“በአንድ ልብ፤ በአንድ ሃሳብ የተወሰነ ነው” ሲሉ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ ማስታወቃቸው ተዘገበ። ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ተቀምጦ እያለ ተከበበ፣ በወታደሮች ትጥለቀለቀ፣ ህዝብ ሁኒታውን ተከታተል፣ በግድ የማይፈለጉ ሰዎችን እንዲሾም መሳሪያ ተመዞባቸዋል ….ወዘተ በሚል ዜና ሲሰራጭ ቢውልም፣ በስተመጨረሻ ውሳኔውም ሆነ ስብሰባው በምን መልኩ እንደተካሄደ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ አመልክተዋል።
“ሁላችንም ተወያይተንበት፣ ቤተክርስቲያንን የሚጠቅማት ምንድነው? ብለን በአንድ ልብ በአንድ ሃሳብ የወሰንነው ነው። በእውነት ደስ የሚል ነበር፤ ለዚህም እግዚአብሔርን እናመሰግናለን” ሲሉ ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ ተናግረዋል።
አቡነ ጴጥሮስ አክለውም “ብዘዎች የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንደነበራችሁ እናውቃለን፤ አንዳንዴ እውነት ነው፤ ብዙ ጊዜ ግን ወሬ ይበዛዋል !… በዚህ ሚዲያ በበዛበት ዘመን … ” ሲሉ ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ በለሆሳስ ሲሰራጭ የነበረውን ወሬና ቅስቀሳ አጣጥለዋል።
ሰፊ ቅስቀሳና ህዝብ በነቂስ ለመውጣት እንዲዘጋጅ ጥሪ የቀረበበት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ውሎው ችግር ባለባቸው እና አስፈላጊ በሆኑባቸው አህጉረ ስብከት ዘጠኝ አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ ውሳኔ ማሳለፉ ተገልጿል። ሹመቱም ወደፊት ይፋ እንደሚሆን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ አስታውቀዋል።

ይህ የተገለጸው የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን በተመለከተ አጭር መግለጫ በሰጡትበት ወቅት ነው። መግለጫውን ተከትሎ የሃሰት መረጃና ጥሪ ሲያሰሙ የነበሩ አካላት ይቅርታም ሆነ ማስተካከያ ዜና አልቀረቡም።
” የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በሰላም እና ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቋል።” ሲሉ አቡነ ጴጥሮስ ማስታወቃቸውን ተከትሎ የሚጠብቃቸው ነቀፌታና ተቃውሞ እስካሁን ለአየር ባይበቃም እንደማይቀርላቸው አካሄዱን የሚያውቁ እየገለጹ ነው።
“ዛሬ የመጨረሻው አጀንዳ ላይ ብዙ ውይይት ተካሂዷል። በመጨረሻ ሁሉም አባቶች ተወያይተው ቤተክርስቲያንን የሚጠቅመው ምንድነው ? የሚለው ላይ በመምከር ዛሬ ውሳኔ ተላልፏል።” ብለዋል።
የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት እንዲካሄድ ተወስኗል። የመጀመሪያው ችግር ያለባቸው ሀገረ ስብከት የሚል ሲሆን አሁን ሰባት አባላት ያሉት ኮሚቴ ተቋቁሟል እነሱ በሚያቀርቡት ጥናት ሹመት ይካሄዳል። የሹመቱ ቀን ወደፊት ይገለፃል። ዋናው ነገር ለቤተክርስቲያን የሚጠቅመው የትኛው ነው ? የሚለውን የጉባኤው አባላት በሙሉ ተስማምቶ ፣ በአንድ ልብ፣ በአንድ ሃሳብ፣ በመነጋገር ውሳኔ መተላለፉን ዋና ጸሃፊው አረጋግጠዋል።
ረቡዕ የማጠቃላይ መግለጫ በቅዱስ ፓትርያኩ እንደሚሰጥ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ተናግረዋል። “ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን፤ ምዕመናን በሙሉ ተጨንቃችኃል፤ አንዳንድ ጊዜ እውነት ነው ሌላ ጊዜ ወሬም ብዙ ይበዛል በዚህ ሚዲያ በበዛበት ዘመን በጣም ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን ፤ በእውነት እግዚአብሔርን እናመሰግናለን ግሩም የሆነ የትምህርት ጊዜ፣ ግሩም የሆነ የውይይት ጊዜ ፣ ቤተክርስቲያን ለይተን የምትፈልገው ምንድነው የሚለውን የተወያየንበት ጊዜ ነው” ሲሉም ለቤተክርስቲያኒቷ ቤተሰቦችና ዜናው ላሳሰባቸው ሁሉ የእረፍት መልዕክት አስተላልፈዋል።
አዲስ አበባ ከብልጽግና ከፍተኛ አመራሮችና የመከላከያ አዛዦች ጋር አብሮ ሲሰራ የነበረው አቶ መሳይ መኮንን “ሁለት አስቸኳይ መረጃዎች” ሲል “ቤተክርስቲያን አካባቢ ጥሩ ነገር የለም” ሲል መነግስት የስብሰባውን ውጤት ለመቀልበስ የኦሮሚያ ብልጽግና የፖሊስና የደህንነት ሃይል ማሰማራቱን አመልክቶ ነበር።
በሌላ መረጃ ከሲኖዶስ ስብሰባ ጋር ያለው ግንኙነት ግልስ ባይደረገም የኦነግ ሰራዊት ከተሞችን እየተቆጣጠረ ግምቱን አስቀምጦ መረጃ አሰራጭቶ ነበር።
ዋሱ በቴሌግራም ገጹ ፎቶ አስደግፎ ” ቅዱስ ሲኖዶሱ ስብሰባ ላይ መሆኑ ይታወቃል።ፎቶው ሲነሳ ቀንና ሰዓት ይመዘግባል። እኔ አሁን ስብሰባው በሚካሄድበት በር ላይ እያለፍኩ ነው።የፀጥታ ሀይሎች ሲርመሰመሱ ያየሁበት ነገር የለም።ከፍ ብሎ አንዲት የፌደራል ፖሊስ ፓትሮል ተመልክቻለሁ።ያለው ነገር ይሄ ነው።ሠላምን እንመኝ።መልካም ነገሮችን ያብዛልን ለማለት ነው” ሲል ምስክርነቱን ሰጥቷል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሃፊ እውነቱን ካስታወቁ በሁዋላ አንዳችም ማስተባበያ ይህ እስከታተመ ድረስ አልተሰማም።
ይህን አስመልክቶ አስተያየት የሰጡ ” ውሸት የተለመደ ነው። ውሸታም ሚዲያን ሁለተኛ አላድምጥም የሚልም የለም። በሰበር መረጃ ሃሰት ሲረጭ የሚቀበሉ ሃሰቱ ሲገለጽ ለምን እንደተዋሸ የሚመረምሩ አለመኖራቸው፣ እንዲያውም በማህበራዊ ሚዲያው ሰፈር ውሸታሞችን የሚያምኑ መበራከታቸው አሳሳቢ ነው”
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ እስከታተመ ድረስ ቴዲም ሆነ የተጠቀሱት አካላት ስለሚሰሙት ቁጥር ስፍር የሌላቸው መረጃዎች በአዎንታም ሆነ በአሉታ አልተነፈሱም። ነገሮችን በጥሞና የሚከታተሉ “ቴድሮስ ራሱ ወይም አግባብነት ያላቸው ሃቁን ለህዝብ ለምን አይናገሩም? ህዝብ ሲተራመስ ዝም የሚሉት ለምንድን… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ ግለሰቦች የኋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማህበርን ዓመታዊ እራት ለመታደም ተሰብስበዋል። ከ2600 ባልይ እንግዶች ፊት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ቀዳማዊት እመቤት ሜላኒያ ትራምፕ በክብር መድረኩ ላይ ተቀምጠዋል። ሴሽታው እየተጠበቀ ባለበት ሰዓት ድንገት አዳራሹን… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም አውርደው ብዙም ሳይቆዩ አሁን ወዳሉበት ደረጃ ደረሱ። የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምንት መፈረሙን ተከትሎ ያኮረፉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ፣ ሰሞኑን አሜሪካ መልሳ ልትዋዳጃቸው ማቀዷ ተሰምቷል። ዜናው መልካም ቢሆንም ኢሳያስ ግን አይቀበሉትም የሚል አስተያየት እየተሰጠ ነው።… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድንገተኛ አደጋ ጊዜ እርስ በርስ የሚረዱበትን አዲስ የጋራ መከላከያ ስምምነት ረቂቅ ለማዘጋጀት መስማማታቸውን አስታወቁ። በቆጵሮስ አስተናጋጅነት በተካሄደው የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ላይ የተወሰነው ይህ ውሳኔ፣ አውሮፓ በራሷ የመከላከያ አቅም ላይ እንድትተማመን ለማድረግ የታለመ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች ስህተት” መሆኑን ጽህፈት ቤታቸው አስታወቀ። ምርመራው ቀጥሎ ማስተባበያው ሃሰት ከሆን የከፋ ቀጣት ይጠበቃቸዋል። ባለፉት ጥቂት ወራት የወጡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት፣ የኢልሀን ኦማር እና የባለቤታቸው ቲም ማይኔት ሀብት ከ51,000 ዶላር ወደ 30 ሚሊዮን ዶላር… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች







