Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  መንግስት ምንጩ የማይታወቅን ሃብት በህግ ለመዳኘት መነሳቱ ዳግም ጫጫታ አስነሳ፤ “ሌብነትን መዋጋት ለምን ያስኮንናል”
lawNews

መንግስት ምንጩ የማይታወቅን ሃብት በህግ ለመዳኘት መነሳቱ ዳግም ጫጫታ አስነሳ፤ “ሌብነትን መዋጋት ለምን ያስኮንናል”

Ethioreview newsEthioreview news—February 1, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር የሚተኮሱ ሃብታሞችን ማየት የተለመደ ነው። ይህ ምንጩ ግልጽ ያልሆነ ሃብት ቁጥጥር ሊደረግበት እንደሚገባ ሕዝብ በተደጋጋሚ ሲጠይቅ፣ በድብቅ ሲያማ እንደነበር ይታወሳል። በተለይም ተቃዋሚዎች ሌብነትን የሚሸከም መንግስት እንደሆነ በመግለጽ ድምጻቸውን ሲያሰሙ ኖረዋል።

ምንጩ የማይታወቅ ንብረትን አስመልክቶ አዲስ ሲወጣ በዋናነት የተቀመጠው ቀደም ሲል የነበሩ ህጎች ለአፈጻጸም ችግር በመሆናቸውና ወንጁእለኞች በህገወጥ ያፈሩትን ንብረት ቢፈርድባቸው እንኳን ሊያጡ የሚችሉበት አግባብ አለመኖሩ ነበር።

አስር ዓመት ወደሁዋላ ተመልሶ እንዲሰራ ፓርላማ ፈቃድ የሰጥው ግፍ ህጋዊ ባለንብረቶችን፣ በህጋዊ አግባብ ንብረት ያፈሩና ገቢያቸው፣ የሚከፍሉት ግብርና ወዘተ የሚጣታመውን የማይነካ መሆኑ በግልጽ ቢነገርም፣ ህጉ ወደ ተጋር ሲመነዘር ልክ ቀደም ሲል ህጉ ሲወጣ እንደሆነው ጫጫታ ማስነሳቱ በርካቶችን አስገርሟል።

በደቦ ህጉን “መንግስት ሊዘርፍ ነው” የሚል ታቤላ በመለጠፍ የሚቃወሙትን ወገኖች ለመገሰጽም ሆነ ለመከራከር አስቸጋሪ መሆኑን የሚናገሩ የህግ አዋቂዎች፣ አፈጻጸሙ ላይ ጥንቃቄ ማድረጉ ላይ ሊተኮርበት እንደሚገባ ከማሳሰብ የዘለለ አሁን ላይ ብዙም አስተያየት መስጠት አግባብ እንዳልሆነ ይናገራሉ። የሚቃወሙትም አካላትና ሚዲያዎች አንድና ሁለት መስመር ጽፈው በቁንጽል ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ማዕበል ለማስነሳት ከሚሞክሩ በአመክንዮ የተቃውሟቸውን ጭብጥ ሊያስረዱ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

More stories

የኢትዮጵያ ነርሶች ማህበር ታካሚዎች ለሞትና እንግልት እንዳይዳረጉ አስጠነቀቀ

May 19, 2025

የቡና ግብይትና ጥራት ቁጥጥር ሕግ (ክፍል አንድ)

August 29, 2023

የአማራ ክልል በቀጣይ አምስት አመት ከ26 ሺህ በላይ የእርሻ ትራክተር እና 300 ኮምባይነር ያስገባል

July 23, 2022

የጦር ሃይሎች ዋና አዛዥ ” ወረን አናውቅም፣ ማንንም አንወርም” ሲሉ ኢትዮጵያ ከባህር በር ፍላጎት አንጻር የያዘችው አቋም ስጋት ለገባቸው ማረጋገጫ ሰጡ

October 26, 2023

የኢ.ፌ.ድ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር የንብረት ማስመለስ አዋጅ ቁጥር 1364/2017ን አስመልክቶ የተሰጠውን ጋዜኛዊ መግለጫ የሚኒስቴሩ ማህበራዊ ገጽ ላይ በዚህ መልኩ ታትሟል። ከስር ያንብቡ።

የፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሐና አርአያስላሴ በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ጥር 1ቀን 2017 ዓ.ም የፀደቀዉን የንብረት ማስመለስ አዋጅ ቁጥር 1364/2017ን አስመልክቶ ለመንግስት እና የግል የመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎችና ጋዜጠኞች በዛሬዉ እለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

የንብረት ማስመለስ አዋጅ ቁጥር 1364/2017 በጥር 1 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁን ተከትሎ የአዋጁን ዓላማ፣ መሠረታዊ ይዘቶች፣ እንዲሁም ቀጣይ አተገባበር በተመለከተ የተፈጠሩ ብዥታዎችን ለማጥራት መግለጫ መስጠት ማሰፈለጉን የገለፁት ክብርት ሚኒስትሯ፣ ይህ አዋጅ ከመውጣቱ በፊት በወንጀል የተገኘ ሃብት ማስመለስን በተመለከተ ራሱን የቻለና ወጥ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ ያልነበረ በመሆኑ በሕግ ማስከበር ሂደት በጣም ክፍተት ፈጥሯል።

የወንጀል ሕጉን ጨምሮ በተለያዩ አዋጆች የሃብት ማስመለስ ሥነ-ሥርዓትን በሚመለከት የተካተቱ ድንጋጌዎች በራሳቸው የተሟሉ ካለመሆናቸው ባለፈ አንዱን ከሌላው ጋር እያስማሙ ለመተግበር አስቸጋሪ የሚያደርጓቸው ድንጋጌዎችን የያዙ እና ተፈጻሚነታቸውም ውስን የሆኑ ወንጀሎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ የተቀረጹ በመሆኑ በርካታ በማህበረሰቡ ላይ ጉዳትን በሚያደርሱ ወንጀሎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ አልተቻልም። በዚህም ወንጀል ፈፃሚዎች ከወንጀል ድርጊት ያገኙትን ንብረቶች በማስመለስ ረገድ ከፍተኛ የሆነ የሕግ እና አሰራር ክፈተቶች እንዲፈጠር ምክንያት መሆኑን ገልፀዋል።

ክብርት ሚኒስትሯ አክለውም ምንጩ ያልታወቀ ንብረትን በተመለከተ እስካሁን ባሉን ሕጎች ተጠያቂ የሚሆኑት የመንግሥትና ሕዝባዊ ድርጅት ሠራተኞች ሲሆኑ ሌሎች ሰዎችን የማይመለከት በመሆኑ ሰፊ በሚባል ደረጃ ምንጩ ያልታወቀ ንብረት የማፍራት ሁኔታ ተስተውሏል።

የዚህ ሕግ አለመኖር ሌሎች የመንግስትና ሕዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች በቀላሉ በሕገ-ወጥ መልኩ ያፈሩትን ንብረት በእነዚህ ሰዎች ስም ለማፍራት እና ለመደበቅ እንዲችሉ ትልቅ አስተዋጽዖ አድርጓል ብለዋል።

በሌላ በኩል አዋጁ የዜጎችን የንብረት መብት ተገቢ ጥበቃ ለማረጋገጥ ብዙ ድንጋጌዎችን ያካተተ ነው ያሉት ክብርት ሚኒስትሯ፣ በቅን ልቦና ንብረትን የያዙ ሰዎች በቅን ልቦና የያዙት ንብረት እንዳይወረስ ተገቢውን ጥበቃ ሰጥቷል።

ምንጩ ያልታወቀ ንብረትን በሚመለከት ለማስረዳት የሚቀርበው የማስረጃ አይነት እንደየ አግባቡ የተለያየ ሊሆን ይችላል። የንብረቱን አመጣጥ የማስረዳት ሸክም ያለበት ሰው በማንኛውም ያስረዱልኛል በሚላቸው የማስረጃ አይነቶች ሊያስረዳ የሚችል ሲሆን የማስረጃው አጥጋቢነት ደግሞ በፍርድ ቤት የሚመዘን ይሆናል።

በመሆኑም የንብረት ማስመለስ ሕግ መውጣት ዜጎች በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ የሚኖራቸውን የእኩል ተጠቃሚነትን የሚያጎለብት እና የግለሰቦችን በሕጋዊ መንገድ ብቻ ንብረት የማፍራት ባህልን በማሳደግ ጠንካራ የሆነ የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን ከፍተኛ አስተዋዕፆ እንደሚኖረው አመላክተዋል።

የዚህ ሕግ አተገባበር በሰዎች የንብረት መብት ላይ ያልተገባ ተጽዕኖን እንዳይፈጥር እና የሕግ አስፈጻሚ አካላት ባልተገባ አሰራር የዜጎችን መብት እንዳይጥሱ በሚያስችል መልኩ እንዲተገበር አዋጁ የአደረጃጀት እና የአሰራር መፍትሔዎችን አካቷል ያሉት ክብርት ሚኒስተሯ፣ አዋጁ የሚተገበረው በፍትሕ ሚኒስቴር በተማከለ አደረጃጀት ለዚህ ሥራ ዓላማ በሚደራጅ የሥራ ክፍል በመሆኑ ግልጽ የአሠራር ሂደትና የተጠያቂነት ሥርዓት እንደሚዘረጋ ተገልፆል።

ምንጩ ያልታወቀ ንብረትን በተመለከተ በቅድመ ክስ ሂደት ማንኛውም ሰው ጉዳዩን እንዲያስረዳ የሚቀርቡ ጥያቄዎች እና አቤቱታዎች የፍርድ ቤቶች የሥነ ሥርዓት ሕጎችንና መርሆዎችን ተከትለው ጥብቅ የሆነ ማጣራት የሚደረግባቸው ሲሆን አቤቱታ የሚቀርብባቸውም ሰዎች በሕጉ መሰረት ያላቸውን ማስረጃዎች የማቅረብ እና በፍርድ ቤት ዘንድ ቀርበው የመደመጥ መብታቸው እንዲከበርላቸው ይደረጋል።

ለሥራ ክፍሉ የሚቀርቡ ምንጩ ያልታወቀ ሀብትን የሚመለከቱ ጥቆማዎችም ሆነ ጥርጣሬዎች ጥብቅ በሆነ አሰራር የሚጣሩ እና በቂ ምክንያት መኖሩ የሚታመንባቸው ጉዳዮች ብቻ ወደ ፍርድ ቤት የሚሄዱበት የአሰራር ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናልም ተብሏል።

በአጠቃላይ የንብረት ማስመለስ ሕግ በኢትዮጵያ ሰዎች ከወንጀል ድርጊት የሚያፈሩትን ሀብት እና ምንጩ ሳይታወቅ የሚያገኙትን ንብረት በመቆጣጠር እና ሲገኝም ለማሕበረሰቡ ተመላሽ እንዲሆን በማድረግ ወንጀል አትራፊ ሥራ እንዳይሆን ማድረግን እና በአጠቃላይ ደግሞ ማህበራዊ ፍትሕን ማስፈንን አላማው አድርጎ የጸደቀ እና ይህንን ዓላማ በሚያሳካ አግባብ ጥብቅ የሆነ የአፈጻጸም ሥርዓትን የሚከተል የሕግ ማዕቀፍ ነው ሲሉ ክብርት ሚኒስተሯ አብራርተዋል።

lawNEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ሻዕቢያ ጦነቱን ትግራይ ምድር ላይ ለማድረግ የነደፈው ዕቅድ ከሸፈ፤ ” ጦርነትን አንፈልግም፣ ጦርነት በቃን”
 አብይ አሕመድ “አዲሱ ትውልድ የሚፈልገው ልማትና ብልጽግና ነው” አሳብ ማፍለቅ፣ መሰልጠንና መነጋገር የወቅቱ ጥሪ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2