Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ በ6 ግለሰቦች ላይ የ15 ቀን ክስ የመመስረቻ ጊዜ ተፈቀደ
law

በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ በ6 ግለሰቦች ላይ የ15 ቀን ክስ የመመስረቻ ጊዜ ተፈቀደ

Ethioreview newsEthioreview news—August 16, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በከባድ የሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እና ምክትል ፕሬዚዳንትን ጨምሮ በ6 ግለሰቦች ላይ የ15 ቀን ክስ የመመስረቻ ጊዜ ፈቀደ።

ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን የክስ መመስረቻ ጥያቄንና የተጠርጣሪ ጠበቆችን የመከራከሪያ ነጥብ ተመልክቷል።

ተጠርጣሪዎቹ 1ኛ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሀብታሙ አበበ አጊሾ ( ዶ/ር)፣ የዩኒቨርሲቲው አካዳሚና ምርምር ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ታምራት ታገሰ ተኮራ (ዶ/ር)፣ 3ኛ ኮንትራክተር የሆነው ደሳለኝ አስረዳ፣ 4ኛ የዩኒቨርሲቲው የግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ኃላፊ ሙላቱ ኤርትሮ ጡንዳዳ፣ 5ኛ የዩኒቨርሲቲው የፋይናንስ ዳይሬክተር ማርቆስ ዮሃንስ ረገዮ እና የቀድሞ የአዋሽ ባንክ ሆሳህና ቅርጫፍ ስራ አስኪያጅ የነበረው መለሰ ግርማ ኤርጋኖ ናቸው።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ደቡብ ቅርጫፍ መርማሪ የምርመራ ስራውን አጠናቆ የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቤ ሕግ ማስረከቡን ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ አስታውቋል።

More stories

ግማሽ ሚሊየን ብር በጥሬው ሲቀበል እጅ ከፍንጅ የተያዘው ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ

February 1, 2022

ዐቃቤ ህግ በቀድሞ የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የክስ መዝገብ ሌሎች ድርጅቶችን አካቶ ለመቅረብ ጠየቀ

July 7, 2023

በሰሜን ኢትዮጵያ ባለው ግጭት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመመርመር የተቋቋመው የሚኒስቴሮች ግብረ-ሀይል ስራውን በይፋ ጀምሯል

November 29, 2021

ሰው በማገት ወንጀል የተከሰሱ ሁለት ግለሰቦች 22 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት ተፈረደባቸው

February 16, 2022

ከዚህም በኋላ የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ በመዝገቡ ላይ ተሰይሞ ተጠርጣሪዎች የተጠረጠሩበትን መነሻ ጉዳይ በዝርዝር ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ አቅርቦ የ15 ቀን ክስ መመስረቻ ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቋል።

በዚህም ተጠርጣሪዎቹ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ለንግስት ኢሌኒ መታሰቢያ ሆስፒታል የኦክስጂን ማምረቻ ለማስገንባት መቀመጫውና ዋና መስሪያ ቤቱን ካናዳ ቶሮንቶ ካደረገ ኤ.ኤ.ኤም. ኢዲ ቴክኖሎጂ ኢንካ ለተባለ ድርጅት የመንግስትን የግዢ መመሪያው ባልጠበቀ መንገድ በአምስት አመት አፈጻጸሙ እየታየ መከፈል የሚገባውን አሰራር በመተላለፍ በውል ላይ የተዘረዘሩ ስራዎች ሙሉ በሙሉ ባልተሰሩበት ሁኔታ ለድርጅቱ የ57 ሚሊየን 383 ሺህ 956 ብር ከ72 ሳንቲም ለታለመለት አላማ ሳይውል በመክፈል ጉዳት እንዲደርስ በማድረግ፤

በተለይም የውል ማስከበሪያ የውሉን ጠቅላል ዋጋ 10 ከመቶ ማለትም 117 ሚሊየን 10 ሺህ 859 ብር ከ60 ሳንቲም የውል ማስከበሪያ ሳይቀርብ እና ስራውም በውል ላይ በተገለጸው ጊዜ ሳይጠናቀቅ በመቅረቱ ይህ የውል ማስከበሪያ ዋስትና ቀርቦ ቢሆን ኖሮ ለመንግስት ገቢ መደረግ የነበረበትን ጥቅም አሳጥተዋል በሚል የተጠረጠሩበትን ወንጀል ዐቃቤ ሕግ በክስ መመስረቻው ላይ በዝርዝር አቅርቧል።

በተጨማሪም ደሳለኝ አስረደ የግንባታ ስራ ተቋራጭ ደግሞ የመምህራን መኖሪያ ቤት 2 ህንጻ ግንባታ ስራ ግንቦት 2013 ዓ.ም እና ጥር ወር 2016 ዓ.ም በተገባው ውል መሰረት ለዚሁ ህንፃ ተቋራጭ በተጋነነ ዋጋ በመስጠት 272 ሚሊየን 170 ሺህ 210 ብር ከ60 ሳንቲም ያለአግባብ ለተጨማሪ የግንባታ ወጪ መደረጉ፤ ክፍያ በመፈጸም በዚህ ልክ በመንግስት ላይ ጉዳት በማድረስ እና ለውለታ 26 ሚሊዮን ብር ጥቅም ማስገኘትና ማግኘት የሚል የጥርጣሬ መነሻም በዐቃቤ ሕግ በኩል ቀርቧል።

እንዲሁም በዝምድና እና በትውውቅ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ባለቤት እህት እና ሌሎች ሁለት ሰራተኞች ባልሰሩት ስራ በአበል መልክ የዩኒቨርሲቲውን ገንዘብ ያለአግባብ በመመዝበር ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት የደረሰ መሆኑን ዐቃቤ ሕግ ጠቅሷል።

ተጠርጣሪዎች ከሌሎች እጃቸው ለጊዜው ካልተያዙ ተጠርጣሪዎች ጋር በመመሳጠር በመንግስት ላይ 487 ሚሊየን 333 ሺህ 912 ብር ከ78 ሳንቲም ጉዳት እንዲደርስና ለሌሎች ያልተገባ ጥቅም እንዲያገኙ የተደረገ መሆኑን ጠቅሶ ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል የተጣራባቸውና የምርመራ መዝገቡን ነሐሴ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ከመርማሪ ፖሊስ እንደደረሰው ለችሎቱ አቅርቧል።

የምርመራ መዝገቡ ውስብስብ መሆኑን የጠቀሰው ዐቃቤ ሕግ መዝገቡን በጥልቀት መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ሰፋ ያለ ጊዜ እንደሚያስፈልገው ገልጾ በተመሳሳይ ወንጀል የተጠረጠሩ ሌሎች ተጠርጣሪዎች ያሉ እና ጉዳያቸው በአንድ መዝገብ የተጣራ በመሆኑ በአንድ ላይ ክስ ለማዘጋጀት በወ/መ/ስ/ስ /109 /1 መሰረት የ15 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።

የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው በዐቃቤ ሕግ የቀረበው ዝርዝር የጥርጣሬ መነሻ ተጠርጣሪዎቹ የተሳትፎ ደረጃ ያልቀረበበትና በጥቅል ወንጀል ተፈጽሟል ተብሎ በደፈናው ክስ መመስረቻ ጥያቄ ሊቀርብ አይገባም በማለት ተከራክረዋል።

በዋናነት ዐቃቤ ሕግ ምርመራውን ሲመራ ቆይቶ እንደ አዲስ “የምርመራ መዝገቡን ተመልክቼ ለመወሰን እንድችል” ክስ የመመስረቻ ጊዜ ይፈቀድልኝ ማለቱ አግባብ አይደለም በማለት ተከራክረዋል።

በተመሳሳይ ከአበል የወንጀል ተግባር ጋር በተያያዘ ሌሎች በዋስ በተለቀቁበት ሁኔታ ላይ ከወንጀል ድርጊቱ ጋር የማይገናኙ ደንበኞቻችን በእስር እንዲቆዩ ተደርጎ የክስ መመስረቻ መጠየቁ ተገቢነት የለውም በማለት የተከራከሩ ጠበቆችም ነበሩ።

በጥቅሉ ደንበኞቻቸው ቋሚ አድራሻ ያላቸውና በየትኛውም ጊዜ ቢጠሩ መቅረብ የሚችሉ መሆናቸውን ጠቅሰው ዋስትና እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የመመርመር ስልጣን ያለው ፖሊስ መሆኑን በመጥቀስ፤ ምርመራ መምራት ማለት የህግ ድጋፍ መስጠት ማለት መሆኑን ገልጾ መልስ ሰጥቷል።

ዐቃቤ ሕግ ተፈጽሟል ባለው የወንጀል ተግባር ጥቅም የተገኘበትና በመንግስት ላይ ከፍ ያለ ጉዳት የደረሰበት መሆኑን በመግለጽ የተጠረጠሩበት ወንጀል የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ቁጥር 881/2007 መሰረት በከባድ ማለትም ከ10 ዓመት በላይ ሊያስቀጣ በሚችል ድንጋጌ ስር ሊያስከስስ እንደሚችል ጠቅሶ የዋስትና ጥያቄውን በመቃወም ተከራክሯል።

የግራ ቀኝ ክርክሩን የመረመረው የጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ዛሬ ረፋድ ላይ ለክስ መመስረቻ ጊዜ መፍቀድ ተገቢ መሆኑን ገልጾ የተጠርጣሪዎችን ዋስትና በማለፍ ለዐቃቤ ሕግ የ15 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቅዷል።

በታሪክ አዱኛ

law
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በሀሰተኛ ማንነት የወራሽነት ማረጋገጫ ከ28 ሚሊየን ብር በላይ ሊመዘብሩ ነበር የተባሉ ተከሰሱ
“ግብፅ ወታደሮቿን በሶማሊያ ለማሰማራት ያላት ፍላጎት ኢትዮጵያን አያሸብርም”
Related posts
  • Related posts
  • More from author
law

ህገወጥ የውጭ ምንዛሪ ወንጀል የፈጸሙ 123 ተጠርጣሪዎች የባንክ ሒሳብ ታገደ

September 20, 2025
law

እነ ቀሲስ በላይ በሙስና ወንጀል ሊፈርድባቸው እንደማይገባ ጠቅሰው ያቀረቡት ይግባኝ ውድቅ ሆነ

July 26, 2025
law

የአዲስ አበባ የከንቲባ ፅ.ቤት ፕሮቶኮልን ጨምሮ 12 ተከሳሾች በሌብነት ተከሰው ተፈረደባቸው

July 23, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2