በደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያዊው በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድሎ አስክሬኑ ከተሽከርካሪው ጋር ተቃጥሎ መገኘቱን የሟች ጓደኞችና ቤተሰቦች ገለጹ ፡፡ የሟች ጓደኞች ለዶቼ ቬለ እንደገለጹት የ35 ዓመቱ ኢትዮጵያዊው መሳፍንት ኢያሱ ባለፈው ቅዳሜ ተገድሎ የተገኘው በአገሪቱ ሰሜን ምዕራብ በምትገኘው ራስተንበርግ በተባለች ከተማ ውስጥ ነው ፡፡
በዕለቱ በአንድ ምግብ ቤት ውስጥ ከሚያውቃቸው ሰዎች ጋር ምግብ በመመገብ ላይ እንደነበር የጠቀሱት የሟች ጓደኞች ሀብታሙ ታደሰ እና ጀማይካ ላቢሶ “ በመኻል የሥልክ ጥሪ ተቀብሎ መጣው ብሎ ነው በመውጣት በዛው ሳይመለስ ቀርቷል፡፡
በነጋታው ግን ተገድሎ ከነተሽከርካሪው መቃጠሉን ከፖሊስ ሰማን ፡፡ አስከሬኑ ሙሉበሙሉ በመቃጠሉ ማንነቱን ለመለየት አስቸጋሪ ነበር ፡፡ ይሁንአንጂ ከቃጠሎው በተረፈው የተሸከርካሪው ሠሌዳ አማካኝነት ሊታወቅ ተችሏል “ ብለዋል ፡፡
መሳፍንት ወደ ደቡብ አፍሪካ ከገባበት ከ2010 ዓም ጀምሮ በግል ሥራ በመተዳደር ቤተሰቦቹን ሲረዳ መቆየቱን የተናገሩት የሟች የቅርብ ዘመድ አሳምነው አብረሃም “ ግድያው በአጋጣሚ ነው የሚል አምነት የለንም ፡፡
ምንአናልባት ከዚህ በፊት በሚያውቁት ሰዎች ታስቦበት የተፈጸመ ይመስላል ፡፡ ይህን ያደረጉ ሰዎች ለፍትህ እንዲቀርቡ እንፈልጋለን “ ብለዋል ፡፡
ዘገባ DW



