Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የሕወሓት መመለስ አንድምታ
News

የሕወሓት መመለስ አንድምታ

Ethioreview newsEthioreview news—July 2, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በተዋጊዎቹ ወዲያና ወዲህ፣ በደጋፊነት ወይም በተቃዋሚነት የተሰለፉ ሰዎች የኢትዮጵያ መንግሥት የተናጠል ተኩስ አቁም ያወጀው የምር ለሕዝቡ አዝኖ ነው ወይስ ተሸንፎ በሚለው ጉዳይ እየተከራከሩ ነው። 

የሕወሓት መመለስ አንድምታ

በፍቃዱ ኃይሉ

የኢትዮጵያ መንግሥት እና የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ጦርነት ባለፉት ሦስት ዓመታት ከተፈጠሩ ፖለቲካዊ ቀውሶች ሁሉ ግዙፉ ነው። ሕወሓት ከቀድሞዎቹ ሦስት ዐሥር ዓመታት ጭቆና እና ብሔር ተኮር ስርዓት ግንባታ ጋር ተያይዟል። ከሕወሓት ጋር አብረው ይሠሩ የነበሩት ደግሞ ሰላማዊ መፈንቅለ ሥልጣን አድርገውበት፣ ራሳቸውን ብልፅግና ፓርቲ ብለው በመሠየም እንዲሁም የቅርፅ እና የርዕዮት ለውጥ በማድረግ የማዕከላዊ መንግሥቱን ሥልጣን ተቆጣጥረዋል። 

More stories

«የቁንጥጫ ዲፕሎማሲ» የዲፕሎማሲው መንገድ መቀየር !

August 5, 2021

መልስ የሚሻ ዜግነታዊ ጥያቄ – ሻለቃ ፈይሳ ናኔቻ

May 9, 2021

… ሶርያ ከ 10 ሚሊዮን በላይ የመን 20 ሚሊዮን ህዝብ እንደተራበና እንደተፈናቀለ …

January 29, 2021

የደብረፅዮን የጦርነት ታክቲክ 22

September 12, 2022

በነዚህ ሁለት ኃይሎች መካከል የሥልጣን ሽኩቻ የተለኮሰው ገና በማለዳ ነበር። የሥልጣን ሽኩቻው የመጀመሪያው ደረጃ ድጋፍ ማሰባሰብ ነበር። ሕወሓት የትግራይ ተወላጆች እና የፌዴራሊዝሙ አፍቃሪዎችን ለማሰባሰብ ሲሞክር፣ ብልፅግና ደግሞ የሕወሓትን ተቃዋሚዎችና የተቃውሞ አጀንዳቸውን ማሰባሰቢያ አድርጓቸዋል። በመቀጠል፣ ድጋፍ ማሰባሰቡ የወታደራዊ ኃይል ወደ ማሳየት ትርዒት ተሸጋገረ፤ መቀሌ እና አዲስ አበባ በተደጋጋሚ ወታደራዊ ትርዒቶች ተጨናነቁ። በዚህ ጊዜ የመቀሌዎቹ አዲስ አበባ፣ የአዲስ አበባዎቹ መቀሌ መግባት እንደማይችሉ ሲታወቅ፥ ከሁለት አንዳቸው ካልጠፉ በስተቀር አንዳቸው ለሌላኛው እንደማይተኙ እርግጥ ሆኖ ነበር። በዚህ ወቅት ሕወሓት ወታደራዊ የበላይነት ያስጨብጠኛል በሚል ሰሜን ዕዙ ላይ ባደረገው ዘመቻ ሰበብ ጦርነቱ ተቀሰቀሰ። ይህም የመጨረሻው መጀመሪያ ሊባል ይችላል።

1) የተኩስ አቁም ወይስ ሽንፈት?

በተዋጊዎቹ ወዲያና ወዲህ፣ በደጋፊነት ወይም በተቃዋሚነት የተሰለፉ ሰዎች የኢትዮጵያ መንግሥት የተናጠል ተኩስ አቁም ያወጀው የምር ለሕዝቡ አዝኖ ነው ወይስ ተሸንፎ በሚለው ጉዳይ እየተከራከሩ ነው። ለሰብኣዊነት ነው ከተባለው የተናጠል የተኩስ አቁም እወጃው አስቀድሞ ባሉት 10 ቀናት ገደማ በርካታ ውጊያዎች እየተካሔዱ ነበር። በነዚያ ውጊያዎች የኢትዮጵያ ሠራዊት ድል የቀናው አይመስልም ነበር።  ሠራዊቱ አንድ ወታደራዊ አውሮፕላን በትግራይ ተዋጊዎች ተመትቶ ወድቋል፤ በርግጥ የኢትዮጵያ ሠራዊት የወደቀው በቴክኒክ ብልሽት ነው ብሎ አስተባብሏል። የኢትዮጵያ ሠራዊት የተኩስ አቁም ማወጅ ብቻ ሳይሆን ይዞታዎቹን፣ ከዋና ከተማይቱ መቀሌ ጭምር ለቅቆ ወጥቷል። ይህ ሲታይ ሠራዊቱ በሽንፈት “አሸባሪ” ብሎ ለጠራው ኃይል የተቆጣጠረውን ቁልፍ ቦታ ለቅቆ ለመሸሽ እንደወሰነ መገመት ይቻላል።

በተቃራኒው የትግራይ ሠራዊት ሕዳር ወር ላይ ጦርነቱ ሲጀመር በነበረው አቅሙ አይደለም። የትጥቅ ትግል መሪዎቹን አግኝተው ካናገሯቸው ቀደምት ገለልተኛ አካላት ዘገባዎች የምንረዳው፣ የመሣሪያ አቅማቸው ተዳክሟል። ማዕከላዊ የትዕዛዝ መሥመራቸው ተበጣጥሷል። ይሁን እንጂ ጦርነቱ ከሕወሓት ውጪ የሕዝብ ጦርነት ሆኗል ሊባል የሚችልበት ደረጃ ደርሷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም፣ ከጋዜጠኞች ጋር ምርጫውን አስመልክቶ በቤተ መንግሠት በነበራቸው ጊዜ ያስተላለፉት መልዕክትም ቢሆን የሚያሳየው ይህንኑ ነው።

የኢትዮጵያ ሠራዊት ተሸንፏል ማለት ግን የሕወሓት ሠራዊት አሸንፏል ማለት አይደለም። በየውጊያው ትንንሽ ድሎች ቢኖሩም በጦርነቱ ሁለቱም ወገኖች ተሸናፊ ናቸው። ሽንፈታቸው የዜሮ ድምር ውጤት ከሚባለውም የከፋ፥ የአንዱ ሽንፈት የአንዱ ድል መሆን እንኳን የማይችልበት የሁለት ወገኖች ሽንፈት የታየበት ክስተት ነው። ምክንያቱም ከተናጠል ተኩስ አቁሙ በፊት የተፈጠረው ቀውስ በረዥም ጊዜ የማይድን እና ሁለቱንም ወገኖች የሚከተላቸው ቁስል ነው። 

ሁለቱም ወገኖች ከስረዋል። አሁን የሚደራደሩት ወደ ጦርነት ከመግባታቸው በፊት ካሰቡት የተለየ ነገር ነው። ሕወሓት የበለጠ ክልላዊ ነጻነትና ቁጥጥር ከማግኘት እና የብልፅግናን መንግሥት ከማስወገድ ኅልውናውን ለማስቀጠል ወደ መፍጨርጨር ትግል ገብቷል፤ የብልፅግና መንግሥት ደግሞ የበላይነቱን ከማስጠበቅ እና ሕወሓትን ከማስገበር ይልቅ፥ በዓለም ዐቀፍ መድረክ በሰብኣዊነት ላይ የተፈፀመ ወንጀል ተከሳሽነት እና ከገጠመው የዲፕሎማሲ ቀውስ ራሱን ለማዳን እየታገለ ነው። 

2) የምሥራች ወይስ መርዶ?

የኢትዮጵያ መንግሥት የተናጥል የተኩስ አቁም አዋጅ ትግራይ ውስጥ ያለውን ቀውስ የማስታገስ ዕድሉ ትንሽ ነው። የትግራይ ገበያ ፈርሷል። መንግሥታዊ መዋቅሩም ፈርሷል። ሕወሓት በቀድሞ ቁመናው አይደለም። ምንም እንኳን ሕወሓት በትግራይ ሕዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው ቡድን ነው ቢባልም፥ ቅቡልነቱ ብቻውን እነዚህን መልሶ የመገንባት አቅም አይሰጠውም። ይባስ ብሎ ክልሉ በጦርነት ስሜት ውስጥ ባሉ ጎረቤቶች ተከብቧል፤ መጪው ጊዜ ካለፈው ይበልጥ ያስፈራል። የፌዴራል መንግሥቱም በትግራይ ሕዝብ ድጋፍ ባለማግኘቱ ቂም ቋጥሮ ከሕወሓት ጋር መከራው እንዲቀጥል የሚፈልግ ይመስላል።

አማራ እና አፋር ክልሎች “በሕወሓት መንግሥት በኃይል ተወስዶብን ነበር” የሚሉትን ግዛት እያስተዳደሩ ነው። እነዚህን ግዛቶች ለመከላከል ወደ ሌላ ጦርነት ለመግባት ዝግጁ ናቸው። ይህንንም ቢያንስ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ከተኩስ አቁም አዋጁ በኋላ በግልጽ ተናግሮታል። በሌላ በኩል ኤርትራ አለች። አምባገነኑ የኤርትራ መንግሥት ሕወሓት በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት እና በኋላ አድርሶብኛል ለሚለው በደል ማወራረጃ የትግራይ ሕዝብ ላይ የበቀል በትር እንዳሳረፈ ባለፉት ስምንት ወራት አይተናል። አሁንም የሕወሓት መሪዎች እንደዛቱት ለተጨማሪ ለዘመቻ የሚሰናዱ ከሆነ ጦርነቱ ተባብሶ መቀጠሉ አይቀሬ ነው። 

በዚህም አለ በዚያ የተዳከመው የሕወሓት ጦር መቀሌ መመለስ ለብዙኃን ተጋሩዎች ተስፋ ሰጪ ሊሆን ቢችልም፣ የሚጠበቅበትን መስጠት ይችላል የሚል እምነት ግን የለኝም። 

3) የኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ

የትግራይ ጦርነት የትግራይ ብዙኃን ከኢትዮጵያ ያቆራረጠ ነው ቢባል ማጋነን አይሆን። ፖለቲካው የእያንዳንዳቸውን የትግራይ ተወላጆችን ጓዳ በአንድም በሌላም በኩል አንኳኩቷል። ከ17 ዓመቱ የሕወሓትና የኤርትራ ሕዝቦች ነጻነት ግንባር ጦርነት ዘግናኝ ትውስታ ያልወጣው የትግራይ ሕዝብ፥ የፖለቲካ ኃያላን የሥልጣን ሽኩቻ ዳግም ሰለባ ሆኗል። ብዙዎች እንደሚገምቱት ብዙኃን የትግራይ ተወላጆች ከዚህ በኋላ ከኢትዮጵያ ጋር አንድ ላይ መቀጠል አይፈልጉም። ነገር ግን ይህ እዚህ ላይ የሚቆም አይመስልም።

የኢትዮጵያ መንግሥት ተቀባይነት አጥቷል። ቁልፍ የፌዴራል ሥልጣኖችን የተቆጣጠሩት ሰዎች የትውልድ ክልል የሆነችው ኦሮሚያ ውስጥ ከፍተኛ የተቃውሞ ስሜት አለ። የዋነኞቹ ተቃዋሚ ድርጅቶች መሪዎች ታሥረዋል፤ ምርጫ ላይ አልተሳተፉም፤ ወዘተ። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የተከፋፈለ ሲሆን፣ አንደኛው ክፋይ ትላንት ለሊት የኦሮሚያ ብሔራዊ የሽግግር መንግሥት መቋቋሙ ይታወቅልኝ ብሏል፤ ይህ መግለጫ የመጣው ሕወሓት ወደ መቀሌ መመለሱን ተከትሎ መሆኑ የአጋጣሚ አይመስልም። ይልቁንም፣ መንግሥትን በተለያዩ አቅጣጫዎች ውጥረት ውስጥ በማስገባት ወደ ሚፈልጉት “የነጻነት” አጀንዳ ሊወስዱት የፈለጉ ይመስላል። ሕወሓት የኦነግ የቀድሞ ጠላት ቢሆንም፥ አሁን ግን የአጭር ጊዜ የዓላማ አጋር ሆኗል ማለት ይቻላል። እነዚህ ቅሬታዎች እና ፖለቲካዊ ጫናዎች እያደር ሥር እየሰደዱ መሔዳቸው አይቀርም። ሆኖም፣ ቤተ መንግሥት ውስጥ እነዚህን ቅራኔዎች ከሥር፣ ከሥር፣ በብልሐት፣ በሕዝባዊ ተሳትፎ እና በንግግር ለመፍታት ዝግጁነት ያለ አይመስልም። 

ከሁሉም የፖለቲካ ቀውሶች ለመውጣት ከሁሉ አስቀድሞ የትግራዩ አንገብጋቢ ችግር መፈታት አለበት። የትግራዩን ችግር ለመፍታት መጀመሪያ ሰላምና መረጋጋት የግድ አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ነው። ይህንን የሕወሓት መቀሌ መግባት ያመጣዋል የሚል እምነት የለኝም። ቀድሞም የተዳከመው ሕወሓት በጠበኛ የትግራይ አጎራባቾች ተከብቦ ራሱንም፣ ትግራይንም መልሶ የማቋቋም አቅም የለውም። ይልቁንም የዓለም ዐቀፍ የሰላም አስከባሪ ተልዕኮ ወደ ክልሉ እንዲገባ በመፍቀድ፣ የሚገኝ ከሆነ ዘላቂ ፖለቲካዊ መፍትሔ በገለልተኛ አሸማጋዮች ለማግኘት መሞከር ብቸኛው መፍትሔ ይመስላል። የትግራዩን ቀውስ በሰላማዊ መንገድ መፍታት ከተቻለ፣ በሌሎች ክልሎች ላቆጠቆጡት ቀውሶችም ትምህርት መቅሰም ይቻል ይሆናል። 

በዚህ አምድ የቀረበው አስተያየት የጸሐፊው እንጂ የዶይቸ ቬለ (DW)ን አቋም አያንጸባርቅም። DW

OPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ምግብ በመመረዝ ሶስት ሰዎች ገለዋል የተባሉ ተያዙ፤ ፍርፍሩን የበሉ ውሻና ድመት ሞተዋል
በሰከረ ትውልድ፣በሞትና በረሃብ መቆመር ይቁም!
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2