Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  በለዘብተኛ አቋማቸው የተነሳ – “ሳይደመሰሱ የቆዩት የስግብግብ ጁንታ አመራሮች ነፍስም እንደ ወፏ ሁሉ በእጃችን መዳፍ ውስጥ መሆኑን እኛ እንደ እናት እናውቀዋለን “
News

በለዘብተኛ አቋማቸው የተነሳ – “ሳይደመሰሱ የቆዩት የስግብግብ ጁንታ አመራሮች ነፍስም እንደ ወፏ ሁሉ በእጃችን መዳፍ ውስጥ መሆኑን እኛ እንደ እናት እናውቀዋለን “

Ethioreview newsEthioreview news—February 19, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

” ይገርማል” አሉ  ልብ እያወቀ እንዲሉ። የኢትዮጵያ ብሄራዊ የመረጃና የደህንነት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ” ይገርማል ” ያሉት ሰሞኑንን የተሰራጨውን ዜና በማስታወስ ነው። ” አንዳንዶችም በለዘብተኛ አቋማቸው ከመሞት መሰንበት ስለሚሻል በነፍስ ብንይዛቸው ይሻላል በሚል መታገሳችንን ልቦናቸው እያወቀ በደሀው ህዝብ የመኖር ዋስትና ላይ አደገኛ ቁማር መጫወት ጀመሩ”  ብለዋል። አክለውም  ” የቀሩት የስግብግብ ጁንታ አመራሮች ነፍስም እንደ ወፏ ሁሉ በእጃችን መዳፍ ውስጥ መሆኑን እኛ እንደ እናት እናውቀዋለን “

” ጭራሽ የካቲት ፩፩ መቀሌ እናከብራለን ብለው ሞኞችን ለማሞኘት ሞከሩ” ሲሉ የሰሞኑንን የትህነግ ሰዎች ዜና ያስታወሱት አቶ ተመስገን፣ ” አንዳንዶች እንደ ቴፕ ሪከርደር የገባላቸውን ካሴት የሚያጫውቱ በመሆናቸው ምክንያት ” ሊሆን የማይችል ጉዳይን በመደጋገም በደሃው ሕዝብ ላይ ቁማር ጨዋታ መጀመሩን ነው ያመለከቱት። ያስታወቁት።

በዚሁ ስብከታቸው ማለታቸው ነው ” ጭራሽ የካቲትት አስራ አንድን መቀሌ ላይ እናከብራለን ብለው ሞኞችን ለማሞኘት ሞከሩ” በማለት ስብከቱን የሞኞች፣ ስብከቱን ተቀብለው ደሃው ህዝብ ላይ የሚጭኑትም ሞኞች መሆናቸውን ገልጸዋል።

” አንዳንዶችም በለዘብተኛ አቋማቸው ከመሞት መሰንበት ስለሚሻል በነፍስ ብንይዛቸው ይሻላል በሚል መታገሳችንን ልቦናቸው እያወቀ በደሀው ህዝብ የመኖር ዋስትና ላይ አደገኛ ቁማር መጫወት ጀመሩ

More stories

“ሸገር ከተማ በመጪዎቹ 50 ዓመታት በአፍሪካ ከሚታወቁ ከተሞች አንዷ ትሆናለች”

February 26, 2023

የስንዴ አብይዮት፣ የትውልድ ማሳ

October 30, 2022

ትህነግ ትጥቅ ለመፍታት ወሰነ – ቴዎድሮስ አድሃኖም አብይ አህመድን በስልክ ተማጸኑ፤ አዲግራት መከላከያ መዳፍ ገባች

October 23, 2022

አዲስዓለም ሁከትና ግጭት ለመቀስቀስና ታጣቂዎችን ለመደገፍ ሲሰሩ ነበር- መርማሪ ፖሊስ

February 15, 2021

አማራ ክልልን በማስተንፈስና አንጻራዊ ሰላም በማስፈን የሚታወቁት አቶ ተመስገን በፌስ ቡክ ገጻቸው “ራስ ሳይጠና ጉተና … የማያድግ ልጅ ከእናቱ ጀርባ ላይ ታዝሎ ያፉጫል” በሚል ርዕስ እመዳፍ ውስጥ እንደገባችው ወፍ ምሳሌ ” የቀሩት የስግብግብ ጁንታ አመራሮች ነፍስም እንደ ወፏ ሁሉ በእጃችን መዳፍ ውስጥ መሆኑን እኛ እንደ እናት እናውቀዋለን ” ሲሉ በተፈለገ ሰዓት ልክ እጅ መዳፍ ውስጥ እንዳለች ወፍ መጨፍለቅ እንደሚቻል ተናግረዋል። ይህ ያልሆነው ግን “አንዳንዶች” ያሉዋቸው ከነበራቸው ለዘብተኛ አቋም አንጻር ከመኖር መሰንበት እንዲሉ በህይወት እንዲያዙ ከነበረው ፍላጎት አንጻር መሆኑንን አመልክተዋል።

አቶ ጌታቸው እጉድጓድ ውስጥ ሆነው ድምጻቸውን ካሰሙ በሁዋላ ” የካቲት 11 መቀሌ ላይ ይከበራል” የሚል መፈክር በስፋት ተደምጦ ነበር። አቶ ጌታቸው ራሳቸውም ቢሆኑ እርስ በርስ በሚቃረን መልኩ አንዴ መልሶ ማጥቃት እንደሚጀመሩ፣ ተመልሰው ደግሞ ” አንቸኩልም” ሲሉ ተደምጠው ነበር። አንድ መቶ ሺህ ሰራዊት መደምሰሳቸውን፣ ነገር ግን አንድ መቶ ሺህ ሰራዊት ደምስሰው ዋሻ ውስጥ መሆናቸው ሰሚውን ግራ ባጋባበት ወቅት አቶ ተመስገን ” ለዘበተኛ አቋም ላላቸው ሲባል” ሲሉ ያስነበቡት ጽሁፍ እንደ አንድ ከፍተኛ የደህንነት መሪ ጠንካራና የማያዳግም እርምጃ እንዳለ የሚያሳይ እንደሆነ ተመልክቷል።

  ” የቀሩት የስግብግብ ጁንታ አመራሮች ነፍስም እንደ ወፏ ሁሉ በእጃችን መዳፍ ውስጥ መሆኑን እኛ እንደ እናት እናውቀዋለን “

” ሁሉንም በንቃት እየተከታተልን ነው” በማለት ስለ ሱዳን ወረራ የከረረ ሃሳብ የሰነዘሩት አቶ ተመስገን ” የአባቶቻችንን ብቻ ሳይሆን የእኛን ክንድም የቀመሱ፣ በለውጥ መሪያችን ድጋፍና ጥረት ከአሸባሪነታቸው ችንካር የተላቀቁ፣ በውስጥ ያልተሳካላቸው፣ በውጭም በሀገራችን ድጋፍ የአይን ጉድፋቸው የተጠረገላቸው ጉዶች…” ነው ያሉዋቸው። አያይዘውም ” ሁሉንም በንቃት እየተከታተልን ነው። ጥንቃቄያችን እና ትዕግስታችን ለንፁሀን ዜጎች ነው። ቀይ መስመሩ ታልፎም የምንታገሰው ከፍርሀትና አቅም እጦት ሳይሆን ለንፁሀን ህዝቦች ካለን ክብር ብቻ ነው። አልያማ እኛ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያውያን ልጆች ነን። መቼ መነሳት እንዳለብን እናውቃለን። ከተነሳን ደግሞ በነቋሪዎች ፍላጎትና ዕቅድ ሳይሆን በራሳችን ነው” ሲሉ እመዳፍ ውስጥ እንዳለችው ወፍ ለቆ የማብረሩም ሆነ የመጨፍለቁ አማራጭ እጃችን ላይ እንደሆነ አምረው አስታውቀዋል።

ሙሉ ሃሳባቸው ከፌስ ቡክ ገጻቸው የተወሰደ

 “ራስ ሳይጠና ጉተና … የማያድግ ልጅ ከእናቱ ጀርባ ላይ ታዝሎ ያፉጫል” ተመስገን ጥሩነህ 

ከላይ የተጠቀሱት አባባሎች የአበው ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ናቸው። ራስ ሳይጠና ጉተና ማለት ራስን መሸከም በማያስችል ሁኔታ ሌሎች ግዝልዛል ጌጣጌጦች በአናት ላይ ደራርቦ ለመሸከም መሞከር ለራስ ህልውና አደገኛ መሆኑን አመላካች ነው። ቅድሚያ የራስን ደህንነት፣ ህልውና፣ የመኖር ዋስትና ሳያረጋግጡ ሌሎች ድሪቶዎችን መከማመር የመኖር ተስፋን እንደማጨለም ይቆጠራል እንደማለት ነው። አንዳንዴ ገደል አፋፍ ላይ ቆሞ ትልቅ ቋጥኝ ከቆምንበት የገደል አፋፍ በላይ ከፍታ ነጥብ ላይ ሆኖ ቋጥኙን ለማንከባለል የሚታገልን አካል እንደ መርዳት ይቆጠራል። የምንረዳው ራሳችንን ለመጥፋት ነው ማለት ነው። እኛ ገደል አፋፍ ላይ ቆመን ትልቁ ቋጥኝ ተንከባሎ እኛንው ወደ ገደል ገፍቶ እንዲያንኮታኩተን ሌት ተቀን መስራት ማለት ነው።

ሁለተኛው አባባል በእግሩ መሄድ የማይችል፣ መሄድ ቢችልም ብዙ እርቀት የማይጓዝ ህፃን በእናቱ ጀርባ ላይ መታዘሉ ግድ ነው። ይሁን እንጅ ታዝሎም የእናቱን ጆሮ የሚያደነቁር ፉጨት መልቀቅ ብቻ ሳይሆን ፋጨቱ ከጨቅላው ህፃን በላይ ሲሆን አስገራሚ ነው። እናቱ እሩህሩህ የእናትነት አንጀት፣ አዝሎ የማሳደግ የተፈጥሮ ግዴታ፣ እስከ ዘጠኝ ወር በውስጥ አቅፎና ተንከባክቦ ራስን የመተካት አስገራሚ የፍጡራን ተግባራዊ ትዕይንት እና ሌሎችም ምክንያቶች የአስገራሚ ልጇን ፉጨት ተቋቁማ ለማሳደግ ጥረቷን አታቋርጥም። እናት በልጇ ድርጊት አንጀቷ እጥፍ፣ ቆሽቷ እርር እና ጨጓረዋ ቅጥል ቢልም ሀዘኗ ቢኖርም ለልጇ ክፉ አትመኝም። ባይሆን እርር ብላም ልቦና ስጠው ልትል ትችላለች። ሆኖም ሌላው ተመልካች የልጁን እናቱ ጀርባ ላይ ሆኖ ማፏጨት የሚያዬው እንደ እናት በትዕግስትና በኃዘኔታ ሳይሆን ይሄ ባለጌ፣ ድኩማን፣ ባጭር ይቅጭህ በሚል መንፈስ ነው።

አንዳንዶችም በለዘብተኛ አቋማቸው ከመሞት መሰንበት ስለሚሻል በነፍስ ንይዛቸው ይሻላል በሚል መታገሳችንን ልቦናቸው እያወቀ በደሀው ህዝብ የመኖር ዋስትና ላይ አደገኛ ቁማር መጫወት ጀመሩ። ጭራሽ የካቲት ፩፩ መቀሌ እናከብራለን ብለው ሞኞችን ለማሞኘት ሞከሩ። ይገርማል።

ትህነግ ከላይ የተገለፁ አባባሎች ተግባራዊ ምሳሌ ነው። የሚገርመው ደግሞ ሁሌም ከስህተቱ የማይማር፣ የማይፀፀት፣ በስህተት ላይ ስህተትን የሚደራርብ ጉድ መሆኑ ነው። ከወደቁ በላይ መንፈራገጥ ትርፉ መላላጥ ነው። ፈላስፋና አዋቂውን አባት ሊገዳደሩ የሞከሩ ግብዞች አንዲትን ወፍ በእጃቸው መዳፍ ውስጥ አስገብተው ይህች ወፍ በህይወት አለች ወይስ ሞታለች? አዋቂ ከሆኑ እስኪ ይንገሩን? ይበሉ? ብለው እንደፈተኗቸው ሁሉ። ፈላስፋው እና አዋቂው ሰውም የወፏ የህይወት ህልውና በእጃችሁ ነው፤ ከፈለጋችሁ ጨፍልቃችሁ መግደል፣ ስትፈልጉም እፉኛችሁን ከፍታችሁ ህይወቷን ማዳን ትችላላችሁ እንዳሉት ሁሉ። የቀሩት የስግብግብ ጁንታ አመራሮች ነፍስም እንደ ወፏ ሁሉ በእጃችን መዳፍ ውስጥ መሆኑን እኛ እንደ እናት እናውቀዋለን።

አንዳንዶች እንደ ቴፕ ሪከርደር የገባላቸውን ካሴት የሚያጫውቱ በመሆናቸው ምክንያት፣ አንዳንዶችም በለዘብተኛ አቋማቸው ከመሞት መሰንበት ስለሚሻል በነፍስ ብንይዛቸው ይሻላል በሚል መታገሳችንን ልቦናቸው እያወቀ በደሀው ህዝብ የመኖር ዋስትና ላይ አደገኛ ቁማር መጫወት ጀመሩ። ጭራሽ የካቲት ፩፩ መቀሌ እናከብራለን ብለው ሞኞችን ለማሞኘት ሞከሩ። ይገርማል።

በለውጥ መሪያችን ድጋፍና ጥረት ከአሸባሪነታቸው ችንካር የተላቀቁ፣ በውስጥ ያልተሳካላቸው፣ በውጭም በሀገራችን ድጋፍ የአይን ጉድፋቸው የተጠረገላቸው ጉዶች፣ ኢትዮጵያ እንኳንስ ለቅርብ ዘራፊና ሙሰኛ መሪዎች ይቅርና ለውጭ ወራሪዎችም እጅ ያልሰጠች፣ ያልተንበረከከች፣ የራሷን ብቻ ሳይሆን አቅም ሳይኖራቸው እና እንደ ወፏ መዳፋችን ውስጥ የሚገኙ ተላላኪዎች ለእነሱ ነፃነት መረጋገጥ ፋና ወጊ ሚና የተጫወተች ሀገራችን መሆኗን የሩቅም የቅርብን ታሪካችን ይመሰክራል።


ይህ አንሶ በእኛው አባይ ፖለቲካ የተጠመዱ ግብዞች መሾፈር የጀመሩ፣ የአባቶቻችንን ብቻ ሳይሆን የእኛን ክንድም የቀመሱ፣ በለውጥ መሪያችን ድጋፍና ጥረት ከአሸባሪነታቸው ችንካር የተላቀቁ፣ በውስጥ ያልተሳካላቸው፣ በውጭም በሀገራችን ድጋፍ የአይን ጉድፋቸው የተጠረገላቸው ጉዶች፣ ኢትዮጵያ እንኳንስ ለቅርብ ዘራፊና ሙሰኛ መሪዎች ይቅርና ለውጭ ወራሪዎችም እጅ ያልሰጠች፣ ያልተንበረከከች፣ የራሷን ብቻ ሳይሆን አቅም ሳይኖራቸው እና እንደ ወፏ መዳፋችን ውስጥ የሚገኙ ተላላኪዎች ለእነሱ ነፃነት መረጋገጥ ፋና ወጊ ሚና የተጫወተች ሀገራችን መሆኗን የሩቅም የቅርብን ታሪካችን ይመሰክራል።

የሚገርመው ደግሞ ማንም ቢመጣ አንንበረከክም፣ አንሸነፍም፣ እኛ ለውጊያ የተፈጠርን ነን የሚለው የታራክ ዝቃጩ ከፋፋይ ስግብግብ ጁንታ በራሱ መሬት፣ ዕቅድና ፍላጎት አከርካሪው ሲሰበር ከቅጥረኛ፣ ሙሰኛና ተላላኪ ጎረቤቶች ጋር ተሰልፎ ዕድሉን ለመሞከር ሽር ጉድ ማለቱ ሌላ የታሪክ ጥቁር ነጥብ እና ጠባሳ ከማስቀመጥ ሌላ የሚያተርፈው ነገር እንደሌለ ልቦናው ያውቀዋል።


ሁሉንም በንቃት እየተከታተልን ነው። ጥንቃቄያችን እና ትዕግስታችን ለንፁሀን ዜጎች ነው። ቀይ መስመሩ ታልፎም የምንታገሰው ከፍርሀትና አቅም እጦት ሳይሆን ለንፁሀን ህዝቦች ካለን ክብር ብቻ ነው። አልያማ እኛ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያውያን ልጆች ነን። መቼ መነሳት እንዳለብን እናውቃለን። ከተነሳን ደግሞ በነቋሪዎች ፍላጎትና ዕቅድ ሳይሆን በራሳችን ነው። ማንም እኛ ዓቅደን የምንሰራውን፣ የእኛ ሀብት የሆነውን ሁሉ የመከልከልና የመዝረፍ ተፈጥሯዊም ህጋዊም ዓቅምም ይሁን ስልጣን እንደሌለው ያውቃል። እናም ነቋሪ ሙሰኛና ዘራፊ የጎረቤቶቻችን መሪዎች ከሌሎችና ከራሳቸው ታሪክ ብቻ ሳይሆን ኮትኩተው ካሳደጉት ስግብግብ ጁንታ አሳፋሪ ታሪክ፣ ስግብግብ ጁንታውም በተመሳሳይ ከውድቀቱ መማር ይገባቸዋል። ካልሆነ እንደለመዱት ከመከራቸው እንዲማሩ ይገደዳሉ። ሁሉ ነገር ለእኛ የእምቧይ ካብ ነው። ይሄው የካቲት ፩፩ በመቀሌ ሳይሆን ገደል ውስጥ ተወሽቀው አሳለፉት። ነገ ደግሞ ልቦና ካልገዙና ከስህተታቸው መማር ካልቻሉ የተወሸቁበት ገደል ውስጥ ይቀበራሉ። ምርጫው ግን በእጃቸው ነው።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!!

  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
NEWSOPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ኢሳያስ አፉወርቂ – የትልቁ ስዕል ቅኔ፣ የቅዠቱ መነሻ፣ የቀጣናው ባዶ የፖለቲካ ጉሊት
« የኢሳያስ ጦር ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን እንደ በረከት፣ መለኮታዊ ጣልቃ ገብነት እቆጥረዋለሁ »
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2