Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ህጋዊ መንግስትን ከአሽባሪ ቡድን ጋር እኩል ማየት ለምን?
News

ህጋዊ መንግስትን ከአሽባሪ ቡድን ጋር እኩል ማየት ለምን?

Ethioreview newsEthioreview news—September 20, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጆ ባይደን በኢትዮጵያ ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ መጣል የሚያስችል ሰነድ አዘጋጀተው ፈርመዋል። ፕሬዚደንቱ የፈረሙት የዕቀባ ትዕዛዝ ሕጋዊውን የኢትዮጵያ መንግሥት ከአሸባሪው ሕወሓት ጋር እኩል በማየት ሊደራደር እንደሚገባ የሚያትት ነው።

ከፕሬዚደንቱ ፊርማ በኋላ የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ወዲያወኑ ባወጡት መግለጫ በጦርነቱ ውስጥ ተሳታፊ የሆኑ አካላት ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ወደ ድርድር የሚመጡ ከሆነ አሜሪካ ልትጥል ያሰበችውን ማዕቀብ ለማዘግየት ዝግጁ ነች ብለዋል። ይህ መግለጫ የወጣው ኢትዮጵያ በህዝብ ድምጽ ምርጫ ተካሂዶ መንግስት ለመመስረት ሳምንት በቀሩበት ወቅት ሲሆን አንድምታው የጆ ባይደን አስተዳደር በመንግስት ላይ ከፍተኛ ጫና በማሳደር ለማስገደድና ቀደም ሲል ያሰቡትን ደካማ መንግስት መፍጠርን ዓላማ ያደረገ ነው።  

አሸባሪው ቡድን በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማይካድራ፣ ጭና፤ ጋሊኮማ፤ አጋምሳ መጨፍጨፉ፣ በርካቶችን ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ ማድረጉ፤ የሰብዓዊ ቀውስ እንዲከሰት እና እንዲባባስ ማድረጉ፤ በርካታ የእምነት ተቋማትን፣ ሆስፒታሎችን እና ትምህርት ቤቶችን ማውደሙ የባይደን አስተዳደር ከበቂ በላይ መረጃ እያለው በዝምታ አልፎታል።

በአንጻሩ የኢትዮጵያ መንግስት የአሸባሪው ህወሃት ቡድንን አጥፊ አካሄድ ከመከላከል አልፎ ቡድኑ የፈጠረውን ሰብዓዊ ቀውስ ለማስተካከል እያደረገ ላለው ጥረት እና እየሰጠ ላለው ምላሽ እውቅና አልሰጠም። የመንግስትን ጥረት የባይደን አስተዳደር ብቻ ሳይሆን መላው የዓለም ማህበረሰብ ድጋፍ እና አድናቆት ሊቸረው ሲገባ ለማዕቀብ መዘጋጀት ተላላኪ መንግስት ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ማሳያ ነው። 

More stories

«የቁንጥጫ ዲፕሎማሲ» የዲፕሎማሲው መንገድ መቀየር !

August 5, 2021

መልስ የሚሻ ዜግነታዊ ጥያቄ – ሻለቃ ፈይሳ ናኔቻ

May 9, 2021

… ሶርያ ከ 10 ሚሊዮን በላይ የመን 20 ሚሊዮን ህዝብ እንደተራበና እንደተፈናቀለ …

January 29, 2021

የደብረፅዮን የጦርነት ታክቲክ 22

September 12, 2022

ላለፉት በርካታ ዓመታት አሜሪካ በተለያዩ ሀገራት የሽብር ቡድኖችን ለማጥፋት በሚል ጣልቃ እስከመግባት የደረሰ እርምጃ ስትወስድ እንደቆየች የሚታወስ ነው። በአንዳንድ ሀገራት ለራሷም ይሁን ለሀገራቱ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ያደረሰ እርምጃ ወስዳለች። ሽብርተኛን መከላከል እና ማጥፋት የአሜሪካ ቀዳሚ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ማጠንጠኛ መሆኑን የሚያስታውሱት የዘርፉ ምሁራን ይህ በኢትዮጵያ ላይ ሲሆን ለምን ይቀየራል የሚል ጥያቄም ያነሳሉ፡፡ 

የኢትዮጵያ አሜሪካውያን የዜጎች ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ የአሜረካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከሰብዓዊ መብት ጥሰት ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ያስተላለፉትን ትዕዛዝ ሊሰርዙት ይገባል ሲል የጠየቀው በዚህ ምክንያት ነው።

ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ መንግስት በክልሉ ያለውን ሰብዓዊ ቀውስ ለመቀየር በማሰብ የተናጠል የተኩስ ማቆም ውሳኔ በወሰነበት፣ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦቱ እንዲቀላጠፍ ከዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ድርጅቶች ጋር በጥምረት እየሰራ ባለበት ይህ ውሳኔ መወሰኑ ተገቢነት እንደሌለው አመልክቷል። ከዚህ በተጨማሪ ምክር ቤቱ ሀገሪቱ አዲስ መንግስት ለመመስረት ዝግጅት እያደረገች ባለበት፣ የአፍሪካ ህብረትም ችግሩን ለመፍታት ጥረት የሚያደርግ ልዩ ልዑክ ሰይሞ እንቅስቃሴ በጀመረበት በዚህ ወቅት የባይደን አስተዳደር ይህን ውሳኔ ማሳለፉ ተቀባይነት የለውም ብሏል።

የሽብር ቡድኑ በመንግስት የታወጀውን የተናጠል የተኩስ ማቆም ውሳኔ በመጣስ በትግራይ ክልል ብቻ ሳይወሰን በአጎራባች ክልሎች እና አካባቢዎች ጦርነቱን እያስፋፋ ባለበት በዚህ ወቅት የአሜሪካ መንግስት የወሰነው ውሳኔ የኢትዮጵያን አሁናዊ ሁኔታ በሚገባ ያልተገነዘበ በመሆኑ ፕሬዝዳንቱ የወሰኑትን ውሳኔ መለስ ብለው ማየት እንደሚገባቸው ከየአቅጣጫው ግፊቶች እየተደረጉ ነው፡፡

ይህን የአሜሪካን ውሳኔ ልዩ የሚያደርገው ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባል እና አለም አቀፍ ሕግን በማክበር እና በማስከበር እንቅስቃሴ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ መሆኗ እንዲሁም የውስጥ ጉዳይን በራስ አቅም የመፍታት ሙሉ መብት ያላት ሉዓላዊት ሀገር መሆኗን የዘነጋ በሚመስል መልኩ  ከሽርተኛ ቡድን ጋር በውዴታ ሳይሆን በግዴታ መደራደር አለባችሁ ማለት ሉዓላዊነት ላይ መሳለቅ እንደሆነ የሚናገሩም አልጠፉም፡፡

ላለፉት በርካታ ዓመታት ወንዶችን ሲያኮላሽ፣ የትግራይ ልጃገረዶችን ሳይቀር ሲደፍር እና ሲያስደፍር፣ ለምስኪኑ ለትግራይ ህዝብ አንዳችም የህይወት አኗኗር ዘይቤ ለውጥ ሳያመጣ፤ ነገር ግን በስሙ ሲምል እና ሲገዘት የቆየው የሽብር ቡድኑ እየፈጸመው ያለው የሽብር ድርጊት መወገዝ ነበረበት።

የሀገሪቱን ሀብት እንደግል ንብረቱ ሲመዘብር፣ ህዝቡን በዘር ሲከፋፍል፣ በተለያዩ አካባቢዎች ሁከት እና ግድያ እንዲፈጸም በገንዘብ እና በቁሳቁስ እንዳንዴም ህጋዊ ከለላ ሲሰጥ ለኖረ በመጨረሻም ለክልሉ ህዝብ ለዓመታት ጋሻ እና ከለላ በመሆን ሲያገለግለው የቆየውን የመከላከያ ሰራዊትን ሲወጋ  የባይደን አስተዳደር ማውገዝ ሲገባው ይህን ዕኩይ ተግባር ለማስተካከል የሚጥርን ህጋዊ መንግስት ከሽብረተኛ ቡድን ጋር በእኩል አይን ማየት ለምን? ይህ ኢትዮጵያውያን በጋራ የሚያቀርቡት ወሳኝ ጥያቄ ነውና ህጋዊ መንግስትን ከሽብር ቡድን ጋር እኩል ማየቱ ከባይደን አስተዳደር የማይጠበቅና በኢትዮጵያውያን ዘንድም ተቀባይነት የሌለው ነው። 

OPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
The politics of Easy-going without Being Questioned and Challenged is Over!
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለሰባት ኩባንያዎች የከፍተኛ ደረጃ የማዕድን ምርት ፈቃድ እንዲሰጥ ተጠየቀ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2