Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ሠላም ለማምጣት የሚደረግ ድርድር ፍኖተ ካርታ በግርማ ሰይፉ ማሩዕይታ!
News

ሠላም ለማምጣት የሚደረግ ድርድር ፍኖተ ካርታ በግርማ ሰይፉ ማሩዕይታ!

Ethioreview newsEthioreview news—September 5, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ሠላም እና እርቅ ምንድን ናቸው? ሠላም እና እርቅ በአገራችን ለማምጣት የሚደረጉ ድርድሮች እንዴት መሆን ይኖርባቸዋል? በሠላምና እርቅ ዙሪያ ለዓለም ለተከሰቱ ግጭቶች መፍትሔ ሲሰጡ የነበሩ ልሂቃን ኢትዮጵያ እንዳላት እሙን ነው፡፡ አርቅ ሠላምና የማህበረሰብ ግጭቶች አፈታት በተመለከተ እንደ ፕሮፌስር ሕዝቂያስ አስፋ የመሰሉ ምሁራን አሉን፡፡

የሠላምና እርቅ ትርጉሞች እና መንገዶች የሚል መፅኃፍም አበርክተውልናል፡፡ ድርድር በየትም የሠላም ማስፈን እሣቤ ውስጥ ወንጀልን ለመደበቅ፤ ወንጀለኞችን ለማስመለጥ ወይም ከወንጀላቸው ለማንፃት የሚደረግ መድረክ አይደለም፡፡ ሠላምን ለማምጣት የሚደረግ ድርድር ፍትሕን ወደጎን አደርጎ ጎልበተኛን ማባባያ መድረክ አይደለም፡፡

አሁን አገራችን ያለችበት ወቅታዊ ሁኔታ አገራዊ ዕርቅ በማድረግ ሠላም ማምጣት፤ የዜጎችን ሞትና እንግልት ማሰቆም የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ቢሆንም፤ ይህ የሚሆነው ግን በአገር ሉዓላዊነት ላይ እየቆመሩ፤ ፍትሕን በመጨፍለቅ ወንጀለኞችን በማባባል የሚሆንበት አንደም ምክንያት ሊኖር አይገባም፡፡

More stories

«የቁንጥጫ ዲፕሎማሲ» የዲፕሎማሲው መንገድ መቀየር !

August 5, 2021

መልስ የሚሻ ዜግነታዊ ጥያቄ – ሻለቃ ፈይሳ ናኔቻ

May 9, 2021

… ሶርያ ከ 10 ሚሊዮን በላይ የመን 20 ሚሊዮን ህዝብ እንደተራበና እንደተፈናቀለ …

January 29, 2021

የደብረፅዮን የጦርነት ታክቲክ 22

September 12, 2022


ድርድር ያስፈልጋል የሚሉና የሠላም ደቀመዝሙር ካልሆንን የሚሉ አጅግ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ይሁን እንጂ አንዳቸውም ሠላም ለማምጣት የሚደረግ ድርድር የሚካሄድበትን ትክክለኛ ፍኖተ ካርታ ሳይሰጡን፤ ሠላም የሚመጣው በድፍኑ በድርድር ነው ይሉናል፡፡

ሠላም እና ድርድር የሚሉ አማላይ ቃላትን በመጠቀም ብቻ ሠላም አይመጣም፡፡ ይልቁንም እብሪተኞችን ወደ ሠላም መድረክ እንዲመጡ የሚመኩበትን ሀይል ለማጥፋት/ለማዳከም ሲሉ ምትክ የሌለውን የሕይወት ዋጋ የሚከፍሉ በወሣኝ ግንባሮች ላይ የሚገኙ የአገር መከላከያ ሠራዊት ዋጋ የሚያሳንስ ይመስለኛል፡፡ ይህ ፅሁፍ ዓላማው በምንም መመዘኛ በሀቅ ለሠላምና ድርድር የሚፈልጉ አካላትን ለማንኳሰስ ወይም ለመንቀፍ አይደለም፡፡ ይልቁንም የሚሉትን ሠላም ማምጫ የድርድር “ፍኖተ ካርታ” እንዲያቀርቡ ለመገፋፋት ተግባራዊ ፈተና ለማቅረብ ነው፡፡
የውጭ ሀይሎች በአገራችን ኢትዮጵያ ሠላም እንዲመጣ ፍላጎት አለን ብለው ጣልቃ ለመግባት የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፡፡ በእርግጥ የእኛ ሠላም መሆን ያሳስባቸዋል? ብሎ መጠየቅ አይከፋም፡፡ በዓለማችን እብሪተኞች ሳይንበረከኩ ሠላም የተገኘበት አንድ ምሣሌ ሊሰጡን አይችሉም፡፡ በመጀመሪያው የዓለም ጦርነት በአስራ አንድ ሰዓት፤ በአስራ አንደኛው ቀን በዓመቱ አስራ አንደኛ ወር የጀርመን እብሪተኛ ለሠላም እጅ የሰጠው በጉልበት ነው፡፡ ዛሬ እኛን ሠላም በጦርነት አይገኝም፤ የምትለን አሜሪካ በመጨረሻው ሠዓት በዚህ ጦርነት ውስጥ ወሣኝ ሚና ነበራት፡፡ ዛሬም ዳቦ እያሳዩ ክብራችንን ሊወስዱ የሚፈልጉ የውጭ ሀይሎች ሠላም ሊያመጡልን አይችሉም፡፡ ይህን አውቀን መንቀሳቀስ ይኖርብናል፡፡
ኢትዮጵያዊ የሆነ ሠላም እንዲመጣ የሚደረግ ድርድር አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ ድርድር የሚካሄድበት አውድ ምን የሚመስል ነው? ብሎ መመልከት ያስፈልጋል፡፡ በአገራችን ትህነግ/ህወሓት ባለፉት 30 ዓመት ያደረገውን ነገር ሁሉ ትተን፤ ከጥቅምት 24 2013 ዓ.ም ወዲህ ያሉትን ብቻ ብንመለከት የሚከተሉትን ወሳኝ ኩነቶች እናገኛለን፡፡
• ትሕነግ በጥቅምት 24 2013 በሰሜን ዕዝ ላይ “መብረቃዊ” ያለውን ጥቃት ፈፅሞ ዋናውን አገራዊ ተቋም በሰው ሀይልም በቁስም በማውደም በዓለም ታሪክ አዲስ ታሪክ አስመዝግቧል፤
• በማይካድራ ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት በመፈፀም በሺዎች የሚቆጠሮ ዜጎችን ሕይወት የቀጠፉ ሲሆን፤ ይህን ድርጊት የፈፀሙት “ሳምሪ” በመባል የሚታወቅ ትህነግ ያደራጀው የወጣት ሀይል መሆኑ ተረጋግጧል፡፡
• በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጠረውን ሕገወጥ ድርጊት ለመቀልበስ በተደረገው ዘመቻ፤ በትግራይ ሕዝብ ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ እንዲፈጠር አድርጓል፤
• ከሰኔ 22 2013 ጀምሮ መንግሥት በተናጥል በወሰደው የተኩስ አቁም ተከትሎ እራሱን መልሶ ለማደራጀት እድል ያገኘው የትሕነግ/ህወሓት ሀይል ወደ አማራና አፋር ክልል ወረራ በማካሄድ ከፍተኛ ውድመት ያደረሰ ሲሆን፤ በአፋር 107 ሕፃናትን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ በመጠላይ ውስጥ ያሉ ሲቪሎችን በማጥቃት ወንጀል ፈፅመሟል፡፡
• በትግራይ የሚገኙ ጊዚያዊ መንግሥቱን ደግፈዋል ያሉዋቸውን ተጋሮዎች ያለምንም የፍርድ ሂደት ረሸነዋል፡፡
• በወረራ በተቆጣጠሩት የአማራና አፋር ክልል አካባቢ እንስሳትን በጥይት እየደበደቡ ገድለዋል፤ የሲቪል መኖሪያዎችን እና የጤና ተቋማትን አውድመዋል፡፡
• የክልል ሀይል ሊታጠቅ ከሚገባው በላይ (በሕገ መንግሥት ድንጋጌ ውጪ) በመታጠቅ የፌዴራል ሥርዓቱን አደጋ ላይ የሚጥሉ ድርጊቶችን በተደጋጋሚ ፈፅሟል እየፈጸመም ይገኛል፡፡
እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩትን የአገር ሉዓላዊነትን አደጋ ላይ የጣለ፤ የዜጎችን ስብዓዊ መብት የጣሰ ከፍተኛ የአገር ሀብት ያወደመ የወንጀል ተግባር ከፈፀመ ሀይል ጋር ድርድር እንዴት መቀመጥ ይኖርብናል? ብሎ ማስብ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ነው፡፡ ልክ ነው፤ አገራችን ኢትዮጵያ ሠላም ትሻለች፤ የሠላም ትሩፋት ዜጎች እንዲቋደሱ መሥራት የሁሉም ሠላም ወዳድ አካላት ርብርብ ይፈልጋል፡፡ ሠላምን ለማምጣት ግን “አንተም ተው፤ አንተም ተው!!” በሚል ባህላዊ መንገድ መሞከር ብዙ ርቀት የሚያስኬድ አይደለም፡፡ ማንኛውም ለሠላም ድርድር እራሱን ያጨ አካል ከላይ የተነሱትን ሁኔታዎች በቅጡ በማስተዋል፤ ወንጀለኛውን መለየትና ተጠያቂ ማድረግ የግድ የሚል ይሆናል፡፡ ይህን አለማድረግ አገሩን ሊጠብቅ በቀበሮ ጉድጓድ እና በካምፕ የነበረን ሠራዊት በድቅድቅ ጨለማ በአንድ ጊዜ ከመቶ በላይ ቦታዎች ላይ ጭፍጨፋ አካሂዶ “መብረቃዊ” ያለውን ጥቃት እውቅና መስጠት እና ቤተሰቦቻቸውን እንደሌሉ መቁጠር ነው፡፡ በሌላ ጊዜም ተመሳሳይ ድርጊቶችን ከማበረታታቱም በላይ ውንብድናን እንደመሸለም ነው፡፡ በአፋር የተጨፈጨፉ ሕፃናት በትግራይ ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች፤ በማይካድራ በማንነታቸው ተለይተው የተጨፈጨፉ ዜጎችን ምንም አይድለም ቻሉት ብሎ እንደማላጋጥ ነው፡፡ ወንጀል መሸፈን እና ወንጀለኞችን ነፃ ማውጣት ነው፡፡
በእኔ እምነት በኢትዮጵያ የሚደረግ ሠላም ለማምጣት የሚደረግ ድርድር ሊያሟላቸው የሚገባ መሰረታዊያን የሚከተሉት መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

  1. የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እና ኢትዮጵያዊነት በማያንኳስስ ሁኔታ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህን ለማንኳሰስ የሚደረጉ መቧደኖቹን የፌዴራሊስት ሀይል ወይም ሌላ ተመሳሳይ ስብስብን ሊቀበል አይገባም፡፡
  2. ወንጀለኞችን በጥፋተኝነት ተጠያቂ የሚያደርግ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎችና ቤተሰቦች ተገቢውን እውቅና እና ካሣ ሊከፈላቸው ይገባል፡፡
  3. ተጎጆዎችን ያሳተፈ የይቅርታና አርቅ መድረክ በተከታይነት ሊኖረው ይገባል፡፡
  4. ወንጀለኞችን ተጠያቂ ለማድረግ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በምንም ሁኔታ በፕሮፓጋንዳ የሚታጀቡ፤ ፍትህን የሚያዛቡ እና ዘላቂ ሠላም እንዳይመጣ ጥላቻ የሚዘራባቸው ሊሆኑ አይገባም፡፡
    እነዚህን መሠረታዊያን ከግምት በማስገባት የሠላም እና እርቅ ለማካሄድ የሚደረጉ ድርድሮች የሚከተሉትን ተግባራት ማከናወን ይኖርበታል፡፡
  5. የትሕነግ አመራሮች በዋና ተዋናይነት ክስ የተመሰረተባቸው ጥፋታቸው መጠን በሂደት በመረጃ የሚጣራ ሆኖ ከላይ ለተፈጠሩት ወንጀሎች በተጠያቂነት እጃቸውን ለመንግሥት እንዲሰጡ፤ ትህነግ እና የትህነግ አርማ በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ አገልግሎት ላይ እንዳይውል ማገድ፡፡
  6. ከዋና አመራር ሰጪነት ውጪ ያሉ የትሕነግ/ህወሓት አመራሮች እና አባላት ምዕረት ተደርጎላቸው በአካባቢያቸው የፈፀሙት ወንጀል ካለ በአካባቢ ደረጃ በሚፈጥር የሠላምና እርቅ ጉባዔ መፍትሔ እንዲያገኝ ማድረግ፤
  7. እጃቸውን የሚሰጡ አመራሮች በገለልተኛ አካላት ክትትል የሚደረግበት ምቹ የማረፊያ ቦታ እንዲዘጋጅላቸው እና የፍርድ ሂደታቸውን ያለምንም ተፅዕኖ እንዲከታተሉና እንዲከላከሉ እድል የሚፈጥር እንዲሆን ማድረግ፤ማስረጃ ያልተገኘባቸው በአፋጣኝ ነፃ እንዲሆኑ ማድረግ፤
  8. የፍርድ ሂደቱ በማንኛውም መመዘኛ ገለልተኛ እንዲሆን አስፈላጊ ከሆነ እና ተከሳሹች ከፈለጉ ገለልተኛ አካላት የሚታዘቡት እንዲሆን ማድረግ፤
  9. የጥፋተኝነት ውሳኔ እና ፍርድ ሲሰጥ የሞት ፍርድ የሚሆን ከሆነ መንግሥት፤ የቅጣት ማቅለያዎችን በማድረግ ለሠላም እና ለጥፋተኞችም የመፀፀቻ እድል የሚሰጥበትን እድል እንዲያመቻች ማድረግ፤
  10. መንግሥት የደረሱትን ጥፋቶችን ያለምንም ማጋነን፤ በትክክል እንዲሰንድ እና ለሕዝብ ይፋ መማሪያ እንዲሆን በጥቅምት 24 ለተጨፈጨፉ የመከላከያ ሀይል አባላትን እርሱን ተከትሎ ለተከሰቱት ውድመቶች መታሰቢያ በሚቋቋም የሠላም ማዕከል ውስጥ እንዲኖር ማድረግ፤ አና
  11. በትግራይ ክልል በአስቸኳይ ምርጫ ተካሂዶ፤ በሕዝብ የተመረጠ መንግሥት እስኪመሰረት ጊዚያዊ የሽግግር መንግሥት እንዲቋቋም፤ ክልሉን ከማንኛውም የጦር መሣሪያና ታጣቂዎች እንቅስቃሴ ነፃ በማድረግ ሠላም ማስፈን፡፡
    በእኔ እምነት ወንጀለኞችን ለመበቀል ያላለመ፤ ተጠያቂነት የሚያሰፈን ለአገራቸው ሕይወታቸውን ለመስጠት ለተሰለፉ የሠራዊት አባላት መስዋዕትነት ክብር የሚሰጥ ፍኖተ ካርታ ይመስለኛል፡፡ የተሻለ የምትሉት ፍኖተ ካርታ ካላችሁ ጀባ በሉን፡፡ እንወያይበት እናዳብረው፡፡
    ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
    ቸር ይግጠመን
    ግርማ ሰይፉ ማሩ
OPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ፍላቂት ከተማ ነፃ ሆናለች – “ወራሪው እንዳይወጣ የመቄት ወረዳ መሪዎች ቁልፍ ቦታን እንዲይዙ”
« I have never seen such barbarous creatures in my life »
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2