– የአቪዬሽን ዘርፍ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቅ በመሆኑ ደንበኞች ለበረራ ደህንነት ህጎችና ደንቦች ተገዢ ሊሆኑ ይገባል
– አውሮፕላኖች መንገደኞችን ስለጫኑ ብቻ በረራ አያደርጉም፣ ቅድሚያ ለደህንነት ይሰጣል፣
የአቪዬሽን ዘርፍ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቅ በመሆኑ ደንበኞች ለበረራ ደህንነት ለህጎች፣ መምሪያዎችና ደንቦች ተገዢ ሊሆኑ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ መንገደኞች የተጣለባቸው ኃላፊነትና ማግኘት የሚገባቸውን መብቶች አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።
በባለስልጣኑ የሴኪዩሪቲና ፋሲሊቴሽን ዳይሬክተር አቶ ደበበ ግርማ በመግለጫው እንዳሉት፤ የአቪዬሽን ዘርፍ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቅ በመሆኑ ተሳፋሪዎቸ ከበረራ ደህንነት አንጻር ለህግና ደንቦች ተገዢ ሊሆኑ ይገባል።
ለአቪዬሽን ደህንነት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በአውሮፕላን ውስጥ የሚፈጸሙ ህገወጥ ተግባራት በህግ አግባብ ይታያሉ ብለዋል።
ኢትዮጵያ የአለም አቀፉ የሲቪል አሺዬሽን ድርጅት መስራችና የሲቪል አሺዬሽን ስምምነት መፈረሟን አስታውሰዋል።
ህብረተሰቡ ስለአቪዬሽን ህጎች ግንዛቤ እንዲኖረው የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ተግባራዊ ማድረጉን ገልጸው አውሮፕላኖች መንገደኞችን ስለጫኑ ብቻ በረራ አያደርጉም ያሉት ዳይሪክተሩ ቅድሚያ ለደህንነት ይሰጣል ብለዋል።
ከመንገደኞቹ ሚነሱ ቅሬታዎችን ለማረም የአሰራር ስርዓቶችን እየተዘረጋ መሆኑን መሆኑን ገልጸው የአየር መንገዱን ገጽታ ለማበላሸት የተለያዩ ዘመቻዎች እየተካሄዱ መሆኑን አውስተው ኢትዮጵያዊያን ድርጊቱን መከላከል እንደሚገባቸው ተናግረዋል።
በአማን ረሺድ
ነሐሴ 23 ቀን 2016 ዓም (ኢ ፕ ድ)


