“ሠራዊቱ በወገኖቹ የተካደበትን ቀን ሁሌም እንዳይደገም እንዘክረዋለን” ፦ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
“እንዳይደገም ሁሌም እንዘክረዋለን” በሚል መሪ ቃል ሰሜን ዕዝ የተጠቃበት 3ኛ ዓመት የመታሰቢያ መርሃ-ግብር ተካሂዷል።
ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ደንበር እየጠበቀ ሰብል እየሰበሰበ የአንበጣ መንጋን እያባረረ ኮቪድ ወረርሽኝን በመከላከል አሰተዋጽኦ አበርክቶ በድካም ጋደም ባለበት በወገኖቹ ተክዶ ጥቃት የተፈፀመበት እና በኢትዮጵያ ታሪክ ጥቁር ጠባሳ የተመዘገበበት ቀን ነው ብለዋል የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ።
በአለም ታሪክ ለግል ስልጣንና ጥቅም ዘርና ወገን ለይተው ራሳቸው ባደራጁት የራስን ጠባቂ እና ጋሻ የሆነ ሠራዊት በጭካኔ በመጨፍጨፍ ሀገርን ያለጠባቂ መስቀረትና መንግስትን ለመጣል ሙከራ የተደረገበት ለኢትዮጵያ መከራ ጥሎ ያለፈ ቀን መሆኑን ያነሱት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ መከላከያ ሠራዊቱ በትግራይ ክልል ትሞህርት ቤቶችን እየገነባ የጤና ኬላ እየሠራ እና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን እያስፋፋ አቅም የሌላቸውን ተማሪዎች አስተምሮ ለቁም ነገር ሲያበቃ ቆይቷልም ብለዋል።
ህዝቡ ከሠራዊቱ ጋር ተዛምዶ ተዋልዶና ቤተሰብ ሆኖ በኖረበት ክልል በፀንፈኛ ፖለቲከሀኞች ምክንያት ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት በሠራዊታችን ላይ መፈፀሙን ጠቁመው ቀኑ ዛሬም ነገም ሁሌም ይዘከራል መላው ኢትዮጵያዊም ይህ ድርጊት እንዳይደገም መዘከር ሠላም እንዲመጣ ማስታወስ ይገባዋል ብለዋል ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ።
መከላከያ ጦርነቱ እንዳይካሄድ ያደረገው ጥረት ዋጋ ከማስከፈሉም በላይ የትግራይ ህዝብ ወገናችን ስለሆነ ሠራዊቱ ግዳጅ እንዳይወጣ አግደንም ነበር ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሀገሪቱ በተለያዩ ቦታዎች ፖለቲከኞች በሚፈጥሩት ሴራ ሀገሪቱ እና መላው ህዝብ ለችግር ተዳርገዋል ይህን ለመቀልበስ መከላከያ ሠራዊቱ ከፍተኛ ዋጋ እየከፈለ መሆኑንም ተናግረዋል።
የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጦርነቱ በሁሉም ወገኖቻችን ላይ ያደረሰው ጉዳት የኢትዮጵያ ጉዳትና መከራ በመሆኑ ከዚህ ታሪክ መላው ኢትዮጵያዊ ተምሮ እንዳይደገም መዘከር ይገባዋል ካሉ በኋላ ሁሉም ህዝብ ለሠላም መሥራት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ዕለቱን በተመለከተ በጀኔራል መኮንኖች የፓናል ዉይይት የተካሄደ ሲሆን የፓናል ዉይይት መድረክን የመሩት በኬንያ ባለሙሉ ስልጣን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጄኔራል ባጫ ደበሌ በበኩላቸው ጥቅምት 24 ቀንን መዘከር ትልቅ ትርጉም አለው የተፈጠረው ነገር ከልባችን ተፀፅተን ለሠላም በህብረት ልንተጋገዝ ይገባል ብለዋል።
የሰሜን ዕዝ መከላከያ ሠራዊት አባላት በወገናቸው ጭካኔና ግፍ በተሞላበት ሁኔታ የተካዱበት 3ኛ ዓመት መታሰቢያ መርሃ ግብር በመከላከያ ጠቅላይ መምሪያ ጄኔራል መኮንኖች ከፍተኛ መኮንኖች የሠራዊት አባላትና ከሲቪል መህበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት በተለያዩ ዝግጅቶች ታስቦ ውሏል።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቅዳሜ ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ.ም
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም።… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች







