Skip to content
VOE
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ሔማን በቀለ – ታይም መፅሄት የዓመቱ ምርጥ ያለው ህልመኛ ታዳጊ ሳይንቲስት

    September 4, 2024

    በዩክሬን በኩል ወደ አውሮፓ የሚደርሰው የሩሲያ የተፈጥሮ ጋዝ  ስራው እንዲቆም ተደረገ

    January 1, 2025

    በኦሮሚያ ክልል ማን፣ ምን ፈጸመ? የኢሰመኮ ሪፖርት

    August 5, 2025

    በኦሮሚያ በሌብነት ጉዳይ አናቱ ተፈርቷል፤ በ289 ሺህ ካሬ.ሜ.መሬት ላይ ማጣራት ተጀምሯል

    December 3, 2022

    የአፋር ክልል ከ፴ ዓመታት በሁዋላ በትግራይ ክልል የተወሰደበትን ኣንድ ቀበሌ “ነጻ አ ወጣሁ” አለ

    June 7, 2021
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  OPINION  የጽንፈኝነት ውጤት!
OPINION

የጽንፈኝነት ውጤት!

Ethioreview newsEthioreview news—April 28, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የሩዋንዳ የዘር ፍጅት እጅግ አስከፊ የኾነ የጅምላ ጭፍጨፋ ነው። በ1994 በሩዋንዳ ውስጥ በዚህ ሳምንት በጽንፈኞች የተጀመረ ክስተት ነበር።

በ100 ቀናት ውስጥ ከ800,000 በላይ የሚገመቱ ሰዎች፣ በአብዛኛው የቱትሲ ብሔረሰብ አባላት በሁቱ አክራሪዎች እንደተገደሉ ይታመናል። የዘር ፍጅቱን የተቃወሙ መጠነኛ የሁቱ ሰዎችም ዒላማ ተደርገው ተገድለዋል።

ይህ የዘር ፍጅት የተቀሰቀሰው የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ጁቬናል ሃብያሪማና በአንድ ሁቱ ሚያዝያ 1994 አውሮፕላናቸው በጥይት ተመትቶ ሲወድቅ ነበር። የዚህ ክስተት ትክክለኛ ኹኔታ አሁንም አከራካሪ ቢኾንም፣ የሁቱ አክራሪዎች በፍጥነት የቱትሲ አማጺ ቡድን የኾነውን የሩዋንዳ አርበኞች ግንባርን (አርፒኤፍ) ተጠያቂ አድርገው ይህንን እንደ ምክንያት በመጠቀም የጅምላ ግድያውን ጀምረውታል።

ግድያው እጅግ በጭካኔ የተከናወነ ነበር። ተጎጂዎች ብዙውን ጊዜ በሰይፍ እና በሌሎች ቀላል መሣሪያዎች ይገደሉ ነበር። ዜጎች በሬዲዮ እና በሌሎች ሚዲያዎች በተሰራጨው ፕሮፓጋንዳ ግድያውን እንዲሳተፉ ይበረታቱ ነበር።

ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለዚህ የዘር ፍጅት የሰጠው ምላሽ ዘግይቷል እና በቂ አልነበረም ተብሎ በሰፊው ተተችቷል። በወቅቱ በሩዋንዳ የነበረው የተባበሩት መንግሥታት የሰላም አስከባሪ ኀይልም ሥልጣን እና በቂ ሀብት ስላልነበረው ውጤታማ በኾነ መንገድ ጣልቃ ለመግባት ሳይችል ቀርቷል።

የዘር ፍጅቱ የተጠናቀቀው በሐምሌ ወር አጋማሽ 1994 በአርፒኤፍ ፖል ካጋሜ መሪነት ሀገሪቱን በመቆጣጠር ወንጀለኞቹ እንዲሸሹ ባስገደደ ጊዜ ነበር።

የሩዋንዳ የዘር ፍጅት በሩዋንዳ ከፍተኛ የሕይወት መጥፋት፣ ሰፊ የሥነልቦና ጉዳት እና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀልን ያስከተለ ቢኾንም በእርቅ ለመፍታት ውጤታማ ሥራ የተሠራበትም ነው።

አሁን ላይ ሩዋንዳውያን ከነበረው ኹነት ተምረው ዳግም ወደ እንደዚህ አይነት ኹኔታ ላለመመለስ ተማምለው ወደ ሀገር ማልማት ገብተዋል። በምንጭነት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የተለያዩ የዓለማቀፍ ሚዲያዎችን ተጠቅመናል።

👉‹‹ድል ከሞት በኋላ››

የብዙ ሙያ ባለቤት የነበሩት ብርሃኑ ዘሪሁን በተለይም በመምህርነት፣ በትርጉም፣ በጋዜጠኝነትና በደራሲነት ሙያቸው ይታወቃሉ።

ከልጅነታቸው ጀምሮ ጎበዝ ተማሪ የነበሩት ብርሃኑ ዘሪሁን በተግባረ ዕድ ትምህርት ቤት አንደኛ በመውጣት ተሸልመዋል።

በዚያው ትምህርት ቤት መምህር ኾነው ያገለገሉ ሲኾን የውጭ መጻሕፍትን በመተርጎም እንዲኹም በተለያዩ ጋዜጦች በጋዜጠኝነት በመሥራት ሙያቸውን አዳብረዋል። በተለይም የአንጋፋው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ በመኾን ትልቅ አበርክቶ ነበራቸው።

ብርሃኑ ዘሪሁን በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ በርካታ ሥራዎችን ያበረከቱ ደራሲ ሲኾኑ ከእነዚህም መካከል 11 ልብ ወለድ ድርሰቶች እና ሦስት ተውኔቶች ይጠቀሳሉ።

‹‹የእንባ ደብዳቤዎች››፣ ‹‹ድል ከሞት በኋላ››፣ ‹‹የቴዎድሮስ እንባ›› እና የማዕበል ተከታታይ ልብ ወለዶች (‹‹ማዕበል የአብዮት ዋዜማ››፣ ‹‹ማዕበል የአብዮት መባቻ›› እና ‹‹ማዕበል የአብዮት ማግስት››) ከታወቁ ሥራዎቻቸው መካከል ይጠቀሳሉ። በተለይም ‹‹የቴዎድሮስ እንባ›› ስለ ዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስ ያልተነገሩ ታሪኮችን በማንሳት ትልቅ ተቀባይነትን አግኝተዋል።

የማዕበል ተከታታይ ልብ ወለዶች በአንድ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ተከታታይ መጻሕፍትን በማሳተም ረገድ በኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ ታሪክ የመጀመሪያው ሥራ በመኾኑ ብርሃኑን ፈር ቀዳጅ አድርጓቸዋል።

እኝህ ባለውለታ ሰው በዚህ ሳምንት ሚያዚያ 16/1979 ዓ.ም ነበር ያረፉት። ምንጭ፦ ኖርዌያዊው ሩዶልፍ ሞልቬር በኢትዮጵያ ደራሲያን ታሪክ ላይ ከጻፉት መጽሐፋቸው የተወሰደ።

👉”ለራስ የተፃፈ ደብዳቤ”

ገጣሚ፣ ፀሐፌ ተውኔት፣ ደራሲ፣ ሃያሲ፣ ተርጓሚ፣ መምህር እና የሥነ ጽሑፍ ተመራማሪው ደበበ ሰይፉ በኢትዮጵያ ሥነ-ጽሑፍ ታሪክ ሰፊ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ሰው ናቸው።

በግጥም ሥራዎቻቸው የታወቁ እና ተወዳጅ ገጣሚም ነበሩ። “የብርሃን ፍቅር” የተሰኘው የግጥም መድብላቸው እና “ለራስ የተፃፈ ደብዳቤ” የተሰኘው ሁለተኛ የግጥም መጽሐፋቸው ለተወዳጅነታቸው በማሳያነት የሚነሳላቸው ነው።

በዘመናዊ የሂስ ጥበብ ውስጥ ግንባር ቀደም ተዋናይ የነበሩት እኝህ ሰው ያለፈውን ከአሁኑ ጋር እያነፃፀረ በመተንተን እና በመዳኘት የሂስ ጥበብን በማሳደግ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።

በትያትር ጥበብ መምህርነት እና ተንታኝነታቸው የጎላ አስተዋፅኦ አበርክተዋል። የመድረክ ሥራዎችን እና የትያትር ጽሑፎችን በመተንተን ለዘርፉ ዕድገት አስተዋጽኦም አድርገዋል።

አዳዲስ የአማርኛ የሥነ-ጽሑፍ ቃላት ፈጣሪም ነበሩ። በእንግሊዝኛ ቋንቋ የነበሩ የሙያዊ ቃላትን ወደ አማርኛ በመተርጎም (“ገፀ ባህርይ”፣ “ሴራ”፣ “መቼት”፣ “ቃለ ተውኔት” ) የአማርኛን ሥነ-ጽሑፋዊ ቋንቋ አበልጽገዋል።

ለትያትር ትምህርት ዕድገት የላቀ አስተዋጽኦም አበርክተዋል። “የቴአትር ጥበብ ከጸሐፌ ተውኔቱ አንፃር” የተሰኘውን መጽሐፍ በ1973 ዓ.ም. በማሳተምም ለትምህርቱ መሠረት ጥለዋል።

በርካታ ተውኔቶችን የጻፉ እና የተረጎሙ ድንቅ ፀሐፌ ተውኔትም ነበሩ። “ከባሕር የወጣ ዓሣ”፣ “እናትና ልጆቹ”፣ “ማክቤዝ” እና “ጋሊሊዮ ጋሊሊ” ከታወቁት ሥራዎቻቸው ጥቂቶቹ ናቸው።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና ተመራማሪ በመኾን በርካታ የምርምር ሥራዎችንም አከናውነዋል። እንዲሁም በሥነ-ጽሑፍ ማኅበራት ውስጥ ንቁ ተሳታፊ በመኾን ለኢትዮጵያ ሥነ-ጽሑፍ መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦም አድርገዋል። እኝህ ባለውለታ ሰው ሚያዚያ 16/1992 ዓ.ም በዚህ ሳምንት ነበር ያረፉት። ምንጭ፦ አዲዘመን ጋዜጣ

Via አሚኮ


ኢትዮሪቬውን ከታች ባሉት ማስፈንጠሪያዎች የከተሉ – የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ ፡  @ethioreview
ፌስቡክ ገጻችንን ላይክ ያድርጉ ፡ ethioreview
ኤክስ ፡ twitter

OPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ግብጽ ሌላ አጣብቂኝ ውስጥ፤ ትራምፕ ለስዊዝ ቦይ ክፍያ የለም አሉ
አንዳርጋቸው ጽጌ ምን እያሉ ነው “ፋኖ እንደ ሃማስ?”
Related posts
  • Related posts
  • More from author
OPINION

እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ…

April 8, 2026
OPINION

ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት!

April 8, 2026
OPINION

ሙስጠፌ ተረኛው ባለስልጣን – የሃሰት ትርክ ዘመቻ በደቦ

March 28, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2