤተ ክርስቲያኒቱ ተሳትፎና አጀንዳ የማቅረብ መብቷ እንዲረጋገጥ ከኮሚሽኑ ጋር በመነጋገር ጉዳዩን ተከታትሎ ለፍጻሜ የሚያበቃ” ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ መሰየሙንም መግለጫው ያትታል፡፡
የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በበኩሉ ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልጾ፣የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንም በዚያው በኩል እየተሳተፈች መሆኑን አብራርቷል፡፡
ሆኖም ቅሬታዎችን ለማጥራትና አብሮም ለመስራት ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጋር ቅዱስ ሲኖዱሱ ጽ/ቤት ድረሰ በመገኘት ለመወያየት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጧል፡፡ ይህ የአካታችነት መርህ ከሁሉም የሃይማኖት ተቋማት ጋር በእኩልነት የሚተገበር መሆኑንም ጨምሮ ገልጧል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶሱ መግለጫ ሰጥቷል ሲሰጥ በምክክር ኮሚሽኑ ቅር መሰኘቱንም ሲያስታውቅ ምልዓተ ጉባኤው ለቤተ ክርስቲያኗ አንድነት፣ ለሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት፣ ለመንፈሳዊ ዕድገትና ለምእመናን ደኅንነት ትኩረት በመስጠት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፊያለሁ ብሏል፡፡
በዚሁ መሠረት ካነሳቸው ነጥቦች መካከል
- በቅድስት ቤተ ክርስቲያንና በሀገራችን መንግሥት መካከል ሊኖር ስለሚገባው መልካም የሥራ ግንኙነት በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሚመካከር የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ልዑክ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፤
- በመላው ሀገራችን በተፈጠሩ ግጭቶች፣ አለመግባባቶችና የሰላም ዕጦት በርካታ የሰው ሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት እንደቀጠለ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን በእጅጉ አሳዝኗል፡፡ ስለዚህ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከግጭትና ከጥፋት ድርጊት ተቆጥበው የተፈጠረውን አለመግባባትና ግጭት በውይይትና በምክክር እንዲፈቱ እና ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንኦት ጥሪውን አቅርቧል፤
- የሀገራዊ ምክክር ሀገረ መንግሥትን ከመመሥረት ጀምሮ በአስታራቂነትና በሰላም ግንባታ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ለሆነችው ቤተ ክርስቲያን እስከአሁን ድረስ በይፋ የቀረበ የተሳትፎ ጥሪ ሳይኖር ኮሚሽኑ የተሳታፊ ልየታንና አጀንዳ መረጣ አጠናቆ ወደ ምክክር ትግበራ እየገባ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን ቅር አሰኝቷል፡፡ በመሆኑም የቤተ ክርስቲያኒቱ ተሳትፎና አጀንዳ የማቅረብ መብቷ እንዲረጋገጥ ከኮሚሽኑ ጋር በመነጋገር ጉዳዩን ተከታትሎ ለፍጻሜ የሚያበቃ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡ ማለቱ አይዘነጋም።


