Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል ምንነትና ልዩ ባህሪያት
law

ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል ምንነትና ልዩ ባህሪያት

Ethioreview newsEthioreview news—April 13, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

“ወንጀሉ በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር በተሻገረው ሰው ላይ ሞት አስከትሎ እንደሆነ አሻጋሪው እስከ ሞት በሚደርስ ቅጣት ሊቀጣ እንደሚችል በህጉ ተደንግጎ ይገኛል”

ሰላም ጤና ይስጥልን ውድ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችን ተከታታዮች ባለፈው ሳምንት በሰው መነገድ ወንጀል ምንነት ላይ አንድ ጥርቅር ወደ እናንተ ማድርሳችን ይታወሳል ታዲያ በክፍል ሁለት ፕሮግራማችን ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል ምንነትና ልዩ ባህሪያት በሚል ርዕሰ-ጉዳይ አንድ ጥንቅር ልናቀርብላችሁ ቀጠሮ ይዘን በተለያየነው መሰረት በዛሬው ጥንቅራችን ስለ ጉዳዩ በፍትህ ሚኒስቴር በብሄራዊ ትብብር ጥምረት ጽ/ቤት ውስጥ ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ ከሆኑት ከአቶ አቤል ገ/እግዚሀበሔር ጋር ቆይታ አድርገን ተከታዩን ማብራሪያ ሰጠውናል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-

ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል ሲባል ምን ማለት ነው?

ሰዎችን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል እንደ በሰዎች የመነገድ ወንጀል ሁሉ በባህሪዉ ድንበር ተሻጋሪ እንዲሁም በተደራጁ ቡድኖች ሊፈፀም የሚችል ነዉ ሲሉ አቶ አቤል ማብራሪያቸውን ይጀምራሉ ወንጀሉ በሀገራት ልዋላዊነት ላይ የሚፈጸምና የተጎጂዎችን ስምምነት መሰረት አድረጎ መፈጸሙ የልዩ ባህሪው መገለጫ መሆኑን ያነሱት ዐቃቤ ህጉ ይህም ሁኔታ በሰው ከመነገድ (ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር) የሚለየው ዋንኛ ምክንያት ነው ይላሉ። በሰው የመነገድ ወንጀል በሰዎች ሰብዓዊ ክብር ላይ የሚፈጸምና የተጎጂው ፍቃደኝነትም የሌለው ወይም ቢኖረውም በህግ ፊት ተቀባይነት የሌለው መሆኑ ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል የሚለየው ጉዳይ መሆኑንም ያነሳሉ።

More stories

ግማሽ ሚሊየን ብር በጥሬው ሲቀበል እጅ ከፍንጅ የተያዘው ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ

February 1, 2022

ዐቃቤ ህግ በቀድሞ የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የክስ መዝገብ ሌሎች ድርጅቶችን አካቶ ለመቅረብ ጠየቀ

July 7, 2023

በሰሜን ኢትዮጵያ ባለው ግጭት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመመርመር የተቋቋመው የሚኒስቴሮች ግብረ-ሀይል ስራውን በይፋ ጀምሯል

November 29, 2021

ሰው በማገት ወንጀል የተከሰሱ ሁለት ግለሰቦች 22 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት ተፈረደባቸው

February 16, 2022

በመሆኑ የአለም ሀገራት ሀገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ ወንጀሉን በጋራ ለመከላከል እንዲያስችላቸዉ ፍልሰተኞችን በየብስ፣ በባህር እና በአየር ማሻገርን የሚከለክለውን የስምምነቱ ድጋፍ ፕሮቶኮል በመፈረም በመተግበር ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ እኛም ከተል አድርገን ለመሆኑ ፕሮቶኮሉ ዓላማ አድርጎ የተነሳው ምንድን ነው ብለን ጥያቂያችን አነሳንላቸው እሳቸውም ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተውናል፡-

ይህ ሰዎችን በህገ- ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ፕሮቶኮል አላማዉ አድርጎ የተነሳዉ
ሰዎችን በህ-ገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል ለመከላከልና ለመቆጣጠር፣
ለዚሁ አላማ የአባል ሀገራትን ትብብር ማጠናከር እና
ሰዎችን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል ተጎጂዉችን መብት ለማስጠበቅ ነዉ ሲሉ አላማውን ይገልጻሉ፡፡

ኢትዮጵያም በአዋጅ ቁጥር 1178/2012 አንቀጽ 8 መሰረት ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል ተፈፀመ የሚባለው ማንኛዉም ሰው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የገንዘብ ወይም ቁሳዊ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ፡-

ሰዉን በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት እንዲገባ ካደረገ፣
ከኢትዮጲያ ግዛት እንዲወጣ ካደረገ፣
በኢትዮጵያ ግዛት እንዲተላለፍ ካደረገ፣ ወይም ሰውን ከኢትዮጵያ ግዛት ለማስወጣት ዝግጅት ያደረገ፣ በሂደት ላይ የተገኘ፣ ያጓጓዘ ወይም የተቀበለ እንደሆነ ነው ሲሉ በአዋጁ ላይ የተካተቱ ሀሳቦችን ዋቢ አድርገው ያነሳሉ፡፡

ከቅጣት ጋር ተያይዞ ላነሳንላቸው ጥያቄ ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራት ፈጽሞ የተገኘ አካል ከ5 ዓመት እስከ 10 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራትና ከ10 ሺህ እስከ 100 ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይጠብቀዋል ሲሉ ይናገራሉ፡፡ ከላይ እንደተመለከተው በአዋጁ መሰረት ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል ማቋቋሚያዎች ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ድርጊትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው ፕሮቶኮል ለወንጀሉ ካስቀመጣቸው ማቋቋሚያዎች ጋር ተመሳሳይ ናቸውም ብለዋል፡፡ ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል በሰው ከመነገድ ወንጀል የሚለየው በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ (በስምምነት የሚፈፀም) መሆኑ፣ ሁልጊዜም ድንበር ተሻጋሪ መሆኑ እና በሰው የመነገድ ወንጀል በአገር ውስጥም ሊፈፀም የሚችል መሆኑ፣ ወ.ዘ.ተ ይገኝበታልም ሲሉ ልዩ ባህሪውን ያብራራሉ፡፡

የወንጀሉ ማክበጃ ሁኔታዎችን በተመለከተም ተከታዩን ማብራሪያ አስቀምጠዋል፡-

በአዋጁ አንቀጽ 8 ስር እንደተመላከተው ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል ማክበጃ ተደርገው የተወሰዱት የወንጀሉ አፈጻፀም ሁኔታ፣ የተጎጅዎች ሁኔታ እና እድሜ እንዲሁም የወንጀል ፈጻሚው ማንነት ሲሆኑ ማክበጃዎቹና የተቀመጠላቸው ቅጣትም ወንጀሉ የተፈፀመው፡-
በሕጻናት፣ በአዕምሮ ህመምተኛ ወይም በአካል ጉዳተኛ ላይ ከሆነ፤
አደንዛዥ ዕፅ፣ መድሃኒት ወይም የጦር መሣሪያ በመጠቀም እንደሆነ፤
በመንግስት ሠራተኛ ወይም በባለሥልጣን ከሆነና ወንጀሉን የፈጸመው የተሰጠውን ኃላፊነት መከታ በማድረግ ከሆነ፤ ወይም
የአገር ውስጥ ወይም የውጭ አገር የሥራ ስምሪት ፈቃድ ባለው አካል ፈቃዱን ሽፋን በማድረግ እንደሆነ፤ ከ7 ዓመት እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እና ከ20 ሺህ እስከ 150 ሺህ ብር በሚደረስ መቀጮ የሚቀጣ ሲሆን የወንጀል ድርጊቱ፣
በተጎጂው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት፣ የማይድን በሽታ ወይም ዘላቂ የአዕምሮ ጉዳት ካስከተለ፣
የተደራጀ የወንጀል ቡድን አባል በመሆን ወይም ቡድኑን በመምራት ወይም በማስተባበር ከተፈፀመ፤
የተጎጂው ህይወት ወይም ደህንነት አደጋ ላይ የወደቀ ወይም ለኢ-ሰብአዊ አያያዝ የተዳረገ እንደሆነ ከ10 ዓመት እስከ 20 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እና ከ30 ሺህ እስከ 150 ሺህ ብር በሚደርስ መቀጮ የሚቀጣ ሲሆን፣

በተጨማሪም ወንጀሉ በተጎጂው ላይ ሞት አስከትሎ እንደሆነ ከ15ዓመት እስከ 25 ዓመት ወይም እድሜ ልክ ፅኑ እስራት ወይም በሞት እና ከሃምሳ ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል ሲሉ የቅጣቱን ማክበጃ ምክኒያቶች በዝርዝር አቃቤ ህጉ ያስቀምጣሉ፡፡

ውድ ተከታታዮቻችን ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ ጥንቅር በዚሁ አበቃን ዐቃቤ ህጉን ከኛ ጋር ላደረጉት ቆይታ እያመሰገንን በቀጣይ በሌላ ጥንቅር እስክንገናኝ ሰላም፡፡

Via – Attorney general

law
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ውሃ ሲወስድ እያሳሳቀ … “አማራ ወደ አራት ኪሎ አምራ” የተከበሩ አቶ ክርስቲያን አዘዙ
ለህብረተሰቡ የቀረበ ጥሪና ጥቆማ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
law

ህገወጥ የውጭ ምንዛሪ ወንጀል የፈጸሙ 123 ተጠርጣሪዎች የባንክ ሒሳብ ታገደ

September 20, 2025
law

እነ ቀሲስ በላይ በሙስና ወንጀል ሊፈርድባቸው እንደማይገባ ጠቅሰው ያቀረቡት ይግባኝ ውድቅ ሆነ

July 26, 2025
law

የአዲስ አበባ የከንቲባ ፅ.ቤት ፕሮቶኮልን ጨምሮ 12 ተከሳሾች በሌብነት ተከሰው ተፈረደባቸው

July 23, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2