Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  በቀድሞው የፋይናንስ ደኅንነት ዋና ዳይሬክተር እነ ቴድሮስ በቀለ ላይ የቅጣት ውሳኔ ተሰጠ
law

በቀድሞው የፋይናንስ ደኅንነት ዋና ዳይሬክተር እነ ቴድሮስ በቀለ ላይ የቅጣት ውሳኔ ተሰጠ

Ethioreview newsEthioreview news—October 22, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የቅጣት ውሳኔውን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 5ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። ተከሳሾቹ ÷ 1ኛ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ቴድሮስ በቀለ፣ 2ኛ የቴድሮስ በቀለ ባለቤት ሩት አድማሱ፣ 3ኛ የወ/ሮ ሩት እህት የሆነችው ቤተልሔም አድማሱ እና በግል ስራ ይተዳደራሉ የተባሉት መርሀዊ ምከሰረ ወ/ፃዲቅ፣ ራሄል ብርሀኑ ፣ ፀሐይ ደሜ እና ጌታቸው ደምሴ ናቸው።

የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾች ላይ አጠቃላይ ሁለት ክሶችን በየተሳትፎ ደረጃ ጠቅሶ ክስ አቅርቦ ነበር።

በ1ኛው ክስ ላይም የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9(1) (ሀ) እና (3) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ አቶ ቴድሮስ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሲሰሩ የተቋሙን አሰራር ባልተከተለ መልኩ አስፈላጊው የደህንነት ይለፍ ያልተደረገለትን የትምህርት ዝግጅቱ ብቁ ያልሆነ በሌላ የሙስና ወንጀል መዝገብ የተከሰሰ አቤል ጌታቸው የተባለ ግለሰብን ከታኅሣስ 1 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በተቋሙ የተደራጁና የሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀሎች ፍተሻና ትንተና ከፍተኛ ኤክስፐርት ሆኖ እንዲሰራ ወደ ተቋሙ እንዲቀላቀል አድርገዋል በሚል ዐቃቤ ሕግ በክሱ ጠቅሶ ነበር።

በዚህም ከሰኔ 1 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ አቤል ጌታቸው የተባለውን ግለሰብ የፋይናንስ መረጃ ክትትል እና ቅበላ ቡድን መሪ አድርገው ባልተገባ መንገድ መመደባቸውን በክሱ ተዘርዝሯል።

More stories

ግማሽ ሚሊየን ብር በጥሬው ሲቀበል እጅ ከፍንጅ የተያዘው ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ

February 1, 2022

ዐቃቤ ህግ በቀድሞ የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የክስ መዝገብ ሌሎች ድርጅቶችን አካቶ ለመቅረብ ጠየቀ

July 7, 2023

በሰሜን ኢትዮጵያ ባለው ግጭት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመመርመር የተቋቋመው የሚኒስቴሮች ግብረ-ሀይል ስራውን በይፋ ጀምሯል

November 29, 2021

ሰው በማገት ወንጀል የተከሰሱ ሁለት ግለሰቦች 22 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት ተፈረደባቸው

February 16, 2022

የተቋሙን የቀደመ የመረጃ ምስጥራዊነት የጠበቀ እና ተጠያቂነትን ያማከለ የመረጃ ቅበላ እና ትንተና አሰራርን በመለወጥ በተቋሙ ውስጥ ስልጣንን ተገን በማድረግ የባለሀብቶችንና የድርጅቶችን የባንክ ሂሳብ አስቀድሞ በማጥናትና መረጃ በመውሰድ በተለያዩ ጊዜያት ለባለሀብቶች ስልክ በመደወል በአካል በማግኘት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንዲከፍሉ በመጠየቅ የማይከፍሉ ከሆነ ደግሞ የፋይናንስ እንቅስቃሴያቸውን በተመለከተ ምርመራ አድርጎ ለፖሊስ በማስተላለፍ የወንጀል ምርመራ እንዲጀመርባቸው ይደረግ ነበር በማለት ዐቃቤ ሕግ በክሱ ጠቅሷል።

አጠቃላይ ተከሳሹ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ውስጥ የነበረውን ኃላፊነት በመጠቀም የፋይናንስ ትንተና በመስራት ውጤቱን ለፍትሕ አካላት የማስተላለፍ ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም ገንዘብ ያላቸው ባለሀብቶችን አሰቀድሞ በማጥናት በመምረጥ በ2013 ዓ.ም እና በ2014 ዓ.ም በተለያዩ ጊዜያት ባለሀብቶችን የባንክ ሒሳባቸው እንደሚታገድ እና በፖሊስ እንደሚመረመሩ እንደሚደረጉ በመግለጽ በማስፈራራት ከ3 ግለሰቦች 3 ሚሊየን 470 ሺህ ብር ገንዘብ ፋፋ ዳባ በተባለ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገቢ እንዲደረግ በማድረግ በዋና ወንጀል አድራጊነት ስልጣንን አላግባብ መገልገል ከባድ ሙስና ወንጀል ተከሷል።

በ2ኛው ክስ ደግሞ በሁሉም ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን÷ በዚህም በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32/1/ሀ እና በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ወይም ንብረትን ሕጋዊ አድርጎ ማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29 (1) (ሀ) (ለ) እና (ሐ) ላይ የተደነገገውን በመተላለፍ ተከሳሾቹ ከላይ በተጠቀሰው መልኩ በወንጀል የተገኘ 3 ሚሊየን 470 ሺህ ብር የወንጀል ፍሬ መሆኑን እያወቁ የገንዘቡን ምንጭ ለመደበቅ በማሰብ ግብረአበር ነው የተባለ ፋፋ ዳባ እየተባለ የሚጠራ ግለሰብ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተ ሒሳብ ገቢ እንዲደረግ በማድረግና ከዚሁ ከተጠቀሰው ገንዘብ በተለያዩ መጠን በመጠቀም ሕገ-ወጥ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል ተከሰዋል።

ከ1ኛ እስከ 6 ኛ የተጠቀሱት ተከሳሾች ከጠበቆቻቸው ጋር ቀርበው ክሱ እንዲደርሳቸው ከተደረገ እና በችሎት ክሱ በንባብ ከተሰማ በኋላ ወንጀሉን አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ከአምስት በላይ ምስክሮችን አቅርቦ አሰምቶ የነበረ ሲሆን÷ ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ሕግ ምስክር ቃልን መርምሮ ብይን ሰጥቷል።

በዚህም በ1ኛው ክስ የቀረበባቸው አቶ ቴድሮስ ላይ የተሰሙ ምስክሮች ቃል ተመርምሮ ወንጀሉ መፈጸሙን በምስክር ተረጋግጧል በማለት ፍርድ ቤቱ በ1ኛው ክስ ብቻ እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

ይከላከሉ የተባሉት በሙስና አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9 ንዑስ ቁጥር 1 እና በንዑስ ቁጥር 2 ስር ነው።

በ2ኛው ክስ ደግሞ ማለትም በቀረበው በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘ ገንዘብን ሕጋዊ አድርጎ ማቅረብና መገልገል ወንጀል የተከሰሱት ከ2ኛ እስከ 6ኛ የተጠቀሱት ተከሳሾች የወንጀል ድርጊቱን ስለመፈጸማቸው በዐቃቤ ሕግ ምስክር የተረጋገጠ መሆኑ ተጠቅሶ እንዲከላከሉ ብይን ተሰጥቷል።

በዚሁ ክስ 7ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሰው ተከሳሽን በሚመለከት በሌለበት ጥፋተኛ የተባለ ሲሆን÷ አቶ ቴድሮስ በቀለ በዚህ ሁለተኛ ክስ የወንጀል ተግባር ስለመፈጸማቸው በሰው ማስረጃ አለመረጋገጡ ተገልጾ ነጻ ተብለዋል።

ተከሳሾቹ በተለያዩ ቀናት የመከላከያ ማስረጃ ያቀረቡ ቢሆንም ባቀረቡት የመከላከያ ማስረጃ ግን የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው መከላከል አለመቻላቸው ተገልጾ የጥፋተኝነት ፍርድ ተሰጥቶባቸዋል።

ከዚህም በኋላ ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየቶችን መርምሮ ዛሬ በዋለው ችሎት የቅጣት ውሳኔ ወስኗል።

በዚህም ዐቃቤ ሕግ የወንጀል ድርጊቱ በትብብርና በስምምነት የተፈጸመ መሆኑን ጠቅሶ ያቀረበው የቅጣት አስተያየት በትብብር ስለመፈጸሙ በማስረጃ አስደግፎ አለማቅረቡን የችሎቱ ሰብሳቢ ዳኛ ገልጸው የቅጣት ማክበጃውን አለመቀበላቸውን አብራርተዋል።

በዚህም ፍርድ ቤቱ 1ኛ ተከራሽ አቶ ቴድሮስ ያቀረቡት አጠቃላይ 7 የቅጣት ማቅለያ አስተያየት ተይዞላቸው በዕርከን 17 መሰረት በ3 ዓመት ከ3 ወር ጽኑ እስራትና በዕርከን 3 መሰረት ደግሞ በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኗል።

3ኛ እና 4ኛ ተከሳሾች ያቀረቡት የቅጣት ማቅለያ ተይዞላቸው እያንዳንዳቸው በዕርከን 22 መሰረት በ5 ዓመት ከ6 ወራት ጽኑ እስራት እና በዕርከን 9 መሰረት በ5 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኗል።

በሌለበት ጉዳዩ የታየው 7ኛ ተከሳሽን በሚመለከት የቀደመ የወንጀል ሪከርድ እንዳለበት ማረጋገጫ አለመቅረቡ ተጠቁሞ አንድ ማቅለያ ተይዞለት በዕርከን 26 መሰረት በ7 ዓመት ከ8 ወራት ጽኑ እስራትና በዕርከን 18 መሰረት በ25 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተጥሏል።

ሌሎች 2ኛ፣ 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች ደግሞ ከ7 እስከ 5 የሚደርስ የቅጣት ማቅለያ ተይዞላቸው በዕርከን 22 መሰረት ከ4 ዓመት እስከ 5 ዓመት የሚደርስ የቅጣት ውሳኔ የተጣለባቸው ቢሆንም ተከሳሾቹ ቅጣቱ እንዲገደብላቸው ያቀረቡት አስተያየት ተይዞላቸው ቅጣቱ ተገድቦላቸዋል።

በተጨማሪም የተገደበላቸው ተከሳሾች የ500 የፍርድ ቤት ወጪን እንዲሸፍኑና 2 ሺህ ብር ደግሞ የመተማመኛ ዋስትና እንዲያሲዙ፤ 7ኛ ተከሳሽን ፌደራል ፖሊስ አፈላልጎ ለማረሚያ ቤት እንዲያስረክብ ታዝዟል።

በታሪክ አዱኛ – ፋና

law
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
አብይ አሕመድና ዝናሽ ታያቸው ካዛን ገቡ፤ የብሪክስ አባላት ውሳኔዎች በጉጉት ይጠበቃሉ
ምርጫ ቦርድ አስራ አንድ ፓርቲዎችን በጊዜያዊነት አገደ፤ ኦነግ አለበት፤ ኢትዮጵያ የአፍሪቃ ዋንጫ ልታዘጋጅ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
law

ህገወጥ የውጭ ምንዛሪ ወንጀል የፈጸሙ 123 ተጠርጣሪዎች የባንክ ሒሳብ ታገደ

September 20, 2025
law

እነ ቀሲስ በላይ በሙስና ወንጀል ሊፈርድባቸው እንደማይገባ ጠቅሰው ያቀረቡት ይግባኝ ውድቅ ሆነ

July 26, 2025
law

የአዲስ አበባ የከንቲባ ፅ.ቤት ፕሮቶኮልን ጨምሮ 12 ተከሳሾች በሌብነት ተከሰው ተፈረደባቸው

July 23, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2