ሀምሌ 10/2013 (ኢዜአ) ጨፌ ኦሮሚያ በክልሉ የፍትህ ተደራሽነትና ትክክለኝነትን ለማረጋገጥ ያግዛል ላለው የባህላዊ ፍርድ ቤቶች ምስረታ እውቅና የሚሰጥ አዋጅ አጸደቀ።
ጨፌው የ2014 የክልሉ በጀት 124 ቢሊዮን ብር እንዲሆን አጽድቋል።
ጨፌ ኦሮሚያ እያካሄደው የሚገኘው 14ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛ ቀኑ የባህላዊ ፍርድ ቤቶች ምስረታ እውቅና የሚሰጥ አዋጅን ማጽደቅን ጨምሮ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል። ባህላዊ ፍርድ ቤቶቹ ከቀበሌ ጀምሮ የሚመሰረትና የክልሉ ሕዝብ በቀደመው ባህሉና ወጉ መሰረት ፍትህ እንዲያገኝ ያግዛል ነው ተብሏል።
ፍርድ ቤቶቹ በተለይ በመደበኛ ፍርድ ቤቶች በፍትህ አሰጣጥ ሂደቱ ላይ ፈተና የሆነውን ሀሰተኛ ምስክርነት ለመቀነስ እንደሚረዳም ተገልጿል። በዋናነት የክልሉ ሕዝብ የቀደመ ባህላዊ የፍትህ አሰጣጥ ሂደትን ተከትሎ የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን ለመፍታት ያስችላልም ተብሏል።
ረቂቅ አዋጁን ያቀረቡት የህግ ተመራማሪው አቶ ሚልኪ መኩሪያ እንደሚሉት ፍርድ ቤቶቹ የፍትህ ተዳራሽነትን የበለጠ ያጠናክራሉ። ከዚህ በፊት በአብዛኛው የክልሉ ነዋሪዎች ፍትህ ለማግኘት ረጅም ጉዞ በማድረግ ለአላስፈላጊ ወጪ ይዳረጉ ነበር ነው ያሉት።
በአዋጁ መሰረት የሚቋቋሙ ፍርድ ቤቶች የክልሉ ሕዝብ ፍትህን በቅርበትና በእውነት ላይ ተመስርቶ እንዲያገኝ ይረዳዋል ብለዋል። ፍርድ ቤቶቹ የመጀመሪያና በፍርድ ሂደቱ ያልረካው አካል አቤት የሚለበት ሁለተኛ እርከን ፍርድ ቤት እንዲኖረው ሆኖ እንደሚደራጅም ገልጸዋል።
ከዚህ ባለፈ ባህላዊ ፍርድ ቤቶቹ አምስት አባላት ያሉትና አባላቱም ለስምንት አመታት የሚያገለግሉ እንደሚሆኑ ተናግረዋል። እነዚህ ፍርድ ቤቶች ከመደበኛና ከማህበራዊ ፍርድ ቤቶች ጎን ለጎን የሚሰሩ ሲሆን ለክልሉ ህዝብ ትልቅ ጥቅም የሚሰጡ እንደሆነም ገልጸዋል።
በዚሁ መሰረት አዋጁ በጨፌው አባላት በሙሉ ድምጽ ጸድቋል። በተመሳሳይ ጨፌው የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አዳምጦ ከተወያየበት በኋላ ሪፖርቱን በሙሉ ድምጽ አጽድቆታል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ የኦሮሚያ ክልል የአስር ዓመት እቅድ ላይ ሰፊ ውይይት አድርጎ እቅዱን አጽድቆታል። በመጨረሻም የጨፌ ኦሮሚያ ምክር ቤት የክልሉን ኦዲተር ጀነራል እቅድ አፈጻጸም፣ የ2013 ዓ.ም ተጨማሪ በጀት እንዲሁም የ2014 ዓ.ም በጀት ላይ ውይይት በማድረግ አጽድቆታል።
በዚህም የክልሉ የ2014 በጀት 124 ቢሊዮን ብር ለካፒታልና ለተለያዩ ወጪዎች እንዲውል አጽድቋል። በጀቱ 19 ቢሊዮን ብር ለተለያዩ ወጪዎች፣ 29 ቢሊዮን ለካፒታል በጀትና 73 ቢሊዮን ብር ለወረዳዎችና ለከተማ አስተዳደሮች ድጋፍ እንዲሁም 600 ሚሊዮን ብር ለተጠባባቂ በጀት ተይዟል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ እስከታተመ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድንገተኛ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች ስህተት”… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
- የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?ቪኦኢ ዜና – በአዲስ መልክ እየተሳለ ያለው የዓለም የንግድ ካርታ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል የዓለም የኢኮኖሚ ሥርዓት በአንድ ያልተጻፈ ሕግ ላይ የቆመ ነበር፤ እርሱም… Read more: የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?







