የህወሓት ታጣቂ ኃይሎች በትግራይ በሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞች ላይ የሚያደርሱትን ጥቃት እንዲያቆሙ አሜሪካ አሳሰበች በትግራይ ክልል በሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞች ላይ በህወሃት ታጣቂዎች እየደረሰባቸው ያለው ጥቃት እና ማስፈራራት እንዲቆም የአሜሪካ መንግሥት አሳሰበ።
በትግራይ በሚገኙ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች ስደተኞች በአሸባሪው የህወሓት ቡድን እየተገደሉ፣ እየተደፈሩና ንብረታቸው እየተዘረፈ መሆኑን የማይፀምሪ ስደተኞች መጠለያ ጣቢያ አስተባባሪ አቶ ስንታየሁ በሪሁን ባለፈው ሳምንት ለኢዜአ መግለጻቸው ይታወቃል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ እየተሰነዘረ ያለው በህወሓት ታጣቂ ኃይሎች እና በትግራይ ሚሊሻ አባላት እንደሆነም ገልጿል፡፡
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቃል አቀባይ ጄሊና ፖርተር እንዳሉት በትግራይ በሚገኙ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ በሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞች ላይ እየደረሱ ያሉትን ዛቻ እና ጥቃቶች የሚገልጹ ተጨባጭ ሪፖርቶች እንደደረሰው ገልጸው፤ጥቃቱ በአፋጣኝ እንዲገታም አሳስበዋል።
በአሸባሪው ቡድን በየቀኑ የሚፈጸሙ በአሰቃቂ ታሪኮች የተሞሉ አሳማኝ ማስረጃዎችን እንደሚቀበል የገለጸው፤ ኮሚሽኑ ሰሞኑን በማይ አይኒ ካምፕ አንድ ስደተኛ በህወሃት ታጣቂዎች የተገደለ ሲሆን ግድያው ከ15ቀናት ወዲህ የተደረገ ሌላኛው ጥቃት መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ባወጣው መረጃ ይፋ አድርጓል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ጄሊና “ትግራይ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ሁሉም ታጣቂ ኃይሎች ኤርትራውያን ስደተኞች ላይ ጥቃት ከመፈጸም እንዲሁም ዛቻ ከመሰነዘር እንዲያቆሙ እንጠይቃለን” ሲሉ መናገራቸውን ነው ሮይተርስ የዘገበው።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በትግራይ ክልል በሚገኙ ወደ 24ሺህ የሚጠጉ ኤርትራውያን ስደተኞች የሰብዓዊ ድጋፍ እንደተቋረጠባቸው መግለጹን ይታወሳል።
ኮሚሽኑ ትላንት ባወጣው ሪፖርት በትግራይ ክልል የሚገኙ በማይ አይኒ እና አዲ ሃሩሽ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች እና በአቅራቢያቸው ግጭት መኖሩን ገልጾ ሁለት ስደተኞች መገደላቸውንም አስታውቋል።
የማይፀምሪ ስደተኞች መጠለያ ጣቢያ አስተባባሪ አቶ ስንታየሁ በሪሁን ባለፈው ሳምንት በትግራይ በሚገኙ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች በአሸባሪው የህወሓት ቡድን ስደተኞች እየተገደሉ፣ እየተደፈሩና ንብረታቸው እየተዘረፈ መሆኑን ለማስተባባሪያው መረጃ መድረሱን ገልጸዋል፡፡
በትግራይ ክልል ተባብሶ በቀጠለው ግጭት በክልሉ ባሉ ሁለት የኤርትራውያን ስደተኞች ካምፖች ውስጥም በመከሰቱ የስድተኞቹን እጣ ፈንታ አሳሳቢ አድርጎታል ያለው ኮሚሽኑ 24 ሺህ የሚሆኑና በማይ አይኒና በአዲ ሃሩሽ ካምፖች ውስጥ የሚኖሩት ስደተኞች ከሰብአዊ እርዳታዎች ከመራቃቸውም በላይ የሚደርስባቸው ጥቃትና በደል ኑሮቸውን አሰቃቂ አድርጎታል ብሏል።
የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ባለፈው ሰኔ ወር ለኢዜአ እንደገለጹት በትግራይ ክልል ባለው ሁኔታ የሽመ ልባ እና ህፃፅ የስደተኞች ካምፖች ምቹ ባለመሆናቸው የተነሳ መዘጋታቸውንና ይህን ተከትሎም “አለምዋጭ” መጠለያ ጣቢያ መገንባት ማስፈለጉን ተናግረዋል ።
በሚመሰረተው ጣቢያ በነዚህ ካምፖች የነበሩና ሌሎችን ጨምሮ እስከ 20 ሺህ የሚደርሱ ስደተኞችን ተቀብሎ ለማስተናገድ መታቀዱን አቶ ተስፋሁን አስረድተዋል።
አሁን ባለው ሁኔታ አሸባሪው የህወሓት ቡድን እየፈጸመ ባለው ትንኮሳና ግጭት ለክልል ህዝብ ሆነ በክልሉ ለሚገኙ ስደተኞች ሰብዓዊ እርዳታ እንዳይደርስ በቡድኑ መንገድ መዘጋቱ እየተገለጸ ነው።
ወደ ትግራይ ሊጓጓዝ የተጫነን የእርዳታ እህል የያዙ 170 ከባድ ተሽከርካሪዎች በአሸባሪው ህወሓት አማካኝነት ጉዟቸው ተገትቶ መቆሙን የትራንስፖርት ሚኒስር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ትላንት ማስታወቁን ኢዜአ አስታውቋል።
- ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed GroupsVOA NEWS – The Ogaden National Liberation Front (ONLF) categorically rejects claims of affiliation with armed groups and reaffirms its unwavering commitment to… Read more: ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed Groups
- Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETVIn an incisive broadcast on EBC English analyzing the architectural shifts of Ethiopia’s 7th General Election, renowned scholar Professor Alemayehu G. Mariam declared… Read more: Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETV
- Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science”VOE June 06, 2026 – Although genetic engineering is a relatively new field of science—spanning no more than 40 years—it is currently transforming… Read more: Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science”
- ዶ/ር ጆቴ ታፈሰ- መድኃኒት አልባ ሕመሞችን በሳይንስ መፈወስሰዎችን – ከሞት አፋፍ መመለስቪኦኢ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም – የዘረ መል ምህንድስና (Genetic Engineering) ዕድሜው ከ40 ዓመታት የማይበልጥ አዲስ የሳይንስ ዘርፍ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት የሕክምናውን… Read more: ዶ/ር ጆቴ ታፈሰ- መድኃኒት አልባ ሕመሞችን በሳይንስ መፈወስሰዎችን – ከሞት አፋፍ መመለስ
- ኬሞቴራፒን ማስቀረት የተቻለበት አዲስ ተስፋ፡ የ64 ዓመቷ ካረን የ«ዳግም መወለድ»ቪኦኢ ሰኔ 30 ቀን 2018 – ከካርዲፍ የመጣችው የ64 ዓመቷ አዛውንት ካረን ቦንሃም፣ የጡት ካንሰር እንዳለባት በወቀችበት ወቅት እንደማንኛውም ታካሚ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ… Read more: ኬሞቴራፒን ማስቀረት የተቻለበት አዲስ ተስፋ፡ የ64 ዓመቷ ካረን የ«ዳግም መወለድ»







