የአማራ ክልል ርዕሰ ብሄር አገኘሁ ተሻገር ለክልሉ ዓቅሙ የደረሰና ብቁ የሆኑ ወጣቶች የክተት ጥሪ አስተላለፉ። የሽብር ቡድኑ ቃል አቀባይ “ከአማራ ጋር የምናወራርደው ሂሳብ አለ” በሚል በገሃድ ከተናገሩ በሁዋላ ክልሉ ያስተላለፈው ይህ ጥሪ ከዳር እስከዳር ንቅናቄ ፈጥሯል።
“በክልሉ ውስጥ የማንኛውም የመንግሥትን መሳሪያ የታጠቀ፣ የግል መሣሪያ የታጠቀ፣ ለግዳጅ ብቁ የሆነ ወጣት ሁሉ ከነገ ጀምሮ ለህልውና ዘመቻ እንዲዘምት የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አገኘሁ ተሻገር የክተት ጥሪ አስተላለፉ” ሲል ነው የክልሉ ሚዲያ ይፋ ያደረገው።
አሜሪካ በኢትዮጵያ መፍንቅለ መንግስት አካሂዳ ትህነግን በመሪነት ለማስቀመጥ እላይ ታች በምትልበት ወቅት የአማራ ክልል ” ለህልውና ዘመቻ ክተት” ማለቱ ስጋት ፈጥሯል።
የትህነግን ምርጫ በብቸኝነት የታዘቡት የኖርዌይ ተወላጅ ፕሮፌሰር ሼትል የአማራ ክልል ይህን ዜና ይፋ ባደረገ ደቂቃዎች ውስጥ በቲውተራቸው አማራ መሳሪያ ያለው ሁሉ ከነገ ጀምሮ ወደ ጦር ግንባር እንዲዘመት መተራቱን ጠቅሰው፤ የሲቪል ጦርነት እንደሚቀሰቀስ ጠቁመዋል። የአቶ አገኘሁ ተሻገርን ምስልና ጥሪ አትመው ለነጮቹ ባሰራጩት መልዕክት ማሳረጊያ እንደተለመደው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ወቅሰዋል።
ዜናው እንደተሰማ በቀጥታ የተላከላቸው የውጩ ማህበረሰብ እንዲያሰራጩ ሲሆን ሰውየው ከቀናት በፊት መንግስት እንደሚገለበጥ የሚያትት ጽሁፍ በማጋራት ” አዳዲስ ተተኪዎቹ ይዘጋጁ” የሚል ሃሳብ አሰራጭተው ነበር።
አዲስ አበባን ጨምሮ በመላው አገሪቱ ሕዝብ ለመንግስት ድጋፍ እየሰጠ ባለበት፣ ትህነግን እንደማይፈልግ እያወገዘ ድምጹን በሚያሰማበት በአሁኑ ወቅት አሜሪካ ኢትዮጵያ ላይ ለመጫን ያሰበችው ሃይል ተቀባይነት እንደማይኖረው፣ ክልሎች ጭራሹኑ ጆሮ እነደማይሰጡት አለመረዳቷ አስገራሚ እንደሆነ ተመልክቷል።
የአማራ ክልል ራሱን በነባር የጦር መኮንኖች ካደራጀ በሁዋላ ለህልውና ዘመቻው እንደሚነሳ ብ/ጄነራል ተፈራ መናገራቸው አይዘነጋም። አዲሱ የልዩ ሃይል አዛዥ እንዳሉት ዘመቻው ስር ነቀለና ትህነግን ለመቸረሻ ጊዜ የሚነቅል ነው።
ትህነግ በትግራይ የሰለጠኑ 250 ሺህ ወታደሮችና አንድ ሚሊዮን በላይ ሚሊሻና ለክተት የተዘጋጀ ሃይል፣ እንዲሁም እጅግ በርካታ ሕጻናትን መልምሎ ውጊያ ላይ ቢያሰልፍም አሜሪካን ጨምሮ ኢትዮጵያ ላይ ውርጅብኝ የሚያወርዱት አገራት ምንም ያሉት ነገር የለም። ይህን በማስረጃ የተደገፈ ጉዳይ በዝምታ ያለፉት አገራቱ የአማራ ህዝብ “ለህልውና” በሚል የጠራውን ክተት ተከትሎ የተለያየ መግለጫና የውግዘት ማሳሰቢያ እንደሚያወጡ ይጠበቃል።
አብዛኞች የሰላም አማራጭ እንዲፈለግ እየወተወቱ ቢሆንም ታላላቁ አገራት መንግስት ለመገልበጥ ከትህነግ ጎን መሰለፋቸው ችግሩን አሳዛኝና ውስብሰብ እንዳደረገው እየተገለጸ ነው።
- 𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨𝐩𝐢𝐚 𝐚𝐧𝐝 𝐍𝐢𝐠𝐞𝐫𝐢𝐚 𝐃𝐞𝐞𝐩𝐞𝐧𝐏𝐚𝐫𝐭𝐧𝐞𝐫𝐬𝐡𝐢𝐩 𝐭𝐡𝐫𝐨𝐮𝐠𝐡 𝐁𝐢𝐥𝐚𝐭𝐞𝐫𝐚𝐥 𝐓𝐚𝐥𝐤𝐬 𝐚𝐧𝐝 𝐋𝐞𝐠𝐚𝐥 𝐂𝐨𝐨𝐩𝐞𝐫𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 𝐀𝐠𝐫𝐞𝐞𝐦𝐞𝐧𝐭VOE NEWS – Minister of Foreign Affairs Gedion Timothewos today held discussions with the Minister of Foreign Affairs of the Federal Republic… Read more: 𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨𝐩𝐢𝐚 𝐚𝐧𝐝 𝐍𝐢𝐠𝐞𝐫𝐢𝐚 𝐃𝐞𝐞𝐩𝐞𝐧𝐏𝐚𝐫𝐭𝐧𝐞𝐫𝐬𝐡𝐢𝐩 𝐭𝐡𝐫𝐨𝐮𝐠𝐡 𝐁𝐢𝐥𝐚𝐭𝐞𝐫𝐚𝐥 𝐓𝐚𝐥𝐤𝐬 𝐚𝐧𝐝 𝐋𝐞𝐠𝐚𝐥 𝐂𝐨𝐨𝐩𝐞𝐫𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 𝐀𝐠𝐫𝐞𝐞𝐦𝐞𝐧𝐭
- Egypt and Eritrea Ink Maritime and Security Deals: What It Means for EthiopiaVOE NEWS CAIRO — Egyptian President Abdel Fattah el-Sisi and visiting Eritrean President Isaias Afwerki have agreed to launch practical cooperation programs… Read more: Egypt and Eritrea Ink Maritime and Security Deals: What It Means for Ethiopia
- ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed GroupsVOA NEWS – The Ogaden National Liberation Front (ONLF) categorically rejects claims of affiliation with armed groups and reaffirms its unwavering commitment… Read more: ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed Groups
- Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETVIn an incisive broadcast on EBC English analyzing the architectural shifts of Ethiopia’s 7th General Election, renowned scholar Professor Alemayehu G. Mariam… Read more: Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETV
- Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science”VOE June 06, 2026 – Although genetic engineering is a relatively new field of science—spanning no more than 40 years—it is currently… Read more: Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science”








