Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  የፌዴራል ፖሊስን ልብስ ለብሰውና የፖሊስ መኪና ይዘው ወንጀል በመፈጸማቸው ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት ግለሰቦች እንዲከላከሉ ብይን ተሰጠ
law

የፌዴራል ፖሊስን ልብስ ለብሰውና የፖሊስ መኪና ይዘው ወንጀል በመፈጸማቸው ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት ግለሰቦች እንዲከላከሉ ብይን ተሰጠ

Ethioreview newsEthioreview news—March 26, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

1ኛ.ሻምበል ሁሴን መሀመድ፣ 2ኛ. ሃይሎም ገብሬ አስረስ፣ 3ኛ. ተመስገን ተወልደመድህን እና 4ኛ. ሀይሉ ገብረሩፋኤል የተባሉት ተከሳሾች በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀጽ 32 (1) ሀ እና 671 (1) ለ ላይ የተደነገገውን ድንጋጌ በመተላለፍ ካልተያዙ ግብራበሮቻቸው ጋር በመሆን ታህሳስ 25 ቀን 2013 ዓ.ም በግምት ከጠዋቱ 3፡00 አካባቢ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው ኒያላ ሞተርስ ኮርፖሬሽን ጀርባ በተለምዶ ወለጋ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተከሳሾቹ የፌዴራል ፖሊስ ሙሉ የደንብ ልብስ ለብሰውና የሰሌዳ ቁጥሩ ፖሊስ 0606 ኢ/ት መኪና ይዘው በማሽከርከር ወንጀሉን ለመፈጸም ወዳሰቡት ስፍራ ተጉዘዋል፡፡ቦታው ላይ እንደደረሱም የግል ተበዳይ ወ/ሮ ነጻነት መሳፍንት እና አቶ ዲሪዮ ሞሬሎ መኖሪያ ቤት በቀጥታ ያመሩ ሲሆን የያዙትን መኪና ጡሩንባ በመንፋት በር እንዲከፈትላቸው ያደርጋሉ፡፡

4ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክርም የመኪና ጡሩንባውን በመስማቷ በሩን የከፈተች ሲሆን ተከሳሾቹ ምስክሯን ገፍትረው ወደ ውስጥ በመግባት ሻምበል ሁሴን የተባለው 1ኛ ተከሳሽ 1ኛ እና 4ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን በመያዝና በማሰር በሀይል እየጎተተ ገንዘብ ያለበትን ቦታ እንዲያሳዩት ሲያደርግ 2ኛ ተከሳሽ ሽጉጥ ይዞ ዶላር፣ መሳርያ እና የካዝና ቁልፍ አምጡ ብሎ በማስፈራራት የተቀበላቸው ሲሆን 3ኛ ተከሳሽ 1ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክርን ጸጉር ጨምድዶ በመደብደብ ይዛው የነበረውን ቴን ፕላስ ሳምሰንግ ጋላከሲ ወስዷል፡፡ ሌላው ለጊዜው ያልተያዘው ግብራበራቸውም በያዘው ሴንጢ ቤት ውስጥ የነበረውን ኮመዲኖ (ብፌ) በመፈልቀቅ ውስጡ የነበረውን 50 ሺ ብር፣ የአንገት ሀብል፣ የጆሮ ወርቅ፣ የእጅ ብራስሌት በአጠቃላይ 47 ግራም 21 ካራት የወርቅ ጌጣጌጦችን የዋጋ ግምታቸው 93.000 (ዘጠና ሲስት ሺ) ብር የሚያወጡ አውጥቶ ሲወስድ

4ኛ ተከሳሽ 1ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክርን የደህንነት ካሜራ ሰርቨር የት እንዳለ እንድታሳየው አስፈራርቶ እንድታሳየው ካደረገ በኋላ ለጊዜው ያልተያዘው ግብራበራቸው የዋጋ ግምቱ 50 ሺ ብር የሚወጣ የደህንነት ካሜራ መረጃ ቋቱን ነቅሎ ወስዷል፡፡

3ኛ ተከሳሽ ተመስገን ተወልደመድህን በበኩሉ የገንዘብ ማስቀመጫ ካዝናውን በመክፈትና ውስጥ የነበረውን 459.000 ብር፣ የዋጋ ግምቱ 1 ሺ ብር የሆነ ሁለት ዋሌት የኪስ ቦርሳ፣ የዋጋ ግምታቸው 12 ሺ ብር የሆነ የተለያየ ብራንድ ያላቸውን አራት ሽቶዎች፣ 1 ሳምሰንግ ኤስ ቴን፣ 2 ኤች ፒ ላፕቶፕ፣ ስድስት የተለያየ ማርክ ያላቸው የእጅ ሰዓቶች በአጠቃላይ የዋጋ ግምታቸው 269.000 ብር የሆነ ንብረት እና በብር ሲመነዘሩ 302,000 የሆኑ የተለያዩ አገራት ገንዘቦችን እንዲሁም ንብረትነቱ በግሪን ላንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ስም የተመዘገበ እና የግል ተበዳይ ወ/ሮ ነጻነት መሳፍንት የምታሽከረክረው ግቢ ውስጥ ቆሞ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ 3-51797 አ/አ የዋጋ ግምቱ 3 ሚሊዮን ብር የሆነውን ጂፕ መኪና ቁልፍን ከተበዳይ ላይ በሀይል በመውሰድ መኪናን አስነስተው ወስደዋል፡፡ተከሳሾቹ በአጠቃላይ የዋጋ ግምታቸው 4.114.240 (አራት ሚሊዮን አንድ መቶ አስራ አራት ሺ ሁለት መቶ አርባ) ብር ዋጋ ያለውን ንብረቶችንና ጥሬ ገንዘቦችን ወስደው ተሰውረዋል በሚል ጥቆማ የደረሰው ፖሊስ ባደረገው ጠንካራ ክትትል ሊያዙ ችለዋል፡፡

More stories

ግማሽ ሚሊየን ብር በጥሬው ሲቀበል እጅ ከፍንጅ የተያዘው ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ

February 1, 2022

ዐቃቤ ህግ በቀድሞ የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የክስ መዝገብ ሌሎች ድርጅቶችን አካቶ ለመቅረብ ጠየቀ

July 7, 2023

በሰሜን ኢትዮጵያ ባለው ግጭት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመመርመር የተቋቋመው የሚኒስቴሮች ግብረ-ሀይል ስራውን በይፋ ጀምሯል

November 29, 2021

ሰው በማገት ወንጀል የተከሰሱ ሁለት ግለሰቦች 22 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት ተፈረደባቸው

February 16, 2022

በዐቃቤ ህግ በበኩሉ የምርመራ ሂደቱን በመምራትና ተገቢውን ክትትል በማድረግ እንዲሁም ተከሳሾቹ የፈጸሙትን ወንጀል የሚያረጋግጡ አስፈላጊ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች እንዲሰባሰቡ በማድረግ ተከሳሾች በፈጸሙት በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ከባድ የውንብድና ወንጀል ክስ መስርቶ ስልጣኑ ላለው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ላከ፡፡በዚህም መሰረት ተከሳሾች ድርጊቱን አልፈጸምንም ብለው ክደው ቃል የሠጡ መሆኑን ተከትሎ ዐቃቤ ህግ ማስረጃዎቹን አቅርቦ አሰምቷል፡፡ ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው ፍርድ ቤትም ዐቃቤ ህግ ያቀረባቸው ማስረጃዎች እንደ ክሱ ያስረዱ በመሆኑ ተከሳሾች እንዲከላከሉ ብይን ሰጥጦ የተከሳሾችን መከላከያ ምስክር ለመስማት ቀጠሮ ይዟል፡፡ውድ የፌስ ቡክ ገጻችን ተከታታዮች የዚህን ክስ ሂደት ተከታትለን መረጃዎችን የምናደርሳችሁ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

SOURCE – FDRE Attorney General

  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

law
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ስዊዝ ካናል ወድቃ የዘጋችው 400ሜትር የምትረዝመው መርከብ በፍጥነት ልትነሳ አለመቻሏ ከፍተኛ ቀውስ አስከተለ
The US Department of Defense did not announce an airstrike on Ethiopia
Related posts
  • Related posts
  • More from author
law

ህገወጥ የውጭ ምንዛሪ ወንጀል የፈጸሙ 123 ተጠርጣሪዎች የባንክ ሒሳብ ታገደ

September 20, 2025
law

እነ ቀሲስ በላይ በሙስና ወንጀል ሊፈርድባቸው እንደማይገባ ጠቅሰው ያቀረቡት ይግባኝ ውድቅ ሆነ

July 26, 2025
law

የአዲስ አበባ የከንቲባ ፅ.ቤት ፕሮቶኮልን ጨምሮ 12 ተከሳሾች በሌብነት ተከሰው ተፈረደባቸው

July 23, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2