መገናኛ ብዙሀን ለሙዚቀኞች የሮያሊቲ ክፍያ እንዲከፍሉ የሚያስገደደው መመሪያ የፊታችን ሀምሌ 1 2017 ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
የሮያሊቲ ክፍያ ረቂቅ መመሪያው የሚመለከታቸው አካላትን ባሳተፈ መንገድ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን ህጉን ለማስፈጸም ስልጣን የተሰጠው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ቢበዛ ከአምስት ወር በኃላ ፀድቆ ወደ ስራ እንደሚገባ የባለስልጣኑ ዋና ዳሬክተር አቶ ወልዱ ይመሰል ተናግረዋል።
በኢትዮጲያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን አማካኝነት የተሰናደው ይህ ውይይት፣ሙዚቀኞች፣ ፕሮዲውሰሮች፣ደራሲያን እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈውበታል።
ውይይቱ በዋናነት በሙዚቀኞች ሮያሊቲ ክፍያ ዙሪያ ያተኮረ ሲሆን ይህንንም ተከትሎ ቀመር ተዘጋጅቷል።
የኢትዮጵያ የቅጅና ተዛማጅ መብቶች የጋራ አስተዳደር እና የኢትዮጵያ የሙዚቃ ቅጅና ተዛማጅ መብቶች የጋራ አስተዳደር በጋራ ያዘጋጁት ይህ የቀመር ሰነድ መገናኛ ብዙሀን ለሙዚቀኞች እንዴት መከፈል እንዳለባቸው ካስቀመጣቸው መስፈርቶች መካከል፣
፧-የመገናኛ ብዙሀኑን የገቢ ምንጭ የመለየት ስራዎን በመስራት
፣ -መገናኛ ብዙሀኑ በቀን ወይንም በ24 ሰዓት ምን ያህል ሙዚቃ እንዳጫወቱ በማጣራት
፥-EMCCMO.COM በተሰኘው ዌብ ሳይት በየመገናኛ ብዙሀኑ የሚተላለፍ
ሙዚቃዎችን በመቁጠር(count)በማድረግ
፧-መገናኛ ብዙሀኑ የስርጭት መጠንን በማጣራት እና የመሳሰሉት ዘዴዎችን በመጠቀም የሙዚቀኛው ስራ ምን ያህል አየር ላይ መዋሉ እና ሚዲያውም ምን ያህል መክፈል እንዳለበት ይሰላል ተብሏል።
ህይወታቸው ያለፍ ሙዚቀኞችን በሚመለት የሟች ወራሾች ገቢውን እንዲያገኙ የሚያደርገው ይህ መመሪያ ሌሎችንም ጉዳዮች አካቷል።
መመሪያው ተግባራዊ መሆን ሲጀምር ሚዲያዎች በአንድ ሙዚቃ በሚቀመጥላቸው የገንዘብ መጠን እና ጊዜ እንዲከፍሉ ያስገድዳል።
መገናኛ ብዙሀኑ ለሚያጫውቱት አንድ የሙዚቃ ስራ ምን ያህል ይክፈሉ የሚለው ግልፅ ሆኖ አልተቀመጠም።
የውልሰው ገዝሙ. Ethoo Fm 107.8



