Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  TIPS 1  ዶ/ር አሸብርን ጨምሮ የኦሊምፒክ ኮሚቴ አመራሮች በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ክስ ተመሰረተባቸው
TIPS 1

ዶ/ር አሸብርን ጨምሮ የኦሊምፒክ ኮሚቴ አመራሮች በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ክስ ተመሰረተባቸው

Ethioreview newsEthioreview news—September 12, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቲ ፕሬዝዳንት [ዶ/ር] አሸብር ወልደጊዮርጊስን ጨምሮ አራት አመራሮች በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር እና ሌሎች ተያያዝ ጉዳዮች ክስ ተመሰረተባቸው።

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቲም ከተከሳሾቹ መካከል ነው።

ክሱን የመሰረቱት ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ አትሌት ገዛኸኝ አበራ፣ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ቴኒስ ፌዴሬሽን ናቸው።

በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በተከፈተው የክስ መዝገብ አራት ግለሰቦች እና አንድ ተቋም በተከሳሽነት ስማቸው ተጠቅሷል።

እነዚህ ተከሳሾች የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቲ፣ፕሬዝዳንቱ አሸብር ወልደጊዮርጊስ፣ ዐቃቤ ነዋይዋ [ዶ/ር] ኤደን አሸናፊ፣ ዋና ፀሐፊው አቶ ዳዊት አስፋው እና ምክትል ፀሐፊው አቶ ገዛኸኝ ወልዴ ናቸው።

በከሳሾቹ ጠበቆች በኩል ክሱ የቀረበለት የፌደራል አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት አራድ ምድብ ችሎት ኮሚቴው፤ ግንቦት 5 እና ሰኔ 4፤ 2016 ዓ.ም. ያካሄዳቸው ጠቅላላ ጉባኤዎች እና ውሳኔዎች እንዲታገዱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

የከሳሽ ጠበቃ የሆኑት አቶ አያሌው ቢታኔ “ከፓሪስ ኦሊምፒክ ጋር በተያያዘ [ተከሳሾቹ] ሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ተሰማርተዋል ብለን እንጠረጥራለን። የወንጀል ተጠያቂነቱ እንዳለ ሆኖ ሥልጣናቸውን ያለ አግባብ በመጠቀም ኦሊምፒክ ኮሚቴውን [በዝብዘዋል]” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

አክለውም “ደብዳቤ ስለተጻፈ ብቻ የማይመለከተው ሰው [ወደ ፓሪስ] ይሄድ ነበር” ብለዋል።

ጠበቃ አያሌው “የሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን በተመለከተ ገና በወንጀል ክስ እንመጣለን። ከሚመለከተው መንግሥታዊ ተቋም ጋር የወንጀል ምርመራ መዝገብ እንዲከፈት ተደርጎ የሚሰሩ ስራዎች ይኖራሉ” ሲሉ ከክሱ ጋር በተያያዘ በቀጣይ የሚኖረውን ሂደት አብራርተዋል።

“ተቋሙ እስካሁን ድረስ ኦዲት አልተደረገም” የሚሉት ጠበቃ አያሌው፤ “የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ደብዳቤዎች ምላሽ አልሰጡም፤ ፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤትም ኦዲት እንዲደረግ ከአንድም ሁለት ጊዜ ደብዳቤ ጽፎ ኦሊምፒክ ኮሚቲው ፈቃደኛ አልሆነም” ሲሉ አስረድተዋል።

“ስለዚህ በገለልተኛ ተቋም ኦዲት ተደረጎ በሚገኘው ግኝት መሰረት ኃላፊነት ይረጋገጥ ነው” ሲሉ የሚጠይቁትን ዳኝነት ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ “ግንቦት አምስት እና ሰኔ አራት ላይ የተደረጉት አስቸኳይ እና መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተወሰኑ ውሳኔዎች የኦሊምፒክ ኮሚቲውን ህግ እና ስርዓት ያልተከተሉ እና ሕገ ወጥ ስለሆኑ በሚል እንዲሻሩ ነው [የጠየቅነው]” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

“ለእነዚህ ምክንያት ናቸው ያልናቸው ዝርዝር ነገሮች አሉ” የሚሉት ጠበቃ አያሌው፤ “አንደኛ [ዶ/ር] አሸብር፣ [ዶ/ር] ኤደን እና አቶ ዳዊት ለሶስተኛ ጊዜ ነው በሕገ ወጥ መንገድ የተመረጡት” ሲሉ የመጀመሪያውን ምክንያት ይጠቅሳሉ።

የኦሊምፒክ ኮሚቴ የስራ ዘመን ሁለት ዓመት መሆኑን የሚያነሱት ጠበቃው፤ “ነገር ግን በሕገ ወጥ መልኩ እነሱ ለሶስተኛ ጊዜ ተመርጠዋል፤ የተመረጡትም በድብቅ በተፈጸመ ጉባኤ ነው” ይላሉ።

በተጨማሪም “በሕግ የመመረጥም ሆነ የመምረጥ ሥልጣን ሳይኖራቸው አንዳንድ ግለሰቦች ተመራጭም መራጭም ሆነው በመግባታቸው ሕገ ወጥ ያደርገዋል” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

“ጠቅላላ ጉባኤውም መጠራት ከነበረበት በጣም ባጠረ ጊዜ ነው የተጠራው ስለዚህ ይሄም ሕገ ወጥ ያደርገዋል” ሲሉ አክለዋል።

ይህ አቤቱታ የቀረበለት ፍርድ ቤቱ ባለፈው ሰኞ ጷጉሜ 4፤ 2016 ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱ በዚህ የችሎት ውሎ የኦሎምፒክ ኮሚቴ ግንቦት 5 እና ሰኔ 4፤ 2016 ዓ.ም. የተካሄዱት አስቸኳይ እና መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤዎች እና የተላለፉ ውሳኔዎች ታግደው እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ከዚህ በተጨማሪ ሰኔ 4 የተመረጠው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቲ ሥራ አስፈጻሚ ምርጫም “ታግዶ እንዲቆይ” አዝዟል። እነዚህን ትዕዛዞች የማስፈጸም ኃላፊነት ለባህል እና ስፖርት ሚኒስትር በፍርድ ቤት ተሰጥቷል።

በአንደኛ ተከሳሽ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቲ ስም የተከፈቱ የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች “በከሳሾች እና በተከሳሾች መካከል ባለው ክርክር ላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ ሳይንቀሳቀስ ታግዶ እንዲቆይ” ችሎቱ አዝዟል።

ባለፈው ወር በተካሄደው የ2024 ፓሪስ ኦሊምፒክ ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ውጤት አመርቂ አለመሆኑን ተከትሎ የኦሊምፒክ ኮሚቴው በተለይ ፕሬዝደንት አሸብር ወልደጊዮርጊስ ትችት ሲቀርብባቸው ነበር።

ፕሬዝደንቱ በቅርቡ በመንግሥት ቴሌቪዥን ቀርበው “ከኃላፊነታቸው የመልቀቅ” ሐሳብ እንደሌላቸው መናገራቸው ይታወሳል።

Read the whole story on bbc Amharic

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
News: Ethiopia rejects Egypt’s ‘unfounded allegations’ in letter to UN Security Council
የፌ.ምክር ቤት የህገ-መንግስት ትርጉምና የሕገ መንግስታዊነት ክትትል ጉዳዮች ዳይሬክተርን ጨምሮ 7 ግለሰቦች በሙስና ወንጀል ተከሰሱ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
TIPS 1

WFP Country Director Says Ethiopia Registered Significant Economic Transformation by Focusing on Rural Dev’t, Poverty Reduction

July 28, 2025
TIPS 1

Almost a third of people in Gaza not eating for days, UN food programme warns

July 26, 2025
TIPS 1

Israeli spy chief visits US amid bid to move Palestinians out of Gaza – Axios

July 20, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2