Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  ቦቆጣቦ – ዘረኝነትን በፍቅር የወጋች መንደር!

ቦቆጣቦ – ዘረኝነትን በፍቅር የወጋች መንደር!

Ethioreview newsEthioreview news—December 18, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ቦቆጣቦ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን በቁጭ ንዑስ ቀበሌ የምትገኝ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦችን መተሳሰብና መደጋገፍ በተግባር ያሳየች መንደር ናት። ይች መንደር ከቡሬ ከተማ 55 ኪሎሜትር ላይ ተገኛለች። ከቡሬ ጉትን እስከ ነቀምት በሚዘልቀው መንገድ ከአባይ ወንዝ ድልድይ መዳረሻ ላይ ትገኛለች። ቦቆጣቦ በማደግ ላይ የምትገኝ አነስተኛ መንደር ብትኾንም፣ መተሳሰብ እና መተባበር የነገሰባት መንደር ናት።

የዘር ፓለቲካ የወለደው ዳፋ ንጹኀን ዜጎችን ለማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ምስቅልቅል እየዳረገ በሚገኝበት በዚኽ ወቅት ቦቆጣቦ “እምቢ ለዘረኝነት” በማለት ኢትዮጵያን በፍቅርና መተሳሰብ በማጽናት ላይ ያለች መንደር ናት።

በቦቆጣቦ የአማራ እና ኦሮሞ ሕዝቦች ዘመንን በተሻገረ የማይናወጥ መተሳሰብ እና ፍቅር ይኖሩባታል። በዚች አነስተኛ መንደር የሚስተዋለው ብሔርና ማንነት ሳይቆጠር አንዱ ለአንዱ የመኖር ምስጢር በዘረኝነት በሽታ ለታመመ ሁሉ ትምሕርት ሰጭ ነው።

አቶ በላይ በቀለ የኦሮሞ ማንነት ያላቸው የቦቆጣቦ ነዋሪ ናቸው። ቦቆጣቦ የአማራ እና ኦሮሞ ሕዝቦች የዓባይ ወንዝ ሳይገድባቸው በጋራ ሠርተው፣ በጋራ ደስታና ችግርን ተካፍለው ይኖራሉ፣ በቅርብ ርቀት በሚገኘው ወለጋ ላይ የዜጎችን ሕይወት እየቀጠፈ ያለው በጥላቻ የሰከረ የዘር ፖለቲካ ልባቸውን ቢሰብረውም ተሳስበው የሚኖሩባትን ቦቆጣቦ ሲያስቡ ደግሞ ይጽናናሉ። አማራነት እና ኦሮሞነት የቦቆጣቦ ባለብዙ መልክነት እና ጌጥ ናቸው ሲሉም ይገልጻሉ። ቦቆጣቦ ሁለቱ ሕዝቦች በፍጹም ወንድማማችነት እና መተሳሰብ የሚኖሩባት ስለመኾኗም አቶ በቀለ ተናግረዋል።

More stories

በሳኡዲ በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ያሉ ዜጎችን ለማስመለስ የተቋቋመው ብሄራዊ ኮሚቴ ባዘጋጃቸው ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ

February 28, 2022

ሚሊየነሩ ሜዳ ላይ – ይህ ጉድ የተፈጸመው ዝዋይ በዘረኞች ነው፤ መርጦ አልቃሽ “ሚዲያዎች” እፈሩ

March 14, 2023

የመስከረም የምግብ ዋጋ ንረት በ10 ዓመታት ከተመዘገበው ትልቁ ሆነ

October 7, 2021

ብጉር | Acne vulgaris

August 24, 2023

ወደ ቡሬ እና ባሕር ዳር እንዲኹም ዓባይን ተሻግሮ ወደ ጉትን እና ነቀምት ምርት የሚጫንባት፣ ንግድ የሚካሄድባት የልማት መንደር ስለመኾኗም ይመሰክራሉ። ይኹን እንጅ በወለጋ አሸባሪው ሸኔ በንጹኀን ላይ በሚደርሰው ጥቃት ነቀምት ለመሻገር የሚያስችለው የዓባይ ወንዝ ድልድይ ዝግ መደረጉን ገልጸዋል። የመንገዱ መዘጋት ለሁለቱም ክልል ሕዝቦች ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እና ማኅበራዊ መስተጋብር እንቅፋት መኾኑንም አቶ በላይ አስረድተዋል።

አቶ በላይ በወለጋ እየደረሰ ያለው የአማራዎች ሞትና እንግልት፤ አሸባሪው ሸኔን በሚታገሉ ኦሮሞዎች እየተፈጸመ ያለው ጥቃት ዘላቂ እልባት አግኝቶ ሰላም እንዲሰፍን መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ መውሰድ እንዳለበት ጠይቀዋል። ከባሕር ዳር እና ቡሬ አካባቢ ወደ ነቀምት ከፍተኛ የኾነ የእህል እና ሸቀጣሸቀጥ ጉዞ እንደነበር ያስታወሱት አቶ በላይ ሁለቱም ሕዝቦች ወደተለመደው የንግድ እንቅስቃሴ እንዲመለሱ መንግሥት የአካባቢውን ሰላም አስጠብቆ መንገዱን ለትራፊክ ክፍት ማድረግ አለበት ነው ያሉት።

የፖለቲካ ነጋዴዎች የተለያየ ስም እየተሰጣቸው በወለጋ ውስጥ በአማራዎች ላይ የሚፈጽሙት ግድያ እና እንግልት ባስቸኳይ መቆም እንዳለበትም መልእክት አስተላልፈዋል።

አቶ ኑርልኝ ገላው የአማራ ማንነት ያላቸው በቁጭ ንዑስ ወረዳ ቦቆጣቦ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ከአቶ በላይ ጋር ኾነው የጋራ ሰላማቸውን ለመጠበቅ በዓባይ ድልድይ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ ነው ያገኘናቸው። አቶ ኑርልኝ ልክ እንደ አቶ በላይ በቦቆጣቦ የሚኖሩ የአማራ እና የኦሮሞ ሕዝቦች ለዘመናት ስለዘለቀው አንድነትና ፍቅር አንስተው አይጠግቡም። ነዋሪዎች በደስታም ኾነ በሐዘን ጊዜ የማይለያዩ፣ ለዘመናት የተጋመደ መስተጋብር እና ፍቅር ያለቸው መሆኑን ተናግረዋል። አማራው ወደ ነቀምት ኦሮሞው ወደ ቡሬ በመንቀሳቀስ ከፍተኛ የኾነ የንግድ ልውውጥ ሲያደርግ ቦቆጣቦ መገናኛ ድልድይ መኾኗንም ገልጸዋል።

አቶ ኑርልኝም የመንገዱ መዘጋት እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። ከወለጋ በመፈናቀል ረጅም እና እንግልት የበዛበት የእግር ጉዞ አድርገው ወደ አማራ ክልል የሚገቡ ወገኖችን እየተቀበሉ እንደሚያሳርፉም ተናግረዋል። “ጉዳዩ እጅግ አሳሳቢ ነው” ያሉት አቶ ኑርልኝ መንግሥት አስቸኳይ መፍትሔ በማስቀመጥ ዜጎችን ከግድያ እና እንግልት መጠበቅ አለበት ብለዋል።

የቦቆጣቦ ነዋሪዎች መተሳሰብ እና ፍቅር ወደ ወለጋ ተሻግሮ በኢትዮጵያም በዝቶ፣ የዜጎች ግድያ እና እንግልት በፍቅር በሻረ ብለን ተመኘን። ቦቆጣቦ ዘረኝነትን በፍቅር የወጋች የሀገር ተምሳሌት መንደር!።

ዘጋቢ:- አሚናዳብ አራጋው (አሚኮ)

SOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Lies, Deceit and Aid: New Revelations about the World Food Programme’s conduct and the TPLF
መንግስት ል ዑካን ከላከ በህይዋላ በማላዊ 245 አስረኞች በምህረት አንዲፈቱ ተውሰነ፤ ስድስት ተጠርጣሪዎች ተያዙ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2