Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ድምጻዊ ጥላሁን ገሠሠ፡ ከ20 ዓመታት በፊት የተቀዳው የሙዚቃው ንጉሡ ‘ምርቃት’
News

ድምጻዊ ጥላሁን ገሠሠ፡ ከ20 ዓመታት በፊት የተቀዳው የሙዚቃው ንጉሡ ‘ምርቃት’

Ethioreview newsEthioreview news—March 14, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ያላዜመበት አርዕስት የለም። በሙዚቃ ሥራዎቹ ያልመዘዘው የሕይወት ሰበዝ፣ ያልዳሰሰው የኑሮ ቋጠሮ፣ ያልደረሰበት የሐሳብ ጥግ የለም ይላሉ በርካቶች።

አገርና ሰንደቅ፤ ሰላምና ፍቅር፤ ትዝታና ናፍቆት፤ ማግኘትና ማጣት፤ ሳቅና ለቅሶ፤ ሕይወትና ሞት፤ መውደቅና ስኬት፤ ጥያቄና ምፀት፤ ጊዜና ቀጠሮ፤ ነጻነትና ፍትሕ፤ መውደድና መጥላት፤ እውነትና እብለት፤ ዝምታና ጩኸት፤ ፅድቅና ኩነኔ፤ ሐብትና ድህነት፤ ተፈጥሮና ውበት፤ መጠጥና ምግብ፤ ስለሳር ቅጠሉም. . . ሌላም ሌላም።

እልፍ ሥራዎችን ሰርቷል። ቆጥሮ የደረሰበት ስለመኖሩም እንጃ።

የጠየቅናቸውም “እሱ መሥራት እንጂ ቆጠራው ላይ መቼ አለበት” ነው ያሉት።

More stories

የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚጥሰው HR6600/S3199 ሕግ ተቋረጠ

April 6, 2022

አጫጭር ወቅታዊ መረጃዎች

June 30, 2021

የብረት ሌባ “ባለሃብቶች” – ነዳጅ ስር የሚርመጠመጡ ባለስልጣናት

December 20, 2022

“ጥምቀትና መተጫጨት”

January 18, 2023

ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ እንደ ብላቴና የሙዚቃን እግር የሙጥኝ ብሎ ጥበብን ከፍ አድርጓታል። ሙዚቃ እራሷ በእሱ ስም ትጠራ የሚሉለትም አሉ።

ሙዚቃዎቹ በእድሜና በዘመን የሚለዩ አይደሉም። ትውልድ እየተቀባበለው የሚሻገሩ እንጂ።

ታዲያ ሙዚቃ ወዳጁ ብትሆንም እንደ ክፉ ባልንጀራም ፍዳውን አብልታዋለች። ፖለቲካዊ ይዘት አላቸው በተባሉ ሥራዎቹ ቡጢና እርግጫ፤ እንዲሁም እስርን ቀምሶባታል። የሙዚቃው ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሠሠ።

ጥላሁን በሞት ከተለየ አስራ ሁለት ዓመታት ተቆጥረዋል።

በስኳር ህመም ሲሰቃይ የነበረው ጥላሁን ድንገት ባጋጠመው ህመም፤ በ68 ዓመቱ ይችን ዓለም የተሰናበተው ሚያዚያ 12/2001 ዓ.ም ነበር።

ምንም እንኳን በሞት ከተለየ ዓመታት ቢነጉዱም ድምጹ ከሙዚቃ አፍቃሪዎች ጆሮ ርቆ አያውቅም።

ጀማሪ ድምጻዊያንም የእሱን ሥራ የብቃታቸው ጥግ ሚዛን አድርገው ሲያነሱ ሲጥሉ ነው የሚውሉት። በየሙዚቃ ውድድሮቹ ተወዳዳሪዎች ይዘዋቸው ከሚቀርቡ ሥራዎችም አብዛኞቹ የእርሱ ናቸው።

አሁን ደግሞ ‘የመጨረሻው’ የሙዚቃ እስትንፋሱ ለአድማጭ ጆሮ በቅቷል – ምርቃት።

‘ምርቃት’ የአልበሙ መጠሪያ ነው። በውስጡ አስር ዘፈኖችን ይዟል። ዜማው የሞገስ ተካ፤ ያቀናበረው ደግሞ አንጋፋው የሙዚቃ አቀናባሪ አበጋሱ ክብረወርቅ ሺዮታ ነው።

በግጥም ሥራዎቹም ሞገስ ተካን ጨምሮ ያየህይራድ አላምረው፣ ሶስና ታደሰና አለምፀሐይ ወዳጆ ተሳትፈውበታል።

‘ምርቃት’

‘ምርቃት’ ሕይወቱ ካለፈ ከ12 ዓመታት በኋላ ነው የወጣው።

ይህ አልበም የጥላሁን ስንተኛው ሥራ እንደሆነ ግን በቁጥር ያወቀ አላገኘንም።

በግምት ከ300 ወይም ከ400 በላይ የሙዚቃ ሥራዎችን ሳያበረክት እንዳልቀረ ግን ባለቤቱ ወ/ሮ ሮማን በዙ ይናገራሉ።

ወ/ሮ ሮማን “ጥላሁን ምን ያህል ሥራዎችን እንደሰራ ባለሙያም፤ ቤተሰብም መናገር መቻል ነበረበት። ግን ይህን ያህል ሥራ አለው ማለት ያልቻልነው፤ ታሪክ የማሰባሰቡ ሥራ ላይ ደካማ ስለሆንን ነው” ሲሉም ይወቅሳሉ።

በእርግጥ ከሙት ዓመቱ በኋላ የሰራቸውን ሥራዎች ሰብስቦ በታሪክ ለማስቀመጥ ሲንቀሳቀሱ ነበር የቆዩት። ሆኖም ዳር አልደረሰላቸውም።

ይህን አልበም ያቀናበረው እውቁ የሙዚቃ አቀናባሪም “ካሉ አርቲስቶች በጣም ቁጥሩ የበለጠ ሥራ የሠራ አርቲስት እንደሆነ እንጂ ቁጥሩን አላውቀውም፤ ግን በርካታ ነው” ብሏል።

አገራዊ ዜማ ከአልበሙ የማይታጣው ጥላሁን፤ በዚህ አልበሙም ስለ አገር አዚሟል።

“. . . ሴራው ይክሸፍበት የመታብሽ አድማ

እጁን ሳር ያድርገው፤ ጉልበቱን ቄጠማ . . .” ብሎላታል አገሩን ሲመርቅ፤ ጠላቶቿን ሲረግም።

ይህ የሙዚቃ አልበም ስለፍቅር፣ ፍትሕ፣ እርቅ፣ አገር እንዲሁም ስለራሱ ሕይወት የሚያነሱ ሥራዎች የተካተቱበት ነው።

‘ቆሜ ልመርቅሽ’ የተሰኘው አገራዊ ዜማ፤ አሁን ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር የሚሄድ በመሆኑ በርካቶች የትንቢት ያህል ቆጥረውታል።

ወ/ሮ ሮማንም “‘ቆሜ ልመርቅሽ’ን ለየት የሚያደርገው የአገራችንን የአሁኑን ሁኔታ የሚያንፀባርቅ መሆኑ ነው” ይላሉ። ‘ያኔ ባለሙያዎቹ ምን ታይቷቸው ነበር?’ ያስባለ እንደሆነም ተናግረዋል።

አልበሙ በሼክ መሐመድ ሁሴን አሊ አላሙዲንና በአቶ አብነት ገብረመስቀል ፕሮዲዩስ መደረጉን የገለጹት ወ/ሮ ሮማን፤ ‘ምርቃት’ ለሕዝብ እንዲደርስ ላደረጉት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።

ይህ ሙዚቃ በምን ሁኔታ ነበር የተሰራው?

የሙዚቃ አቀናባሪው አበጋሱ ለጥላሁን ሥራዎች እንግዳ አይደለም።

ከዚህ ቀደም የወጡ አራት አልበሞቹን ከሙላቱ አስታጥቄና ቴዲ ማክ ጋር በመሆን እንደገና አቀናብሯል። የአሁኑን ጨምሮ ሁለት አዲስ አልበሞችንም ሰርቷል።

ይህንን አልበም በማቀናበሩም “በጣም እድለኛ እንደሆንኩ ነው የሚሰማኝ” ይላል።

አበጋሱ እንደሚለው ይህ አልበም መጀመሪያ ከተቀረጸ 20 ዓመት ገደማ ይሆነዋል። የቀረጸውም እራሱ ነበር። የተጀመረው አሜሪካ በአበጋሱ ስቱዲዮ፤ የተጠናቀቀው ደግሞ አዲስ አበባ።

‘ምርቃት’ በአበጋሱ እጅ ለ18 ዓመታት ያህል ቆይቷል።

“ከእኔ ጋር መሆኑ ትልቅ እድል ነው፤ በጣም ደስተኛ ነኝ” ይላል አበጋሱ።

በአልበሙ ላይ የምንሰማቸው የጥላሁን ድምፆች ከህመም ጋር እየታገለ ያወጣቸው ናቸው። የልምምድ እንጂ የመጨረሻ ያለቀላቸው ቅጂዎች አልነበሩም።

በዚያ ላይ ደግሞ በህመሙ ምክንያት ወጣ ገባ እየተባለ የተሰራ።

አበጋሱ እንደሚለው በጊዜው ጥላሁን ጥሩ ቀኖችም፤ መጥፎ ቀኖችም ነበሩት። የሁኔታዎችና የስሜት ለውጦችም እንዲሁ።

“ትዝታዎች ውስጥ የሚገባበት ጊዜም ነበር። የዝምታ ድባቦችም ነበሩ። ጥሩ ግንኙነቶችም ነበሩን። ታሪኮችን እጠይቀው ነበር። እኔ ከእርሱ መውሰድ እፈልግ ነበር። ጋሽ ጥላሁን ህልመኛ ነው፤ በራሱ ዓለም የሚሆንበት ጊዜም ነበር” ይላል አበጋሱ-በወቅቱ የነበረውን ሲያስታውስ።

በእርግጥ ያኔ ሙዚቃውን እንደ ሥራ እንጂ፤ ሰው ጋ እንዲህ ዓይነት ስሜት ይፈጥራል ብሎ አላሰበም ነበር።

ድምጻዊ ሚኒሊክ ወስናቸው፣ ጥላሁን ገሠሠ፣ አለማየሁ እሸቴና ማህሙድ አሕመድ [ከግራ ወደ ቀኝ]
የምስሉ መግለጫ,ድምጻዊ ሚኒሊክ ወስናቸው፣ ጥላሁን ገሠሠ፣ አለማየሁ እሸቴና ማህሙድ አሕመድ [ከግራ ወደ ቀኝ]

ጥላሁን ሌሎች ያልወጡ ሥራዎች ይኖሩት ይሆን?

አበጋሱ ይህ አልበም የጥላሁን የመጨረሻ ሥራ እንደሆነ ነው የሚያስበው።

“በእርግጥ እንደ ጥላሁንና ማህሙድ ዓይነት የመዝፈን ፍቅር ያላቸው ባለሙያዎች የሆነ ቦታ ሄደው ‘ሙዳቸው’ ከመጣ ሊዘፍኑ ይችላሉ። በዚህ ምክንያት ያልወጡ ይኖሩ ይሆናል ብዬ እገምታለሁ” ይላል።

ወ/ሮ ሮማንም ‘ይህን የሚያውቁት ባለሙያዎች ናቸው’ የሚል ምላሽ ሰጥተውናል።

አልበሙ ይህን ያህል ዓመት ለምን ቆየ?

አበጋሱ እንደሚለው ሥራው ሳይጠናቀቅ ጥላሁን ከዚህ ዓለም በሞት በመለየቱ ነገሮች እንደታሰቡት አልሆኑም።

ከ20 ዓመታት በፊት የተቀዳን ድምፅ አሁን ካለው ቴክኖሎጂ ጋር ማጣጣም ፈተና ነበር ይላል። ብዙ ድካሞችና ልፋቶች ነበሩት።

የመጨረሻ ቅጂም ስላልነበር ጥላሁን በወቅቱ የነበረበት እውነተኛ ስሜት በድምፁ ተይዟል።

አንዳንዴ ከጀርባ የሚሰሙ ድምፆች ነበሩ። ያንን ማፅዳቱም ጊዜ ፈጅቷል። ቢሆንም ግን “በውጤቱ ረክቻለሁ” ብሏል አበጋሱ።

ከዚህም ባሻገር የነበሩበት የሥራ ጫናዎችም፤ አልበሙ የአፍላ ወጣት እድሜ ያህል ቆይቶ እንዲወጣ ምክንያት ሆነዋል።

አበጋሱ እንዳለው ሙዚቃዎቹን አሳምሮ ለማውጣት የተጠቀመው የተለየ ቴክኒክ የለም። ድምፁን ማሻሻልም አልተፈለገም።

ይሁን እንጂ በተለያየ ጊዜና በተለያየ የሙዚቃ ‘ኪይ’ ሲለማመድ ስለነበር እነርሱን ለማጣጣም “‘አውቶ ቲዩን'[የድምፅ ፒች ማስተካከያ] በትንሹ በመጠቀም ስሜቱን ለማውጣት ሙከራ አድርገናል” ብሏል።

“አንድም ቀን ያለ ስሜት ሲዘፍን አይቼው አላውቅም”

ጥላሁን አንድን ዜማ ሲቀበል ወደ ራሱ በማምጣቱና ወደ ራሱ ቅላጼና ገለጻ በማጣጣም ችሎታው ለአበጋሱ ለየት ይልበታል።

“ከጥላሁን ጀርባ ከባድ ስሜት አለ። መመሰጥ አለው። ከስሜት ጋር ቁርኝት አለው” የሚለው አበጋሱ አንድም ቀን ያለ ስሜት ሲዘፍን አይቶት እንደማያውቅ ይናገራል።

“በህመም ላይ ሆኖም ሲቀረጽ ያ ተፅእኖ አያሳድርበትም ነበር። ታሞም ይመሰጣል። እንደዚያ መሆን ሲያቅተው ‘በቃኝ ቤት ውሰደኝ’ ይለኛል” ይላል አበጋሱ።

አበጋሱ እንደሚለው ጥላሁን ስሜት ከሌለው ለሙዚቃ የሚገባውን ነገር ያልሰጠ ይመስለዋል።

ወ/ሮ ሮማንም ሥራዎቹ በግርድፍ ያሉ ስለነበሩ እንደዚህ ይሰራል የሚል ሃሳብ እንዳልነበራቸው ገልፀው፤ “ታሞ የነበረ ድምፅ እኮ ራሱ ታሪካዊ ነው” ይላሉ።

“ጥላሁን የሙዚቃ ጥጉን አስቀምጦ የሄደ ባለሙያ ነው። እያቃሰተም፤ እያለቀሰም ቢዘፍነው ታሪክ ነው” ብለዋል ወ/ሮ ሮማን።

የዋለውን ያህል ያልተዋለለት ጥላሁን

ጥላሁን ይህችን ዓለም ከተሰናበተ ድፍን 12 ዓመታት ተቆጥረዋል።

ነገር ግን ከዘመን አይሽሬ ሙዚቃዎቹ በስተቀር ለስሙ መጠሪያ አንድም ማስታወሻ አልቆመለትም፤ አልተሰየመለትም። ለምን? ይህ የብዙዎች ጥያቄ ነው።

ባለቤቱ ወ/ሮ ሮማን ለጥላሁን በስሙ መንገድ ለማሰየም፤ አደባባይ ለማሰራት የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን በር ሲያንኳኩ ነው የቆዩት። ግን በአሰቡት ልክ አልሄደላቸውም።

“ጥላሁን የገንዘብ ሰው አይደለም። እያነባ እያለቀሰ ‘አገሬ አገሬ’ እያለ የሞተ ሰው ነው። ይህንን ሥራ ለሰራ ሰው፤ አደባባይ ለመሥራት እንኳን 12 ዓመት 12 ወር መፍጀት አልነበረበትም” ይላሉ ወጥተው የወረዱትን በማስታወስ።

ለነገሩ ወደ መሿለኪያ አካባቢ አደባባይ ለማሰራት ፈቃድ አግኝተው ነበር። ይሁን እንጂ ኋላ ላይ ቀለበት መንገድ ተሰርቶበት በመፍረሱ ሳይሆን መቅረቱን ይናገራሉ።

ተለዋጭ ቦታ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም ሰሚ ሳያገኙ ቆይተዋል።

“አሁን ከረዥም ዓመታት በኋላም ቢሆን፤ በአገር ደረጃ መታየት የነበረበት ባለሙያ በክብር ስለታየልን ደስ ብሎናል” ብለዋል ወ/ሮ ሮማን።

ድምጻዊ ጥላሁን ገሠሠ እና ባለቤቱ ሮማን በዙ
የምስሉ መግለጫ,ድምጻዊ ጥላሁን ገሠሠ እና ባለቤቱ ሮማን በዙ

ይህን ያህል ደጅ መጥናት ለምን? ያልናቸው ወ/ሮ ሮማን ዝርዝር መልስ አልሰጡም።

“ምንም እንኳን ጥላሁን የአገር ሐብት ቢሆንም፤ የሚመጣውም፤ የሚሄደውም መንግሥት ጥላሁንን እንዴት ያየዋል የሚለው ራሱን የቻለ ጥያቄ ነው” ሲሉ በደምሳሳው አልፈውታል።

“ባለታሪክን የምናደንቀውና የምናወድሰው ጊዜና ወቅት እየጠበቅን መሆን የለበትም” ሲሉም በተለያየ ሙያ ላይ ብዙ ጀግኖች አስታዋሽ አጥተው ደብዛቸው ጠፍቶ የቀሩ ስለመኖራቸው ያወሳሉ።

በዚህ መንግሥት የታየው ጭላንጭል ግን ተስፋ ሰጭ ነው ብለዋል።

በጥላሁን ስም ምን ለመስራት ታስቧል?

ጥላሁን በሕይወት እያለም፤ ከህልፈቱ በኋላም በስሙ ለመስራት የተያዙ ፕሮጀክቶች እንደነበሩ ወ/ሮ ሮማን ይናገራሉ።

ወ/ሮ ሮማን እንደሚሉት ጥላሁን የኢኮኖሚ አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ሰዎች በነጻ የሚታከሙበት የስኳር ህሙማን ሆስፒታል ለማቋቋም ቃል ገብቶ ነበር።

እርሱም ጤንነቱ የተጓደለው በዚሁ በሽታ ነበር።

በሕይወት ሳለም ሆስፒታሉን ለማሰራት የተወሰነ እንቅስቃሴ አድርገዋል። ግን ይህ እውን ሳይሆን ነው ሕይወቱ ያለፈው።

“ከስኳር ህሙማን ማኅበር ጋር ለመስራት ተስማምተን፤ የሆስፒታሉ ዲዛይን ተቀርጾ እዚያ ላይ ነው በእንጥልጥል የቆመው” ብለዋል ወ/ሮ ሮማን።

ሙዚቃዎቹን እንዲሰባሰቡ ለማድረግ ሞክረውም በቤተሰብ አቅም ይህን ማድረግ ሳይቻል ቀርቷል።

አሁን ምላሽ ያገኘው የአደባባይ ጉዳይም የእቅዳቸው አካል ነበር።

የሙዚቃ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሌሎች መታሰቢያዎችን ለመስራት እየታሰበ መሆኑን ወ/ሮ ሮማን ተናግረዋል።

“ባለሙያውም፣ ባለሃብቱም፣ መንግሥትም ተረባርቦ እቅዱ እውን እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ” ብለዋል።

    FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
    “The crime of Genocide in Ethiopia; The case of Mai-Kadra” – Term paper
    በሃላይደጌ አሰቦት እጩ ብሄራዊ ፓርክ በተከሰተ የእሳት አደጋ እስካሁን ከ100 ኪሎ ሜትር ስኩየር የሚገመት ሳርና ቁጥቋጦ
    Related posts
    • Related posts
    • More from author
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    News

    ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

    April 13, 2026
    Load more
    Read also
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    WORLD

    ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    WORLD

    አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

    April 26, 2026
    WORLD

    የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

    April 26, 2026
    WORLD

    የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

    April 26, 2026
    Load more
    Recent Posts
    • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
    • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
    • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
    • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
    • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
    • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
    • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
    • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
    • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
    • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
    • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
    • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
    • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
    • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
    • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
    Social networks
    FacebookLikes
    X TwitterFollowers
    PinterestFollowers
    InstagramFollowers
    YoutubeSubscribers
    VimeoSubscribers
      VOE
      The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

      MENU

      NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
      © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
      • CONTACT
      • INTERVIEW
      • law
      • ECONOMY
      • Home demo times
      • ያበደው
      • VOE VIDEO
      • ENGLISH PAGE
      • Home Demo default 2