Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  General  የወለጋ ክፍለ ሃገር ፋኖ- “ሕዝብ ላይ ጦርነት ማወጅ ነው፤ አንቀበለውም” ኦፌኮ
GeneralNews

የወለጋ ክፍለ ሃገር ፋኖ- “ሕዝብ ላይ ጦርነት ማወጅ ነው፤ አንቀበለውም” ኦፌኮ

Ethioreview newsEthioreview news—December 19, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በአንድ አካባቢ ሁለትም፣ ሶስትም አደረጃጀት ቢኖርም የጎንደር ፋኖ፣ የጎጃም ፋኖ፣ የሽዋ ፋኖ፣ የደሴ፣ የኮምቦልቻ ወዘተ እንደሚባለው ሁሉ ” የወለጋ ክፍለ ሃገር ፋኖ” የሚለው አደረጃጀት ይፋ መሆኑን ተከትሎ ” ክፍለ ሃገር” የምትለዋ ተቀጥያ በተለይ ኦሮሚያ ላይ “ለምን ተፈለገች?” የሚል ጥያቄ በኦሮሞ ፖለቲከኞች ዘንዳ መነጋገሪያ ሆናለች። በተመሳሳይ አማራዎች በርከት በለው በሚኖሩባቸው አካባቢዎች ክልል ሳይለይ ተመሳሳይ አደረጃጀት እየተፈጠረ መሆኑም እየተሰማ ነው። ይህ እንቅስቃሴ በሁሉም አገሪቱ ውስጥ በሰላም የሚኖሩ የአማራ ተወላጆችን ይጠቅማል? የሚለው ጉዳይ አድሮ የሚታይ ቢሆንም የሌሎች ክልሎች ምላሽ ባይታወቅም በኦሮሚያ ግን ከቶውንም እንደማይፈቀድ በይፋ እየተገለጸ ይገኛል።

አንድን ወገን እወክላለሁ የሚል የታጠቀ ኃይል፣ በአንድ በሚታወቅ፣ በህገ መንግስት ራሱን እንዲያስተዳድር ስልጣን በተሰጠው፣ የራሱ ወሰን፣ የአስተዳደር እርከንና ህግ ባለው ክልል ውስጥ ትጥቅ አንስቶ መንቀሳቀሱን በምንም መልኩ እንደማይቀበለው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ በተለይ ለኢትዮሪቪው የገለጸው በዚሁ እሳቤ ነው። አካሄዱ የጎንዮሽ ግጭት ሊያስነሳ እንደሚችልም ስጋቱን ከማስጠንቀቂያ ጋር አስተላልፏል።

የኦፌኮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሱልጣን ቃሲም፣ ይህን ያሉት ራሱን ” የወለጋ ክፍለሃገር ፋኖ” በሚል ስያሜ በማስተዋወቅ በኦሮሚያ የትጥቅ ትግል ማድረጉን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ፓርቲያቸው ጉዳዩን በምን መልኩ እንደሚያየው ለተተየቁት ሲመልሱ ነው።

የወለጋ ክፍለሃገር ፋኖ መሪ ፋኖ ንጉሴ ሰሞኑን በይፋ እንዳስታወቁት እቅስቃሴው ከዚህ በፊትም የነበረ መሆኑንን አመልክተው አሁን ላይ በዕዝ ደረጃ መደራጀቱን አስታውቀዋል። ቀደም ሲል ራስን ለመከላከል በሚል የተጀመረው አደረጃጀት አሁን ላይ ወደ ዕዝ ደረጃ ማደጉን ያስታውቁት ፋኖ ንጉሴ ” በአማራ ክልል ካለው የፋኖ እንቅስቃሴ ጋር ግንኙነት አለን” ብለዋል።

የፋኖ ታጠቂዎች በምስራቅ ወለጋ አንገር ጉቲን አራት ወጣቶችን አግተው ሁለቱን ገደሉ፤ ግድያው የጠየቁት ገንዘብ ከተከፈለ በሁዋላ ነው
More stories

አብይ አሕመድ አዳነችን ቀነ ገደብ አስቀምጠው ሪፖርት አንዲያቀርቡ አዘዙ፤ ቢያንስ ፩ ቢሊዮን ብር ተሰርቋል

February 24, 2023

ከአዲስ አበባ የመሬት ዘረፋ ጋር በተያያዘ ” አንቱ” የተባሉ ሊጠየቁ ነው፤ አቃቤ ህግ ክስ እያደራጀ መሆኑ ተሰማ፤ ውክልና መሬት ተዘርፏል

February 9, 2021

ሱዳን፣ የህወሃት የሽብር ቡድንን በመደገፍ ለሽብር እያደራጀች ቢሆንም በክልሉ በሁሉም የድንበር አካባቢዎች ጥብቅ ክትትል እየተደረገ ነው

August 3, 2021

ፖለቲካ – የትህነግ ወኪሎች ስካይ ላይን ናቸው ፤ ጌታቸው ረዳ ወደ ኮሙኒከሽን ?

November 3, 2022

በኦሮሚያ በጃል ሰኚ የሚመራው ታጣቂ ኃይል ወደ ሰላም አማራጭ መመለሱን ተከትሎ፣ ይፋ የሆነው የወለጋ ክፍለሃገር ፋኖ አደረጃጀት በዚህ ስም ራሱን ባይጠራም ከኦነግ ሸኔ ጋር ተናቦና ህብረት ፈጥሮ ይሰራ እንደነበር በርካታ መረጃዎች ሲወጡ እንደነበር ይታወሳል።

እንዲህ መሰል መረጃዎች በሚወጡበት ወቅት ኢስመኮ ያወጣውን ሪፖርት አስመልክቶ ጃዋር መሐመድ ለቢቢሲ ”  ተኩስ በማቆም ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ጋር ንግግር መጀመር አለበት፤ በተጨማሪም የፋኖ ሚሊሻዎችን ከኦሮሚያ አስወጥቶ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው መመለስ አለባቸው ፣ አጠቃላይ ብሔራዊ የሰላም ሂደት ብቸኛው መፍትሄ በመሆኑ ይህን ለማሳካት አቅዶ መተግበር ያስፈልጋል” ማለቱ አይዘነጋም።

“ኦሮሚያ ውስጥ የሚሆነው ሁሉ በመናበብ የሚሰራ ላለመሆኑ ምን ማስረጃ ማቅረብ ይችላል”

ፋኖ ንጉሴ ከፋሲል የኔ ዓለም ጋር ባደረጉት ውይይት “መንግስት ሸኔ ስለሚል በተለምዶ ኦነግ ሸኔ እንላቸዋለን እንጂ ስማቸው ABO ወይም የኦሮሞ ነጻ አውጪ ጦር ነው” በማለት የስም ማስተካከያ ካደረጉ በሁውላ፣ ላለፉት አራት ዓመታት አማራን መንካት እንዳቆሙ አስታውቀዋል። ፋኖ በወለጋ ከተመሰረት መቆየቱንም ይፋ አድርገዋል።

አቶ ሱልጣን አሁን ላይ ይፋ ይነገር እንጂ ጉዳይ አዲስ እንዳልሆነ፣ ድርጅታቸው በተለያዩ ጊዜያት መግለጫ በማውጣት ማስጠንቀቂያ የሰጠበት ጉዳይ መሆኑን ያስታውሳሉ። አክለውም፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ‘በኦሮሚያና በቢኒሻንጉል ውስጥ ያሉ አማራዎች መታጠቅ አለባቸው’ ብለው በይፋ ሲናገሩና እንዲተገበር ሲያደርጉት ኦፌኮ ጉዳዩ አድሮ ችግር እንደሚያስነሳ ገልጾ መቃወሙን ይገልጻሉ።

“ታላቁ እስክንድር” በሚል ማዕረግ የሚጠራውና በአንድ ወገን ያለውን የፋኖ አደረጃጀት የሚመራው እስከንድር ነጋ፣ በውጭ አገር የአማራ ትግል አስተባባሪ ያላቸው ሻለቃ ዳዊት ወለደ ጊዮርጊስ፣ “ወለጋ የአማራ ዕርስት ነው” በሚል ትግሉ በገሃድ ወለጋንም የማስመለስ ትግል እንደሆነ መናገራቸው አይዘነጋም። ፋኖ ንጉሴ ይህን ጉዳይ ከፋሲል ጋር ሲወያዩ አልገለጹም፣ ፋሲልም አላነሳባቸውም።

ፋኖ ንጉሴ ትግሉ አማራውንም ሆነ ኦሮሞውን ነጻ የማውጣት እንደሆነ ጠቅሰው፣ በውስጣቸው ኦሮሞ የሆኑ አመራሮች መኖራቸውን አስታውቀዋል። በፋኖ ስም ኦሮሞን ላይ ያልተገባ ተግባር የሚፈጽሙ መኖራቸውንም አስታውቀዋል። ይህ አግባብ ባለመሆኑ እንደሚያወግዙ ገልጸዋል።

አቶ ሱልጣን የፋኖ አደረጃጀት የሚባል ትጥቅ ላይ የተመሰረተ እንቅስቃሴ ” አንድ በራሱ በህግ በተወሰነለት ድንበር ውስጥ በሚኖር ህዝብ ላይ ጦርነት ማወጅ ነው፤ በፍጹም ተቀባይነት የለውም”

የኦሮሞ ሕዝብ ትልቅ ቁጥር ያለው አንድ የኢትዮጵያ አካል መሆኑን አስታውሰው፣ ” አንድ የታጠቅ ኃይል በዚህ ህዝብ መካከል መንቀሳቀሱ ጣልቃ ገብነት ነው። የጎንዮሽ ግጭትም ሊያስከትል የሚችል አደገኛ አካሄድ ነው” ሲሉ ተቀባይነት የሌለውና በአስቸኳይ ሊታረም የሚገባው ጉዳይም መሆኑን አቶ ሱልጣን ያስረዳሉ።

“ዜናው ይፋ መሆኑን ተከትሎ በኦሮሚያ አማራዎች በሚኖሩበት ቦታ ሁሉ ህዝብ በጥርጣሬ እንዲመለከት እያደረገ ነው። መሰል አደረጃጀቶች ከወከጋም አልፎ በተለያዩ አካባቢዎች እንዳሉም መረጃዎች አሉ” ሲሉ የኦፌኮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አስታውቀዋል።

አካሄዱ ተዋልዶና ተከባብሮ በፍቅር የሚኖረውን ህዝብ ለማጋጨት ካልሆነ በቀር ሌላ አንዳችም ውጤት እንደማያመታ ትኩረት ሰጥተው የተናገሩት አቶ ሱልጣን፣” በኦሮሚያ ውስጥም ሆነ በአጎራባች ክልሎች በሰላም መኖር የሚቻለው ህዝብን ከህዝብ በሚያጋጭ አደረጃጀት ሳይሆን፣ በመከባበርና በመስማማት ብቻ ነው” ሲሉ ውጤቱን በማየት ዕርምት እንዲደረግ መክረዋል።

“ሕዝብን ከሕዝብ ማጋጨት የጽንፈኞች ተግባር ነው” በማለት የኮነኑት አቶ ሱልጣን፣ “የግዛት ይገባናል ጥያቄ ካለ በህግና በህገ መንግስቱ አግባብ መጠየቅ ይበጃል። ሌሎችም ተመሳሳይ ጥያቄ ሊኖራቸው ይችላል” ብለዋል።

ህጋዊ ያልሆኑ ታጣቂዎች ለሰላማዊ ዜጎች ፈተና መሆናቸው በርካታ አብነት የሚቀርብበት ጉዳይ በመሆኑ ድርጅታቸው ቀደም ሲልም፣ ዛሬም ሆነ ነገ የትጥቅ ትግልን እንደማይደግፍም እግረ መንገዳቸውን አስታውሰዋል።

አቶ ሱልጣን ደጋግመው ያነሱት ” ወለጋ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተመሳሳይ እንቅስቃሴ እንዳለ ይሰማል” የሚለውን ጉዳይ ነው። እንቅስቃሴው ከፖለቲካው በላይ የድህንነት ስጋት መሆኑን እንደሆነ ይገልጻሉ። በኦሮሚያ በስፋት ተቀላቅለውና ተዋልደው ለሚኖሩ የአማራ ተወላጆችም እረፍት የሚነሳ አደገኛ አካሄድ መሆኑን በመጠቀስ ለሰማዊ ዜጎች ሲባል አሁን ደግመው እንዲያስቡ ጥሪ ያቀርባሉ።

በኦሮሚያ ማንም ከማንም ሳይለይ በእኩልነት ለረዥም ዓመታት መኖራቸውን፣ አሁንም እየኖሩ እንደሆነ ያመልከቱት አቶ ሱልጣን፣ መንግስት የፖለቲኪአ ምህዳሩን ማጥበቡ አንዱና ትልቁ የአገሪቱ ችግር ቢሆንም ህዝብን ሰላም የሚነሳ፣ የሚያጋጭና የሚያጫርስ የትግል ስልት አግባብ እንዳልሆነ ገልጸዋል።

የፋኖ ኃይል ጫካ ካለው የኦነግ ሰራዊት ጋር አብረው እየሰሩ እንደሆነ መስማታቸውን ተጠይቀው ” እሱ የሁለቱ ጉዳይ ነው። እናን አይመለከትም” ብለዋል። ይህ ስለመሆኑ የኦነግ ሰዎች ማረጋገጫ ባልሰጡበት አግባብ ዘርዝር ጉዳይ መናገር እንደማይቻልም ገልጸዋል። በሳቸው ዕምነት አሁን የተጀመረው አካሄድ ግን ምንም ይሁን ምን ግጭት ከማስፋት የዘለለ ውጤት ሰላማያመጣ ወደ ውይይት ማምራቱ ሁሉንም ተጠቃሚ ያደርጋል ባይ ናቸው። መንግስት የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት ለንግግር በሩን መክፈትም እንዳለበት አሳስበዋል።

በቴሌግራም ይከተሉን https://t.me/+f_kxmaPjD-9jYTdk

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ምርመራ የተከፈተባቸው ፕሬዚዳንት ለአቃቤ ሕግ ትዕዛዝ ተገዥ እንዳልሆኑ ተገለጸ
ያለ ደረሰኝ ሲነግዱ በተገኙ 1 ሺህ 145 ነጋዴዎች ላይ ርምጃ ተወስዷል
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2