Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ታላቁ ህዳሴ ግድብ በመገባደጃ ምዕራፍ ላይ

    April 1, 2023

    የአሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችል ስራ መጀመሩን ይፋ አደረገ

    August 22, 2024

    ዶናልድ ትራምፕ በቁጥጥር ሥር ውለው በቀረበባቸው ሰላሳ አራት ክሶች ጥፋተኛ አይደለሁም አሉ

    April 6, 2023

    የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰነድ የሌላቸው የኤርትራዊ ስደተኞች መታሰራቸውን ኮነን፤ “ያለ ህጋዊ ማስረጃ የትኛው አገር መኖር ይቻላል?”

    June 4, 2023

    ቻይናዊው የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ከ9 ግብረ አበሮቻቸው ጋር የውጭ አገር ብሮች በማተምና በጥቁር ገበያ ወንጀል ታስረው ፍ/ቤት ቀረቡ

    September 5, 2023
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  የጆ.ባይደን አስተዳደር የሰላም አማራጭ ንግግሩን ቀድሞ የትህነግን ፍላጎት አቋም አድርጎ አቀረበ
News

የጆ.ባይደን አስተዳደር የሰላም አማራጭ ንግግሩን ቀድሞ የትህነግን ፍላጎት አቋም አድርጎ አቀረበ

Ethioreview newsEthioreview news—November 1, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በተደጋጋሚ የትህነግ አመራሮችና ደጋፊዎች፣ የአውሮፓ ህብረትና የህብረቱ አካላት ሲደጋግሙ የነበሩትን አቋም አሜሪካ በአራት አሳቦች ጠቅላላ ከንግግሩ ፍጻሜ የሚጠበቅ እንደሆነ አስታወቀች። መንግስት ጣልቃ ገብነቱ አሳስቢ መሆኑንን ጠቅሶ ለጫናው እንደማይንበረከክ ማስታወቁ ይታወሳል።

በቅርቡ በትህነግ ሚዲያ አቶ ስዬ አብርሃ በዝርዝር ያቀረቡትን መሰረታዊ የድርጅታቸው ፍላጎቶችን ቃል በቃል ደግማ አሜሪካ በትናንትናው እለት እንዳስታወቀችው አራት አንኳር ጉዳዮች ላይ ስምምነት ይደረጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው።

“በኢትዮጵያ ተፋላሚ ወገኖች መካከል የሚደረገው የሰላም ንግግር አራት ግቦች አሉት ። አፋጣኝ የተኩስ አቁም፣ ያልተገደበ ሰብዓዊ ዕርዳታ ፣ የሰላማዊ ሰዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ተጨማሪ እርምጃዎች መውሰድና የኤርትራ ወታደሮች ከሰሜን ኢትዮጵያ መውጣታቸውን ማረጋገጥ” ስትል አሜሪካ ያስታወቀችው በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቃባይ ኔድ ፕራይስ በኩል ነው።

መንግስት አካሄዱን በውል በመገንዘብ ከላይ የተነሱትን ፍላጎቶች አንድ በአንድ እያነሳ ከህግ፣ ከመንግስት ስልጣንና ከአገሪቱ ሕገ መንግስ ጋር በማያያዝ እንደማይቀበላቸው፣ የተነሱት ነጥቦች አግባባቸውን ጠብቀው በህግ በተቀመጠ ስልታን እንደሚከናወኑ፣ አማጺው ቡድን የሚለው አካል በህገ መንግስቱ መሰረት የስራ ጊዜው ያበቃና ህጋዊ ማንዴት የሌለው በመሆኑ የሽግግር አስተዳደር እንደሚተከል፣ ትህነግም ይህን አክብሮ ልክ እንደ ጋምቤላ፣ ቤኒሻንጉል፣ አፋር … ክልሎች አንድ መሆኑንን አምኖና በተለየ መልኩ ራሱን ማየት እንዲያቆም፣ በአገሪቱ አንድ መከላከያ ብቻ ስለሚኖር ትጥቅ እንዲፈታ የያዘውን አቋም ለህዝብ ይፋ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል። ሕዝብም ከዳር እስከዳር ወጥቶ ” አሜሪካ በአገራችን ጉዳይ ጣልቃ አትግቢ” ብሏል። ከሁሉም በሁዋላ መንግስት ስም ሳይጠቅስ ” ግንኙነቴን ለመረመር እገደዳለሁ” ሲል አቋሙን አጽንቶ መቆየቱ ይታውሳል።

More stories

“ትህነግ ከጁንታነትም ወርዶ በየጫካው ተሹለክላኪ የእህል ሌባ ሆኗል፣ ከያለበት እየታደነ ነው “ሜ/ጀ መሐመድ ተሰማ

April 7, 2021

የመ/ሰራዊትን መለያ ለብሶ ከሱዳን ወደ ወልቃይት ሊገባ የነበረ የትህነግ የሽብር ሃይል ተደመሰሰ፤ አንገታቸው የተቀላ መኮንኖች ፊልም ሊታዩ ነው

May 13, 2021

ከሱዳን የተነሳ የትህነግ ሃይል (ሳምሪ) ሳይዋጋ ሙሉ በሙሉ ተማረከ

August 11, 2021

የመንግስት ማጅራት መቺዎች ፈተና ሆነዋል – ሃላፊዋ አምነዋል

May 9, 2022

ቀደም ስሊ ባወጣነው ዘገባ ድርድሩ ከመጀመሩ በፊት ትህነግ ትጥቅ ለመፍታት መስማማቱን፣ ራሱን እንደክልል ለማየትና የፌደራል መንግስቱን ለማክበር መስማማቱ መዘገባችን ይታወሳል። “አሜሪካ አታለሉን” ብለው የሚደርሳባቸውን ጫና እንዲያልፉ ምክር መስጠቷንና የኢትዮጶያ መንግስ አቋም ከበረታ ምንም ማድረግ እንደማይቻል ለትህነግ ሰዎች ማስታወቃቸውን በዜናው ማካተታችን ይታወሳል።


ትህነግ ትጥቅ ለመፍታት ወሰነ – ቴዎድሮስ አድሃኖም አብይ አህመድን በስልክ ተማጸኑ፤ አዲግራት መከላከያ መዳፍ ገባች

“ከውጭም ሆነ ከውስጥ በትህነግ ተስፋ የቆረጡ ቁርጠኛ አቋማቸውን በገሃድ ባያስታውቁም፣ ነገሮች ሁሉ መገለባበጣቸውን እያመኑ ነው” ሲሉ የሚናገሩ፣ በዚህ ስሜት ላይ የመንግስት ጦር አዲግራትን ከተቆጣጠረ በደቡብ አፍሪካው ንግግር ትህነግን ከሚወክሉ አካላት ጋር ምን ዓይነት ስምምነት እንደሚደረግ ከወዲሁ መገመት አዳጋች እንዳልሆነ እየገለጹ ነው።


ከስር ጉዳዩን አስመልክቶ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር የዘገበውን ያንብቡ።

የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና የህወሓት የሰላም ንግግር መራዘም፤ ሁለቱ ወገኖች “የተራራቀ” አቋም ይዘው ወደ ደቡብ አፍሪካ ማምራታቸውን እንደሚጠቁም የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቃባይ ተናገሩ። ቃል አቀባዩ ኔድ ፕራይስ በአፍሪካ ህብረት መሪነት የሚካሄደው የሰላም ንግግር የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ህወሓት “ልዩነታቸውን የሚወያዩበት እና በመካከላቸው ያለውን ርቀት ማጥበብ የሚቀጥሉበት እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን” ብለዋል። 

ቃል አቃባዩ ይህን ያሉት፤ ስምንተኛ ቀኑን ስላስቆጠረው የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት የሰላም ንግግርን በተመለከተ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ትላንት ምሽት በሰጡት መግለጫ ነው። ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የተጀመረው የሰላም ንግግር እስከ እሁድ ጥቅምት 20 እንደሚቆይ የደቡብ አፍሪካ መንግስት አስታውቆ የነበረ ቢሆንም፤ ንግግሩ እስከ ትላንት ምሽት መቀጠሉን ከቦታው የወጡ ዘገባዎች አመልክተዋል።

በፕሪቶሪያ ከተማ እየተካሄደ ለሚገኘው ለዚህ የሰላም ንግግር የተቀመጠ የቀን ገደብ እንደሌለ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ቃል አቃባይ ኤባ ካላንዶ ትላንት ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ተናግረዋል። በንግግሩ ላይ በ“ተሳታፊነት እና በታዛቢነት” እየተካፈሉ የሚገኙት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር፤ ንግግሩ እስከሚያበቃበት ዕለት ድረስ በደቡብ አፍሪካ እንደሚቆዩ ኔድ ፕራይስ ተናግረዋል።

  • – የንግግር ሂደቱ “ብዙ ጣልቃገብነት” እንዳጋጠመው ጠ.ሚ ዐቢይ ገለጹ – በዜናው አብይ አህመድ ጣልቃ ገብነቱ ከየአቅጣጫው እንደሆነ ገልጸዋል። ሊንኩን ተጭነው ያንብቡ

የሰላም ንግግሩ እስከ ረቡዕ ድረስ ይቀጥላል መባሉ የሂደቱን አለመሳካት ያመልክት እንደሆነ የተጠየቁት ፕራይስ፤ ሁለቱ ወገኖች “የተራራቀ” አቋም ይዘው ወደ ደቡብ አፍሪካ ማምራታቸውን የሚጠቁም ነው ብለዋል። የሰላም ንግግሩ መራዘም ሁለቱ ወገኖች “አብረው ለመቀመጥ ፈቃደኛ ሆነው መቀጠላቸውንም አመላካች” ጭምር ሊሆን እንደሚችልም ጠቁመዋል። የደቡብ አፍሪካው ውይይት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ህወሓት “ልዩነታቸውን የሚወያዩበት እና በመካከላቸው ያለውን ርቀት ማጥበብ የሚቀጥሉበት እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን” ሲሉም ሀገራቸው ከሰላም ንግግሩ የምትጠብቀውን አመልክተዋል። 

ፕራይስ በትላንቱ ዕለታዊ ጋዜጣዊ መግለጫቸው፤ በኢትዮጵያ ተፋላሚ ወገኖች መካከል የሚደረገው የሰላም ንግግር አራት ግቦች እንዳሉት አስረድተዋል። አፋጣኝ የግጭት ማቆም ላይ መድረስ፣ ለተቸገሩ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሰብዓዊ ዕርዳታ ማድረስ፣ የሰላማዊ ሰዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ተጨማሪ እርምጃዎች መውሰድ እና የኤርትራ ወታደሮች ከሰሜን ኢትዮጵያ መውጣታቸውን ማረጋገጥ ፕራይስ የጠቀሷቸው የሰላም ንግግሩ አራት ዋነኛ ዓላማዎች ናቸው። በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ የሚገኘው የሰላም ንግግር ሁለቱ ወገኖች ”ልዩነቶቻቸውን ለማጥበብ” እና ለአራቱ ግቦች ስኬት “መልካም ዕድል” እንደሆነ ቃል አቃባዩ ጠቅሰዋል። 

ከነገ በስቲያ ሐሙስ ጥቅምት 24፤ 2015 ሁለተኛ ዓመቱን በሚደፍነው የሰሜን ኢትዮጵያዊው ጦርነት የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እና ግፎች መፈጸማቸውን ያጋለጡ በርካታ ተአማኒ ሪፖርቶች መኖራቸውን በጋዜጣዊ መግለጫቸው ያስታወሱት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቃባይ፤  የሰላማዊ ሰዎችን ደህንነት መጠበቅ አሁንም “አንገብጋቢው ጉዳይ” እንደሆነ ጠቅሰዋል። “በግጭቱ ወቅት በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን የሚገልጹ ሪፖርቶች እጅግ እንደሚያሳስቡን በድጋሚ እንገልጻለን” ያሉት ኔድ ፕራይስ፤ ሁሉም ታጣቂ ኃይሎች መሰል ጥቃቶች አቁመው ለሰላማዊ መፍትሔ ዕድል እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በትላንቱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መግለጫ ላይ በተሳተፉ ጋዜጠኞች ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል፤ የኢትዮጵያ መንግስት “ያልተረጋገጡ እና ፖለቲካዊ ዓላማ ያላቸውን ውንጀላዎች” ከሚያቀርቡ ከአንዳንድ ሀገራት እና ተቋማት ጋር ያለውን ግንኙነት መልሶ ለማጤን እንደሚገደድ ማስታወቁን የተመለከተ ይገኝበታል። የኢትዮጵያ መንግስት ላቀረበው ውንጀላ ያቀረበውን “መረጃ” እና “ዓላማውን” መመልከት እንደሚኖርባቸው የገለጹት ኔድ ፕራይስ፤ “የዩናይትድ ስቴትስ ዓላማ፤ በአፍሪካ ህብረት መሪነት የሚካሔደው የሰላም ንግግር ግብ ቀላል ነው። ድብቅ የፖለቲካ ዓላማ የለውም” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

በደቡብ አፍሪካ እየተካሔደ ያለውን የሰላም ንግግር በተመለከተ በሳምንቱ መጨረሻ ከቻይናው ሲቲጂኤን የቴሌቭዥን ጣቢያ ጋር ቃለ መጠየቅ ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ፤ “ከግራ እና ከቀኝ የሚደረጉ ጣልቃ ገብነቶች” የሰላም ንግግሩን “ከባድ” ሊያደርጉ እንደሚችሉ ስጋታቸውን ገልጸው ነበር። “ህወሓት የአገሪቱን ህግ እና ህገ መንግስቱን እንዲያከብር ለማሳመን እየሞከርን ነው” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “ጥቅማችንን ተረድተው፤ በህገ መንግስታቸው አምነው በዚሁ መሰረት ቢሰሩ ኖሮ ሰላም ይፈጠር ነበር” ሲሉ ተደምጠዋል።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
አሰሪዋን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የተጠረጠረችው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለች
Public backs gov’t to weed out black market culprits
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2