Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ሃውጃኖ፡ የራያው መብረቅ
News

ሃውጃኖ፡ የራያው መብረቅ

Ethioreview newsEthioreview news—August 14, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በዚያ አስፈሪ ዘመን፣ እነዚያ አስጨናቂ የፖለቲካና የሴራ ጉንጉኖች ወቅት ሁሉም በቆፈን ታሥሮ፣ በፍርሃት ተወድሮ በስስ ልቡ ውስጥ ተደብቆ ነበር፡፡ የትውልድ ስብራት እና የኢትዮጵያዊነት መደብዘዝ ከ1960ዎቹ ጀምሮ በተረጨው የጥላቻና የመገዳደል የፖለቲካ ሸማ ሽምን ውጤት፤ ቅይጥ ርዕዮት፡፡

ሕወሐት ሰሜን-ምዕራብ አማራ፣ ወልቃይትን እና ሰሜን-ምሥራቅ አማራ ራያን በልቡ አልሞ፣ በዘረፋ መዳፎቹ ለማጋበስ አቆብቁቦ ቆሞ ይሠራ ነበር፡፡ በተለይ የአማራን ሕዝብ በጡንቻ በመግዛት፣ የሕዝቡን መሬትም በመቀማት ግዛት ማስፋት ግቡ ነበርና ራያን አሰፈሰፈበት፤ ጥላውንም ጣለ፡፡

ግና የአማራ ማሕጸን በየአዝማናቱ አይነትፍ-አይመክንምና የራያው መብረቅ ይርጋ አበበ ወይም በትግል ሥሙ ሀውጃኖ ትሕነግን የእግር እሳት ሆነበት፡፡

በኢትዮጵያዊነቱም አይደራደርም፣ ላመነበት ሟች፣ ታግሎ አታጋይ፣ ተኩሶ መራዥ፣ ቆራጡ ሀውጃኖ አላማጣ-ራያ ተወልዶ ደርግን ለመጣል በተደረገው እልህ አስጨራሽ ትግል በወቅቱ ወደተመሠረተው የሕወሐት ጥፍጥፍ ድርጅት ኢህዴን ተቀላቅሎ ይንቀሳቀስ ጀመር፡፡

More stories

«የቁንጥጫ ዲፕሎማሲ» የዲፕሎማሲው መንገድ መቀየር !

August 5, 2021

መልስ የሚሻ ዜግነታዊ ጥያቄ – ሻለቃ ፈይሳ ናኔቻ

May 9, 2021

… ሶርያ ከ 10 ሚሊዮን በላይ የመን 20 ሚሊዮን ህዝብ እንደተራበና እንደተፈናቀለ …

January 29, 2021

የደብረፅዮን የጦርነት ታክቲክ 22

September 12, 2022

የኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልም እስከመሆን ቢደርስምሪው የትህነግ ሐገር አፍራሽ ቡድን የሚያራምደውን ድብቅ ሴራ ፈጥኖ የተረዳው በመረዳቱ አጥብቆ መቃወም ጀመረ፡፡

ኢትዮጵያዊነትን የተላበሰው፣ አማራዊ ማንነቱን እና የማንነቱ መብቀያ ርሻ የሆነውን ርስቱን አላስነካም ያለው የጀግናው ሀውጃኖ አካሄድ ያልተዋጠላቸው የትህነግ ቡድኖች ሀውጃኖን በዓይነ ቁራኛ ይከታተሉት ጀመር፡፡ ሊያሳምኑትም ሞከሩ፤ከአቋሙ ንቅንቅ ሊልላቸው አልቻለም፡፡

በሀውጃኖ ፅኑ አቋም ያልተደሰቱት የትህነግ አባላት ከኢህዴን ማዕከላዊ ከሚቴ አባልነት እንዲታገድ አደረጉት፡፡ ከነበረው ከፍተኛ ወታደራዊ ኃላፊነትም አሳነሱት፡፡ በዚህ ማናለብኝነታቸው ሀሳቡን ሊቀይርላቸው፣ ከቆመበት የሀቅ ኮረብታ፣ የማንነት የዕውነት አምባ ፈቅ ሊል አልቻለም፡፡ እንዲያውም የህወሐትን ጉምቱ ባለሥልጣናትና የደሕንነት ሠዎች ፊት ለፊት ቀርቦ ‹‹ግንኙነታችን የድርጅት ከሆነ እኩል መሆን አለብን›› ይላቸው ነበር።

አስቀድመው የፈሩትና የተሸፈነውን አካሄዳቸውን ፈልፍሎ ያወቀ በመሆኑ ሟቹ መለስ ዜናዊ እና የዛሬው የፖለቲካ ማማሰያ አቀባይ ታምራት ላይኔ ሀገረሠላም ድረስ አስጠርተው ሊያሳምኑት ሞክረው የማይቆረጠም የብረት ቆሎ ሆኖባቸው ጥርስ ነከሱበት።

አካሄዳቸው የጋራ የሆነች ታላቅ ሀገር ለመምራት እንደማያስችልም በተደጋጋሚ ነገራቸው። ቢችሉ በመንገዳቸው እንዲሄድ ካልሆነ ግን ከመንገዳቸው ላይ እንዳይቆም ለማድረግ ወሰኑ። አማራጭ ሲያጡ ሊያስሩት ሞከሩ፤ ስለ አውነት አልታሰር አለ። በነበረው የተኩስ ልውውጥም ሀውጃኖ ተገደለ።

የራያ አማራ የተረጋጋ ሕይወት እንዳይኖር ማድረግ፤ በፈለገው ጊዜ የሚታሰር፤ የሚገረፍ፤ የሚፈናቀል ሕዝብ እንደነበር ዶክተር ሲሳይ መንግስቴ በተደጋጋሚ ምስክርነታቸውን ይሰጣሉ፡፡ ለምን ብሎ የጠየቀ ደግሞ ‹‹አካባቢውን ለቀህ ውጣ! ከመሬቱ እንጂ ከእናንተ ምንም የለንም›› እንደሚባሉም ዶክተር ሲሳይ የሀውጃኖን የትግል ጥያቄዎች አስታውሰው ይገለጻሉ፡፡

ሕጻናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዳይማሩ ማድረግ ሌላኛው የሕወሓት ሥራ ነበር። የራያ አማሮች በአማርኛ ቋንቋ እንዳይናገሩ፣ እንዳይፅፉና ሌሎችም የመከራ ቀንበር ተጭኗቸውም ብዙ የመከራ ዘመናትን አለፉ። ሕዝቡ ታፍኖ የኖረ፤ ነፃነት የጠማው ሕዝብም እንዲሆን ተገደደ፡፡

ዳሩ የሀውጃኖ እና ዕልፍ የራያ አማራ ታጋዮች መራር ትግል ዳዋ አልለበሰም፣ ንፋስ አልበተነውም፡፡ የራያ አማራ በልጆቹ ትግል ከትህነግ ነጻ ወጥቶ ወደቀደመ ማንነቱ ተመልሷል፡፡ ማንነት አይሸጥምና ከግዞት ተላቆ በራሱ ማንነት ቆሟል፡፡

ይህ ያንገበገበው አሸባሪ ዛሬም እንደትናንት የራያን አማራ ለመጨፍጨፍ፣ ለመጨቆን እና ለመዝረፍ ቢቋምጥም የዛሬዎቹ ጃውሃኖዎች ተሰልፈው ቆመዋል፡፡ ራያን ለዳግም ባርነት ‹‹ ሒሳብ ሊያወራርድ›› የሚያሰላውን ሰላቶ ሊቀብሩት በሀውጃኖ ምህላ አስረዋል፤ ቃልኪዳን ቋጥረዋል፡፡

ሀውጃኖነት በመቃብር ያልተገታ፣ የትውልድ አደራ ውል ነውና ሐውጃኖ መብረቃዊ ኃይል ዛሬም በአላማጣ፣ በቆቦ፣ በወልድያ፣ በአላውኃ፣ በላልይበላ፣ በላስታ፣ በዋግ፣ በአንጎት፣ በመርሳ፣ በውርጌሳ፣ በኃይቅ፣ በሲሪንቃ፣ በአምባሰል፣ በቦረና፣ በመቅደላ በቃሉ፣ በኮምቦልቻ እና በተዋጊዎቹ በመነን ልጆች ልብ ውስጥ አለ፡፡

ቢወለድ ጀግና እንደ ሀው’ጃኖ
ጠላት ይወቃል ከአውድማ ዘግኖ

እየተባለ ትላንት እንደገነነ፣ ዛሬ ተከብሮ ነገን ሕያውነት ለትውልዱ አልብሶ አልፏል፤ ደመላሽነቱ ግን በፍጹም አያልፍም፡፡

Via AMC

OPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በጋምቤላ ከተማ በአሸባሪዎቹ ህወሃትና ሸኔ ተላላኪነት የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
መሳሪያና ገንዘብ በቀይ መስቀል መኪና ጭነው ወደ ደቡብ ጎንደር ሰርገው የገቡ የህወሀት ተላላኪዎች ተደመሰሱ‼
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2