Skip to content
VOE
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የነጻ አውጪ ድርጅቶችን ያካተተ የተቃዋሚ ፓርቲዎች የምክክር ቤት (caucus) ተቋቋመ-በምርጫ ዜሮ ድምጽ ያገኘ ፓርቲም አለበት

    June 7, 2022

    የፊታችን ማክሰኞ ከሸኔ ጋር የሰላም ንግግር በይፋ ይጀመራል

    April 23, 2023

    ያሞጠሞጠ እባጭ – “ጥርስ ነቀላ መጣሁ”

    September 15, 2021

    BRICS: Zambia Seeks De-Dollarization, Plans to Ban US Dollar For Local Trade

    August 1, 2024

    በ30 ቢሊዮን ብር ወጪ 3 የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ተገንብተው ለባለሃብቶች ክፍት ሆኑ

    November 26, 2022
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  OPINION  መስቀል አደባባይ ፕሮፋይሉ ነው፤ ሊንኩ ግን ወያኔ ነው
OPINION

መስቀል አደባባይ ፕሮፋይሉ ነው፤ ሊንኩ ግን ወያኔ ነው

Ethioreview newsEthioreview news—February 12, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

መስቀል አደባባይ በትውፊት የኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ይዞታና የአዲስ አበባ ኦርቶዶክሳውያን የደመራ በዓል ማክበርያ አደባባይ ነው ። ነገር ግን በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዐት መሠረት የሥርዐተ አምልኮ ማስፈጸምያ ቤተ ክርስቲያን ግን አይደለም።

የመስቀል አደባባይ ክርክር የነገረ ድኅነት (ነገረ መስቀል) ክርክር የሚያደርጉ አዲስ ክርስቲያኖች ይገርሙኛል ፣ ክርክሩ የዜግነት ክርክር መሆኑ መዘንጋት የለበትም ። የዜግነት ክርክር ከሆነ ደግሞ ትውፊታዊ ይዞታነቱ የኦርቶዶክስ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ውይይቱ ሃይማኖት ሳይለይ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ሁሉ ይመለከታል ። #ከኦርቶዶክስ ውጭ ላሉ አማኞች የአደባባይ መርሐ ግብር የሚያደርጉበት አማራጭ መፍትሔ ከተገኘ ጥሩ ነበር። አማራጭ መፍትሔ ካልተገኘ ደግሞ ሁሉም ኢትዮጵያውያን መርሐ ግብራቸውን በመስቀል አደባባይ አድርገው ቢገለጉሉበት ኃጢአትነቱ አይታየኝም ። ስለሚያደርጉበት ሁኔታና አፈጻጸም ላይ ስምምነት መፍጠር ግን ይቻላል ። ይህንን የሚደግፍ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል አለን ፤ ነገር ግን ይህን የሚቃወም የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል የለንም ። (የሐዋ.ሥራ 17 ላይ የአርዮስፋጎስ አደባባይ አገልግሎትን ይመልከቱ)

ለምን ይዋሻል ???

በውጭው ዓለም አብዛኛዎቻችን ኦርቶዶክሳውያን የራሳችን ቤተ ክርስቲያን እስኪኖረን ድረስ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንን ወይም የፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያንን ተከራይተን ወይም በችሮታ አግኝተን ከካቶሊክ ወይም ከፕሮቴስታንት ቀጥሎ ወይም በቅድምያ በሰዓት ልዩነት በፈረቃ እያመለክን አይደል ??? ምነው ታድያ በሀገራችን በሀገራቸው ኢትዮጵያውያንን ማግለል ለምን አስፈለገን ???

“መስቀል አደባባይ የኦርቶዶክስ ይዞታ ሲሆን የሌሎች ኢትዮጵያውያን ሁሉ አደባባይ ነው “በሚለው መስማማት ያለብን ይመስለኛል ። ከይዞታ ጋር በተያያዘ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በመስቀል አደባባይ ጉዳይ ስያሜው እንዲጠበቅላት ፣ አደባባዩ ደግሞ የገንዘብ ጥቅምና ገቢ የሚያስገኝ ከሆነ ሕግ እስከፈቀደላት ድረስ የጥቅም ተካፋይ እንድትሆን መደራደርና መወያየት ትችላለች ።
ከዚህ ባለፈ እንደቫቲካን ኢትዮጵያን በፍትሐ ነገሥት የምትተዳደር ማስመሰል የትም አያደርሰንም ፤ በአሁኑ ግዜ እንኳን ሀገር በፍትሐ ነገሥት የሚመራ ጳጳስ የለም ፣ በዚህ ምክንያት ጳጳሳቱ ሕገ ቤተ ክርስቲያን ብለው የራሳቸው የቃለ ጉባኤ ስምምነት እንጅ ከፍትሐ ነገሥቱ ጋር ከተቆራረጡ ቆይተዋል ።

ጎበዝ !!!

More stories

በአማራ ክልል የሰላም ዋጋ ስለምን ተራከሰ? የንጹሐንና ሕጻናት … እምባ

October 3, 2024

ለሰሞኑ የሰማይ ላይ ትዕይንት ንጽጽር “የሽግግሩ አመራርና አሻጋሪ” የጓሮ ድራማው እንደ ወረደ – ጦርነት ዳግም?

July 20, 2021

ኢህአዴግ ጣና በለስን ለምን አፈራረሰው?

July 7, 2024

“ብርሃኑ የጣለውን ብርሃኑ ያነሳዋል?” የሰሞኑ ወግ

September 19, 2025

አሁን የተቸገርነው በቢሮ አሠራር የሚፈታ የመስቀል አደባባይ ጉዳይን የፓለቲካ ጉዳይ የሚያደርጉ ዲጅታል ወያኔዎች ቤተ ክህነቱን እያዋከቡት ስለሆነ ነው ። ጉዳዩን መቀሌ ካለው ስውር አንጃ ጋር እንደሚገናኝ የሚያውቅ ሰው ያለ ግን አይመስልም ፤ በተለይ ምእመናን አልተረዱትም ። ወያኔ ከመቀሌ ሆኖ አንዳንድ “ባለትዳር ጳጳሳትን” በርኲሰታቸው እያሸማቀቀ ጠበል እንደገባ ጸበልተኛ በመስቀል አደባባይ ጉዳይ የፓለቲካ እንዲሆንለት ያስለፈልፏቸዋል ።

ወገኔ ንቃ !!!!

የብሔርና የሃይማኖት ግጭት ለማስነሳት መስቀል አደባባይ ፕሮፋይሉ ነው፤ ሊንኩ ግን ከሰሜን ወያኔ ነው ። ከቤተ ክህነት ደግሞ ፓለቲካው ያጠለላቸው አቅመ ቢሶች፣ ኮንዶሚንየም ጠይቀው አይሰጣችሁም የተባሉ የአምልኮ መልክ ያላቸው የሜዳ ቄሶች ፣ ከቤተ ክህነት ውጭም መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት የሌላቸውና መዋቅር ውስጥ የሌሉ “አቶዎች” እንዲሁም ከተከፈላቸው ለወያኔ ብቻ ሳይሆን ለሰይጣንም የሚሠሩ ጥቅመኞች የብሔርና የሃይማኖት ግጭት ለመፍጠር የተሰለፉበት ነው ።

እነዚህ ሰልፈኞች ከዲጂታል ወያኔ ጋር በመተባበር በቢሮ አሠራር የሚፈታውን የመስቀል አደባባይን ጉዳይ ኾን ብለው አዲስ አበባ ላይ “የኦርቶ አማራና የኦርቶ ኦሮሞ” በሚል ስያሜ ግጭት ለማስነሳት በማኅበራዊ ሚድያ እየተውተረተሩ ነው።

እነዚህ ግጭት ጠማቂዎች በግጭቱም መሀል ወያኔን አዝሎና በመካከል አሾልኮ አዲስ አበባ ለማስገባት የጊዜ ሰሌዳ ነድፈዋል ፤ ወያኔ ቆዳውን የሃይማኖት አድርጎ “ሰሜናውያን” በሚልና በልዩ ልዩ ኢመደበኛ አደረጃጀት ማኅበራትን ፈጥሮ “ኦርቶ አማራ” ባለው ስውር አደረጃጀት ውስጥ ራሱን ሸሽጓል ፤ ባጠቃላይ ምንም ይሁን ምን የሃይማኖት ግርግርና ግጭት ከተነሣ ወያኔን አዲስ አበባ ለማስገባት የተጀመረ ኅቡእ አደረጃጀት ቤተ ክህነቱን እየናጠው ነው ።

ኦርቶዶክሳዊ ወገኔ ንቃ !!!

የመስቀል አደባባይ ጉዳይ የባሕር ዳር ጉዳይ አይደለም፣ ወይም የወለጋ ጉዳይም አይደለም ፣ ወይም የአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳይ አይደለም፣ የሲኖዶስም ጉዳይ አይደለም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጉዳይም አይደለም ፣ ጉዳዩ የሚመለከተው በአዲስ አበባ ያሉ የሌሎች ቤተ እምነቶችን አስተያየት ባካተተ መልኩ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትንና የአዲስ አበባ መስተዳድርን ብቻ ነበር። የመስቀል አደባባይን ጉዳይ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ደረጃ መፍታት ይቻል ነበር ። ነገር ግን ጉዳዩን በሲኖዶስ ደረጃ ማድረጉ ለማያዳግም ውሳኔ ይረዳል በሚል ታስቦ ሊሆን ይችላል ። በአንጻሩ ግን ጉዳዩ በሲኖዶስ ደረጃ በመታየቱ ምክንያት የሃይማኖትና የብሔር ግጭት ለማስነሳት ስውር የወያኔ ተልእኮ ያላቸው ቡድኖች ጉዳዩን እያጋነኑ ሀገራዊ የብሔርና የሃይማኖት ግጭት ለመፍጠር እየተጠቀሙበት ነው ።

እውነታው ይህ ነው።

ይሁንና የከተማችን የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ሥልጣኔን ልጠቀም ሳይሉ ከቢሮዬ ድረስ አቤቱታችሁን ይዛችሁ ኑ ሳይሉ ፣ እስከአሁን ድረስ በትሕትና አባቶችን በማክበር አቤት በማለት ላገልግላችሁ በሚል መንፈስ ችግሩን በሰላምና በሕጋዊ መንገድ ለመፍታት ከፓትርያርኩ ጋር የተወያዩበት መንገድ ከሲኖዶስ ጽ/ቤት ጋር የሚሄዱበት የትሕትና መንገድ ያስመሰግናቸዋል ።

አባ ማትያስ ግን የአዲስ አበባን ከንቲባ ሳይሆን የመቀሌን ከንቲባ ካላናገሩ የሚስማሙ አይመስልም ። የሳቸው ኢቀኖናዊ አካሄድ የታወቀ ነው ፤ ነገር ግን ሌሎች አባቶች ይህንን የትሕትና አቀራረብ መረዳት ካልቻሉና የውይይት ዕድሉን የማይጠቀሙት ከሆነ የአባቶችን ቃል ላክብር በማለት ወደ ፓትርያርኩ የመጡትና ከሲኖዶስ ጽ/ቤት ቤት ጋር መልካም ግንኙነት የፈጠሩት የከተማችን ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እስካሁን ያሳዩትን ጥረት እያደነኩ ከዚህ በኋላ የዲጅታል ወያኔ የአሉባልታ ዘመቻ ሳይበግራቸው የመስቀል አደባባይን ጉዳይ በሕግና በሰላማዊ መንገድ ሥልጣናቸውን ተጠቅመው እንደከንቲባነታቸው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመወያየት መፍትሔ መስጠት የሚችሉ ጀግና መሆናቸውን አምንባቸዋለሁ ።

ይኸው ነው ። ሻሎም !!! Via Dr Zerihun Mulatu / ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ – ነጻ አሳብ የአዘጋጁ አቋም የለበትም!!

OPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“መከላከያ የማያዳግም ሙሉ ማጥቃት ሊሰነዝር እንደሚችል ፍንጭ ሰጠ”
የታዳጊው ወጣት ሰናይ ተግባር – በደባርቅ ።
Related posts
  • Related posts
  • More from author
OPINION

እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ…

April 8, 2026
OPINION

ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት!

April 8, 2026
OPINION

ሙስጠፌ ተረኛው ባለስልጣን – የሃሰት ትርክ ዘመቻ በደቦ

March 28, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2