በኤርትራና በኢትዮጵያ የተፈጸመው የዕርቅ ሂደትን ሰላም መምጣቱ ያላስደሰታቸው አሜሪካ እና የቀድሞ ቅኝ ገዢዎች (አውሮፓ ሕብረት) በህዋሃት በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እየፈጠሩ መሆኑን እያየነው ነው። ቢሆንላቸው ጠ/ሚሩን ለማስወገድ ወይም አደጋ ላይ ለመጣል የሚችሉትን ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይሉ እናውቃለን። አፍሪካ ውስጥ በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም እና አንድነት እንዲጠናከር አይፈለግም። በአፍሪካ ምድር የቅኝ አገዛዝ ዘመን ካበቃ በኋላ ሃያ ዘጠኝ ሰላም ወዳድና ለሃገራቸው ህዝብ የቆሙ መሪዎች በአሜሪካና ሌሎች ውጪ ሃይሎች ጣልቃ ገብነት ተገድለዋል።
ልጅ ግሩም ( ፒኤችዲ)
እርቅ፣ ሰላም እና ትብብር የሚል ሀሳብ ስለፈለገ ብቻ ነው። ግብፅን እንደ ምሳሌ እንመልከት፡-ግብፃውያን ከእስራኤል ጋር አራት ጊዜ ታላላቅ ጦርነቶችን አካሂደዋል፡፡ እስከ መጀመሪያው የግብፅ አብዮት መሪ ጋማል አብድል ናስር አስተዳደር ድረስ ከእስራኤል ጋር ሦስት ጦርነቶች ተካሂደዋል፡፡
ፕሬዝዳንት አንዋር ሳዳትንም አራተኛውን ጦርነት ተሸንፈው በኋላ ግን ፊታቸውን ወደ ሰላም አዞሩ፡፡ የዛሬ 40 ዓመት ገደማ በዘመኑ ብዙዎችን ያስገረመ ያስደነቀም ያልተጠበቀም ነገር አደረጉ፡፡ የሰላም እና እርቅ ንግግር ለማድረግ ወደ እስራኤል አቀኑ፡፡
ከዘመኑ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ሜኒያሂም ቤጊን ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተው በመነጋገር የመጀመሪያው አረብ ሆኑ። በጊዜው ለፍልስጤማውያን ተቆርቋሪዎች ነን ይሉ የነበሩ የአረብ አገሮችና ሌሎች ሳዳትን በከሃዲነት አብጠለጠሏቸው፡፡
ሰላምን መምረጣቸው የተቀረውን ዓለም አድናቆት አተረፉ፣ ተወደሱ፣ ተሞገሱበት፡፡ እስራኤል በስድስቱ ቀን ጦርነት ከግብፅ የነጠቀችውንና በኋላም ያስፋፋችውን የሲናይ ግዛት ለግብፅ መለሰች። ፕሬዝዳንት ሳዳት የኖቤል የሰላም ሽልማት (1978) አሸናፊ ሆኑ፡፡ ከሶስት በኋላ ዓመታት በኋላ (October 6, 1981) በካይሮ በአንድ የሠልፍ ስነ-ስርዓት ላይ በህዝብ ፊት መድረክ ላይ ተቀምጠው እያሉ ተተኩሶባቸው ተገደሉ። በተመሳሳይ ስሌት ሰኔ 16 ቀን በመስቀል አደባባይ የተከሰተውን እናስታውሳለን።
በኤርትራና በኢትዮጵያ የተፈጸመው የዕርቅ ሂደትን ሰላም መምጣቱ ያላስደሰታቸው አሜሪካ እና የቀድሞ ቅኝ ገዢዎች (አውሮፓ ሕብረት) በህዋሃት በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እየፈጠሩ መሆኑን እያየነው ነው። ቢሆንላቸው ጠ/ሚሩን ለማስወገድ ወይም አደጋ ላይ ለመጣል የሚችሉትን ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይሉ እናውቃለን። አፍሪካ ውስጥ በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም እና አንድነት እንዲጠናከር አይፈለግም። በአፍሪካ ምድር የቅኝ አገዛዝ ዘመን ካበቃ በኋላ ሃያ ዘጠኝ ሰላም ወዳድና ለሃገራቸው ህዝብ የቆሙ መሪዎች በአሜሪካና ሌሎች ውጪ ሃይሎች ጣልቃ ገብነት ተገድለዋል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ እስከታተመ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድንገተኛ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች ስህተት”… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






