በስምንት ወር ብቻ ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ ከ4.5 ቢሊኦን ብር በላይ አገኘች። ኢትዮጵያም አሜሪካ የጣለችውን የአስር በመቶ ታሪፍ እንደምትቀበለው ይፋ አድርጋለች።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዓለም አቀፍ ንግድ ላይ አዲስ የታሪፍ እርምጃ ወስደዋል። ረቡዕ ዕለት በዋይት ሀውስ በሰጡት መግለጫ፣ አሜሪካ ከሌሎች ሀገራት ጋር በምታደርገው የንግድ ልውውጥ ላይ አዲስ የታሪፍ መጠኖችን መጣላቸውን አስታውቀዋል።
ትራምፕ እንደገለጹት፣ ይህ እርምጃ አሜሪካን ቀዳሚ ለማድረግ እና የንግድ ጉድለትን ለመቀነስ ያለመ ነው። በአብዛኛዎቹ ሀገራት ላይ የተጣለው ታሪፍ ከ10% እስከ 49% የሚደርስ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ 10% ታሪፍ እንደተጣለባት ታውቋል።
አሜሪካ የንግድ ጉድለቷን ለመቀነስ እና የአሜሪካን ኢኮኖሚ ለመጠበቅ ይህን እርምጃ እንደወሰደች የገለፁት ፕሬዝዳንቱ ከ20 በላይ ሀገራት ላይ የታሪፍ ጭማሪ የተደረገ ሲሆን፣ ኢትዮጵያም ከነዚህ ሀገራት አንዷ መሆኗ ተዘግቧል ።
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ የቀረበላትን አዲሱን የታሪፍ አወቃቀር እንደምትቀበል አስታወቀች
ኢትዮጵያ አዲሱን የበጀት ታሪፍ እንደምትቀበል ይፋ አድርጋለች። የታሪፉ አወቃቀር የኢትዮጵያ ምርቶች ወደ አሜሪካ ገበያ ሲገቡ የሚጣልባቸውን ታሪፍ 10% ብቻ በማድረግ ተወዳዳሪነታቸውን ያሳድጋል ብሏል።
መንግስት ይህ ውሳኔ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ግንኙነት ለማጠናከር እና የኢትዮጵያን ኤክስፖርት ለማሳደግ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ገልጿል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ዉሳኔዉን ተከትሎ እንዳስታወቀዉ ይህ አዲሱ የታሪፍ አወቃቀር ኢትዮጵያ እንደ ቬትናምና ባንግላዴሽ ካሉ ትልልቅ የማምረቻ ማዕከላት ጋር ስትወዳደር የተሻለ እድል እንዲኖራት ያደርጋል።
“የ10% የታሪፍ መጠን ለኢትዮጵያ ላኪዎች ከፍተኛ ማበረታቻ ይሰጣል” ሲል ሚኒስትሩ አስታውቋል ። “ይህ የኢትዮጵያ ምርቶች በአሜሪካ ገበያ ተወዳዳሪ ዋጋ እንዲኖራቸው በማድረግ የፍላጎት እና የኢንቨስትመንት መጨመርን ያመጣል ሲል ተስፋዉን ጥሏል ሲል ካፒታል አስነብቧል ።
በተመሳሳይ የገቢ ዜና የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ እንደገለጹት፣ በ2010 ዓም የኢትዮጵያ የውጪ ንግድ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር የነበረ ቢሆንም በስምንት ወራት የውጪ ንግድ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ደርሷል። በ2017 በጀት ዓመት መጨረሻ ከ6 ቢሊየን ዶላር በላይ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
መንግስት የንግዱ ዘርፍ ተወዳዳሪና ተገማች ለማድረግ በመስራት ላይ መሆኑን መሆኑን ጠቅሰው ንግዱ ቀጠናውን የሚያስተሳስር የንግድ ልውውጥ ለማድረግ መሆኑንም ገልጸዋል።
በሀገሪቱ የንግድ ፖሊሲ እንዳልነበረ በመግለጽ ከብዙ ጥረትና ድካም በኋላ ረቂቅ የንግድ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያና የአሜሪካ ንግድ ልውውጥ ምን ይመስላል
በፈረንጆቹ 2024 አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር 1.5 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ዕቃ ተገበያይታለች። በ2024 እ.ኤ.አ አሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ 1.0 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ዕቃ የላከች ሲሆን ይህም ከ2023 ከነበረው (202.8 ሚሊዮን ዶላር) የ16.6 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።
በ2024 እ.ኤ.አ አሜሪካ ከኢትዮጵያ 465.8 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ዕቃ ያስመጣች ሲሆን ይህም ከ2023 ከነበረው (24.4 ሚሊዮን ዶላር) የ5.0 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።
ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ በብዛት የሚላኩ ምርቶች;
የአውሮፕላን ክፍሎች ፣ የኤሌክትሪክ መቆጣጠሪያ ቦርዶች ፣ የኬሚካል ትንተና መሳሪያዎች እና ሌሎች የኤሌክትሪክ ማሽኖች
ከኢትዮጵያ ወደ ከአሜሪካ በብዛት የሚገቡ ምርቶች;
ቡና ፣ ፣ የአኩሪ አተር ዱቄት ፣ የተጠለፉ የህፃናት ልብሶች እና ያልተጠለፉ የወንዶች ልብሶች ፣የቁም ከብቶች
በ2024 አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር የነበራት የገቢ ወጪ ንግድ ትርፍ 551.9 ሚሊዮን ዶላር የነበረ ሲሆን ይህም ከ2023 ጋር ሲነፃፀር (178.4 ሚሊዮን ዶላር) የ24.4 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።
ባለፉት ስምንት ወራት 2 ነጥብ 5 ሚሊየን የንግድ ማህበረሰብ አዲስ የንግድ ፈቃድ አውጥቷል። ከአንድ ሺህ 300 በላይ የቅዳሜና እሁድ ገብያዎችን በማደራጀት ሸማቹን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በንግዱ ዘርፉ ላይ ለውጥ እያመጣ እንደሚገኝ ጠቅሰው የኢትዮጵያን የአለም የንግድ ድርጅት አባል ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያን የአለም የንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን የሚያስችል ተጨባጭ ተስፋ ታይቶበታል ያሉት ሚኒስትሩ የንግድ ፖሊሲው ሀገሪቱ ያላትን ዝግጁነት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።
ሀገሪቱ ጥራት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የጥራት መንደርን ከ8 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ መገንባቱን ጠቅሰው በዓመት ከ4 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን በላይ ወጪና ገቢ ምርቶችን የጥራት የማረጋገጥ ሥራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

