Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የአገር ደህንነት – ከአንድ ሺህ በላይ የህወሃት ወታደራዊ አመራሮችና በጥፋት የተሳተፉ አባላት ህግ ፊት ልያቀርብ ነው፤
News

የአገር ደህንነት – ከአንድ ሺህ በላይ የህወሃት ወታደራዊ አመራሮችና በጥፋት የተሳተፉ አባላት ህግ ፊት ልያቀርብ ነው፤

Ethioreview newsEthioreview news—February 6, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በጁንታው ፀረ ሰላም እንቅስቃሴ ውስጥ የተሳተፉ 420 የህወሃት ከፍተኛ የፖለቲካና ወታደራዊ አመራሮችና 682 በወንጀል ድርጊት የተሳተፉ አባላት በህግ እንዲጠየቁ እየተሰራ ነው –ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት

ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በጁንታው ፀረ ሰላም እንቅስቃሴ ውስጥ የተሳተፉ 420 የህወሃት ከፍተኛ የፖለቲካና ወታደራዊ አመራሮች እንዲሁም 682 በወንጀል ድርጊት የተሳተፉ የጁንታው አባላት ላይ መረጃ በማሰባሰብ በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑን ገለጸ ።

ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የመጀመሪያ ስድስት ወር የሥራ አፈጻጸም በተመለከተ ያካሄደውን ግምገማ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መረጃ፤ ከትግራይ ክልል የህግ ማስከበር ዘመቻ ጋር በተያያዘ በጁንታው ፀረ ሰላም እንቅስቃሴ ውስጥ ሲሳተፉ የቆዩ 420 የህወሃት ከፍተኛ የፖለቲካና ወታደራዊ አመራሮች እንዲሁም 682 በወንጀል ድርጊት የተሳተፉ የጁንታው አባላት በቁጥጥር ሥር ውለው በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ አስፈላጊው መረጃ ተዘጋጅቶና ተደራጅቶ ለጸጥታ አስከባሪ ዘርፉ መሰጠቱን ገልጿል፡፡

አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ በ2010 ዓ.ም ካካሄደው ሪፎርም በኋላ የተቋሙ አባላት ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ በመሆን እንዲያገለግሉ አቅጣጫ አስቀምጦ እስከታች በማውረድ ተግባራዊ ቢያደርግም፤ የተቋሙን አሠራር በመጣስ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ተልዕኮ ለማስፈጸም በተግባር የተሳተፉ ሰራተኞች ላይ እርምጃ መወሰዱን አመልክቷል።

More stories

የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚጥሰው HR6600/S3199 ሕግ ተቋረጠ

April 6, 2022

አጫጭር ወቅታዊ መረጃዎች

June 30, 2021

የብረት ሌባ “ባለሃብቶች” – ነዳጅ ስር የሚርመጠመጡ ባለስልጣናት

December 20, 2022

“ጥምቀትና መተጫጨት”

January 18, 2023

 በተለይ በተቋሙ የውጭ ስምሪት ሥራ ላይ የነበሩ 3 አባላት ከአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መርህ ውጪ ከጁንታው ቡድን ጋር በማበር የዲፕሎማቲክ ሽፋናቸውን አላግባብ በመጠቀማቸው እንዲሁም 20 አባላት ደግሞ መረጃን ተገቢ ባልሆነ መንገድ ሲጠቀሙ በክትትል ስለተደረሰባሰቸው በተቋሙ ህግና አሰራር መሠረት እርምጃ እንዲወሰድባቸው መደረጉን ገልጿል።

 እንደ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ማብራሪያ፤ በትግራይ ክልል በሚገኘው የሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ከተፈጸመ በኋላ ለመንግስት አስፈላጊ የደህንነት መረጃ ሪፖርቶች ሲቀርቡ ነበር፡፡

 የህግ ማስከበር ዘመቻው በድል እንዲጠናቀቅ በመደገፍ ጁንታው በትግራይ ክልል የሰሜን ዕዝ ላይ ከፈጸመው አሠቃቂ ጥቃት ጋር በተያያዘ የጁንታው ቁልፍ የፖለቲካና ወታደራዊ አመራሮችና ሰራዊታቸውን እንቅስቃሴ፤ የተለያዩ ወታደራዊ ሚስጥሮችን፣ ድብቅ ሴራዎችን፣ የጁንታውን ትልሞችና የሽብር ሥራዎችን የሚያጋልጡ መረጃዎችንና ሰነዶችን በማሰባሰብ ረገድ ተቋሙ ውጤታማ ሥራ ማከናወኑ በግምገማው ወቅት መገለፁን መረጃው አመልክቷል።

በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱትን የኦነግ ሸኔና የጉምዝ ታጣቂዎችን እንዲሁም የድንበር ተሻጋሪ ወንጀለኞችን እንቅስቃሴዎች ለመግታት በሚደረገው ጥረትም በአጠቃላይ ከ432 በላይ ተጠርጣሪዎች ላይ መረጃ በመሰብሰብ ለሚመለከተው አካል እንዲሰጥ ማድረጉን ገልጿል፡፡

 በተጨማሪም የኢትዮጵያን ሰላምና መረጋጋት በማወክ ፍላጎታቸውን ለማራመድ የሚንቀሳቀሱ አሸባሪ ሀይሎችና ቡድኖች በሀገሪቱ ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት ላይ ስጋት እንዳይደቅኑ ለማድረግ በተከናወነው የክትትል ሥራ 233 ተጠርጣሪዎች ላይ መረጃ በመሰብሰብ ለሚመለከታቸው አካላት የተለካ ሲሆን፤ 13 ተጠርጣሪዎች ደግሞ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተመልክቷል።

 በተቋሙ ፕሮፌሽናል፣ ትውልድ ተሻጋሪና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስራ እንዲከናወን በተደረገው ሁሉን አቀፍ ሪፎርም አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ ሲሆን፤ በተያዘው የበጀት ዓመትም የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱን ተልዕኮና አላማ የሚወክል አዲስ ሎጎ ሥራ ላይ እንዲውል፤ በተቋሙ ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠርና ለተልዕኮው ስኬት አስፈላጊ የሆኑ ግብዕቶችን ለማሟላት የተጀመሩ ስራዎች አበራታች መሆናቸውን በሚቀጥለው ግማሽ አመትም ይሄው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አገልግሎት መስሪያ ቤቱ በላከው መረጃ አስታውቋል።

 ከዚህ በተጨማሪም ተቋሙ፤ በሀገር ውስጥ ከህዝቡ የሚሰበሰቡ መረጃዎችን ጥቅም ላይ በማዋል፤ ከውጭ ከተለያዩ ሀገራት አቻ የመረጃ የደህንነት ተቋማት ያለውን ግንኙነት በማጠናከርና የመረጃ ልውውጥ በማድረግ መረጃ የመሰበሰብ አቅሙን ለማጎልበት እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎች በጥሩ ጎን ተገምግመዋል፡፡

 ይህ በእንዲህ እንዳል ከላይ በጥንካሬ የተገመገሙ ጉዳዮች ቢኖሩም፤ የተጀመረውን ሃገራዊ የለውጥ ሪፎርም በሃሰት ለማደናቀፍ፤በመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፤ በመንግስት የአሰራር ስርዓቶች፤ ሲስተሞችና አጠቃላይ መዋቅሩ ላይ አልፎ አልፎም በፀጥታና ደህንነት ተቋማት ላይ የሃሰትና የበሬ ወለደ ስም የማጠልሸትና የማጥፋት እንቅስቃሴ መንግስት በህዝብ ላይ ያለውን ተቀባይነት ጥራጣሬ ውስጥ ለመክተትና የሃገርን ሰላም ለማደፍረስ ሌት ተቀን ከሚሰሩ የውስጥና የውጭ ሃይሎች አጀንዳ በመቀበል የሚሰሩ አካላት ላይ መረጃ በማሰባሰብ በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ከማድረግ አኳያ ክፍተት መኖሩ በግምገማው የታየና በቀጣይ ተቋሙ በዚሀ ጉዳይ ላይ በትኩረት መስራት እንዳለበት ከመግባባት ላይ መደረሱ የኢዜአ ዜና ያሳረዳል።

 መጪው ሀገራዊ ምርጫም ያለምንም የፀጥታና የደህንነት ስጋቶች በሰላም እንዲጠናቀቅ ተቋሙ ከሌሎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር ለመስራት አቅዶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አገልግሉት መስሪያ ቤቱ በላከው መረጃ አስታውቋል፡፡

    FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
    የዓለም ምግብ ድርጅት ሠብዓዊ ድጋፍ፣ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አቀርባለሁ አለ፤ 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዜጎች ሠብዓዊ ድጋፍ አግኝተዋል
    ለኦሮምኛ ላቲን ወይስ የአማርኛ (ኦ ይቅርታ) የግዕዝ ፊደል?
    Related posts
    • Related posts
    • More from author
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    News

    ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

    April 13, 2026
    Load more
    Read also
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    WORLD

    ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    WORLD

    አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

    April 26, 2026
    WORLD

    የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

    April 26, 2026
    WORLD

    የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

    April 26, 2026
    Load more
    Recent Posts
    • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
    • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
    • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
    • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
    • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
    • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
    • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
    • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
    • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
    • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
    • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
    • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
    • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
    • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
    • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
    Social networks
    FacebookLikes
    X TwitterFollowers
    PinterestFollowers
    InstagramFollowers
    YoutubeSubscribers
    VimeoSubscribers
      VOE
      The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

      MENU

      NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
      © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
      • CONTACT
      • law
      • INTERVIEW
      • ያበደው
      • ECONOMY
      • Home demo times
      • VOE VIDEO
      • ENGLISH PAGE
      • Home Demo default 2