Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ታላቁ ህዳሴ ግድብ በመገባደጃ ምዕራፍ ላይ

    April 1, 2023

    የአሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችል ስራ መጀመሩን ይፋ አደረገ

    August 22, 2024

    ዶናልድ ትራምፕ በቁጥጥር ሥር ውለው በቀረበባቸው ሰላሳ አራት ክሶች ጥፋተኛ አይደለሁም አሉ

    April 6, 2023

    የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰነድ የሌላቸው የኤርትራዊ ስደተኞች መታሰራቸውን ኮነን፤ “ያለ ህጋዊ ማስረጃ የትኛው አገር መኖር ይቻላል?”

    June 4, 2023

    ቻይናዊው የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ከ9 ግብረ አበሮቻቸው ጋር የውጭ አገር ብሮች በማተምና በጥቁር ገበያ ወንጀል ታስረው ፍ/ቤት ቀረቡ

    September 5, 2023
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  በፔሮል የሚከፈላቸው የውጭ አገር ሚዲያና የሠብዓዊ መብት ታጋይ ነን የሚሉ ሃይሎች ኢትዮጵያ ላይ ዘመቻ መክፈታቸውን ይፋ ሆነ
News

በፔሮል የሚከፈላቸው የውጭ አገር ሚዲያና የሠብዓዊ መብት ታጋይ ነን የሚሉ ሃይሎች ኢትዮጵያ ላይ ዘመቻ መክፈታቸውን ይፋ ሆነ

Ethioreview newsEthioreview news—March 17, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

 በትግራይ ክልል ቀውስ ሰበብ በኢትዮጵያ ላይ ተፅዕኖ እንዲደርስ የሚሹ ተከፋይ የምዕራባዊያን ሚዲያና በሠብዓዊ መብት ስም የሚንቀሳቀሱ ሃይሎች መኖራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለጹ። የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዜጋ፣ በኢኮኖሚና በፖለቲካ ዲፕሎማሲ ሣምንታዊ አበይት ክንውኖች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸው በትግራይ ክልል ከተካሄደው የሕግ ማስከበር ዘመቻ በኋላ ምዕራባዊያን በየጊዜው በኢትዮጵያ ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር የሚያደርጉትን ጥረት አስመልክቶ ለተነሱላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።

የአገራቱ ጥያቄ በመጀመሪያ በጦርነቱ ወቅት ሠብዓዊ ድጋፍ አልተፈቀደም፣ ቀጥሎም የሠብዓዊ መብት ጥሰት አለ፣ በመጨረሻም ሠብዓዊ ድጋፉ ይጠናከር የሚሉ ጉዳዮችን ሲያነሱ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

ጥያቄያቸው በጊዜው እንደተፈቀደላቸው ገልጸው፤ ነገር ግን ከዓመታት በፊት እንደተደረገው በሠብዓዊ ድጋፍ ሰበብ በመግባት በእርዳታ ማሰባሰብ ስም መክበር የሚሻ ሃይል እንዳለ ጠቁመዋል። ከዚህ ባሻገር ቀጣናውን ወደ ትርምስ ለማስገባት የሚሹ የጦር መሳሪያ ነጋዴዎች ፍላጎት እንዳለም ገልጸዋል።

More stories

“ትህነግ ከጁንታነትም ወርዶ በየጫካው ተሹለክላኪ የእህል ሌባ ሆኗል፣ ከያለበት እየታደነ ነው “ሜ/ጀ መሐመድ ተሰማ

April 7, 2021

የመ/ሰራዊትን መለያ ለብሶ ከሱዳን ወደ ወልቃይት ሊገባ የነበረ የትህነግ የሽብር ሃይል ተደመሰሰ፤ አንገታቸው የተቀላ መኮንኖች ፊልም ሊታዩ ነው

May 13, 2021

ከሱዳን የተነሳ የትህነግ ሃይል (ሳምሪ) ሳይዋጋ ሙሉ በሙሉ ተማረከ

August 11, 2021

የመንግስት ማጅራት መቺዎች ፈተና ሆነዋል – ሃላፊዋ አምነዋል

May 9, 2022

የሕግ ማስከበር ዘመቻው በጥፍነት በመጠናቀቁ ተስፋ የቆረጠ ሃይል መኖሩን የጠቀሱት አምባሳደር ዲና፤ በተለያየ ጊዜ ኢትዮጵያ ላይ ተጽዕኖ እንዲያርፍባት የሚሹ መኖራቸውን ጠቅሰል።

በዚህም ቀድሞውኑ የፔሮል ተከፋይ የነበሩ ታዋቂ ሰዎችን፣ የሚዲያ ባለሙያዎችና በሠብዓዊ መብት ተሟጋች ስም የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን ያካተተ ፕሮፓጋንዳ የሚነዛ ሃይል መኖሩንም ጠቁመዋል።

የኢትዮያ ሠላም ለአሜሪካም ሆነ ለአውሮፓ ጠቃሚ እንደሆነ ገልጸው፤ ‘በኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ ይጣላል’ በሚል የሚነዙትም የፔሮል ተከፋይ ግለሰቦች መሆናቸውን ተናግረዋል።

ያም ሆኖ ነባራዊ ሁኔታውን ዲፕሎማቶችና ሚዲያዎች በመታየቱ፤ የአውሮፓና አሜሪካ ተጽዕኖ ይቀጥላል የሚል እምነት እንደሌላቸው ቃል አቀባዩ አብራረተዋል።

በኢትዮጵያ በኩል የተዛባ ምልከታ የነበራቸውን ወገኖች ነባራዊ ሁኔታውን የማስረዳት ዲፕሎማሲያዊ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።

በዚህም በሣምንቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከተለያዩ አገራት አቻዎቻቸውና አምባሳደሮች ጋር መወያየታቸውን፤ በአዲስ አበባ የሚገኙ የአገራት አምባሳደሮች በትግራይ ክልል በአካል ተገኝተው ሁኔታውን መመልከታቸውንና እርዳታ ለማድረግ አዎንታዊ ምላሽ መስጠታቸውን ጠቅሰዋል።

በተለያዩ አገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ አምባሳደሮችም ለሚመለከታቸው አገራት መንግስታት የማስረዳት የዲፕሎማሲ ስራዎች ማከናወናቸውን ተናግረዋል።

በትግራይ ክልል ከ4 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ለሆኑ ዜጎች የመጀመሪያ ዙር ምግብና ምግብ ነክ ሠብዓዊ ድጋፍ መቅረቡንና በቀጣይ ምዕራፍ ድጋፍ የሚሹ ዜጎችን የመለየት የዳሰሳ ጥናት እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ከተለያዩ አገራት ዜጎች እየተመለሱ መሆኑን፤ ከሳዑዲ ዓረቢያ ጂዳ ብቻ 888 ዜጎች ባለፈው ሣምንት መመለሳቸውን አስታውሰዋል።

በየመን ሰንዓ እስር ቤት በደረሰው የእሳት አደጋም ሕይወታቸው ካለፈ 43 ሰዎች መካከል ኢትዮጵያዊያን እንዳሉበት ገልጸው፤ በየመን ኤደን የሚገኙ ከ150 በላይ ዜጎች ዛሬ እንደሚመለሱም ጠቁመዋል።

በአሜሪካና በአውሮፓ አገራት ኢትዮጵያዊያን ለአገራቸው ብሔራዊ ጥቅም ወግነው ያካሄዱት የድጋፍ ሠልፍ የሣምንቱ አበረታች ክስተት እንደነበረ በመግለጽ ምስጋና አቅርበዋል።

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሶሰትዮሽ ድርድርን በተመለከተም ሱዳንና ግብፅ አራት አደራዳሪ ወገኖች ይግቡ በሚል ያቀረቡትን ሃሳብ በተመለከተ ለኢትዮጵያ በይፋ እንዳልቀረበላት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ የሶስትዮሽ ድርድር የሚቋጨው በሶስቱ አገራት እንጂ በአደራዳሪዎች እንዳልሆነ የገለፁት ቃል አቀባዩ፤ “የአደራዳሪ ሚና ማስተባበር እንጂ ማጉረስ አይደለም” ብለዋል።

“ለአፍሪካ ኅብረት ትልቅ ክብር አለን፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካን ችግር በአፍሪካ የመፍታት ፅኑ አቋም አላት” ነው ያሉት።

“ኢትዮጵያ ለድርድር ሁሌም ዝግጁ ናት” ያሉት አምባሳደር ዲና፤ የውሃ ሙሌቱም በታቀደለት መንገድ እንደምትፈጽም፣ ድርድሩም “ከሙሌቱ በፊትም ቢሆን ቢቋጭ ኢትዮጵያ ችግር የለባትም” ብለዋል።

ሱዳንና ግብጽ በሶስትዮሽ ድርድሩ ከአፍሪካ ኅብረት በተጨማሪ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአውሮፓ ኅብረትና አሜሪካ እንዲገቡ ፍላጎት እንዳላቸው ማስታወቃቸው ይታወሳል።

ENA

    NEWS
    FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
    Ethiopia, China State Ministers Hold Consultations on Wide-ranging Issues
    ደብረጽዮን እንደጻፉት በማስመሰል በእንግሊዛዊቷ ተዘጋጅቶ ለአፍሪካ ህብረት የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤት ሊላክ የተዘጋጀ ደብዳቤ መያዙ ተሰማ
    Related posts
    • Related posts
    • More from author
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    News

    ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

    April 13, 2026
    Load more
    Read also
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    WORLD

    ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    WORLD

    አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

    April 26, 2026
    WORLD

    የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

    April 26, 2026
    WORLD

    የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

    April 26, 2026
    Load more
    Recent Posts
    • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
    • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
    • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
    • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
    • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
    • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
    • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
    • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
    • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
    • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
    • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
    • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
    • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
    • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
    • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
    Social networks
    FacebookLikes
    X TwitterFollowers
    PinterestFollowers
    InstagramFollowers
    YoutubeSubscribers
    VimeoSubscribers
      VOE - VOICES OF ETHIOPIA
      The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

      MENU

      NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
      © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
      • CONTACT
      • law
      • INTERVIEW
      • ያበደው
      • ECONOMY
      • Home demo times
      • VOE VIDEO
      • ENGLISH PAGE
      • Home Demo default 2