Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  ከ15 ሚሊየን ብር በላይ ለግል ጥቅም በማዋል
law

ከ15 ሚሊየን ብር በላይ ለግል ጥቅም በማዋል

Ethioreview newsEthioreview news—July 3, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የተጠረጠሩ 24 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ15 ሚሊየን ብር በላይ ለግል ጥቅም በማዋል የተጠረጠሩ የቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምርታማነት ማሻሻያ ልህቀት ማዕከል ዲንን ጨምሮ 24 ግለሰቦች ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው። ክሱ የተመሰረተው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ችሎት ነው።

ተከሳሾቹ ፍሬው አመነ በምርታማነት ማሻሻያ ልህቀት ማዕከል ዲን፣ ተፈሪ ፈይሳ የማዕከሉ ምክትል ዲን እና ኢንተርፕርነርሺፕ አሰልጣኝ፣ ሀይማኖት አቡን በማዕከሉ ምክትል ዲን፣ ወ/ሮ አሊማ መሃመድ ፋይናንስ ዳሬክተር፣ ሶስና መሃመድ ግዢ ዳይሬክተር እና እንግዳ ወንድአፍረሽ የኦዲት ዳይሬክተርን ጨምሮ 24 ናቸዉ።

1ኛ ክስ በ1ኛ፣ 3ኛ፣ 4ኛ፣ 5ኛ፣ 8ኛ፣ 9ኛ፣ 10ኛ፣ 11ኛ፣ 12ኛ እና 13ኛ ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 (1) (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 9 (1) (ሀ) እና (2) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት ወይም ለሌላ ለማስገኘት እና በመንግስት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ የሚል ነው።

1ኛ፣ 3ኛ፣ 4ኛ እና 8ኛ ተከሳሾች ያለ ክፍያ መሰጠት ያለበት ለጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የሚሰጥ ስልጠና፤ በተቋሙ የሚሰጡ ስልጠናዎች ያለ ክፍያ መሰጠት ያለበት መሆኑን የሚገልፀውን የአሰራር መመሪያ በመተላለፍ 3ኛ ተከሳሽ አበል ክፍያ እንዲፈፀም በደብዳቤ በመጠየቅ፣ 1ኛ ተከሳሽ ክፍያውን በመፍቀድ በማፅደቅ ከ459 ሺህ ብር በላይ ወደ 11ኛ ተከሳሽ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር በማስተላለፍ ለግል ጥቅማቸዉ ያዋሉ እና ያለአግባብ የስልጠና አበል ክፍያ የከፈሉ በመሆኑ።

1ኛ እና 8ኛ ተከሳሾች የስልጠና አበል 200 ሺህ ብር ወደ 11ኛ ተከሳሽ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ በማስተላለፍ ለግል ጥቅማቸዉ ያዋሉ ሲሆን ያለአግባብ የስልጠና አበል ክፍያ በመክፈል 1ኛ፣ 4ኛ እና 8ኛ ተከሳሾች፣ 8ኛ ተከሳሽ የክፍያ ሂሳብ በማዘጋጀት በመመሪያ መሰረት ሁሉም ቅድመ ሁኔታዎች ባልተሟላበት ሁኔታ እና ሊከፈል የማይገባዉ ክፍያ 300 ሺህ ብር እንዲከፈል በማድረግ፣ በ4ኛ ተከሳሽ የክፍያ ሂሳብ ፈቃጅነትና አረጋገጭነት እንዲሁም በ1ኛ ተከሳሽ ክፍያን በማፅደቅ 143 ሺህ ብር ያለአግባብ የውሎ አበል ክፍያ እንዲፈፀም ያደረጉ በመሆኑ።

በአጠቃላይ ተከሳሾች የተቋሙ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በመሆናቸዉን የተሰጣቸውን ኃላፊነት በግልፅ ተግባር በመተላለፍ ከተቋሙ ባንክ ሂሳብ ቁጥር በድምሩ 2 ሚሊየን 400 ሺህ ብር ወደ ራሳቸዉ እና የተለያዩ አካላት ባንክ ሒሳብ በማስተላለፍ ለግል ጥቅም በማዋል እና በዚሁ ልክ በማዕከሉ ላይ ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ በመሆናቸዉ፤ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል።

በሁለተኛ ክስ በተመሳሳይ በ1ኛ፣ 3ኛ፣ 4ኛ እና 13ኛ ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን ተከሳሾች በማዕከሉ በኃላፊነት እና ሰራተኝነት ተመድበው በሚሰሩበት ወቅት የማዕከሉን የአሰራር መመሪያ በመተላለፍ ወደ ማዕከሉ ገቢ መደረግ ያለበትን የአገልግሎት ክፍያ በድምሩ 4 ሚሊየን 750 ሺህ 790 ብር ወደ ግለሰቦች እና ወደ ራሳቸው የባንክ ሂሳብ ገቢ ማድረጋቸዉ በክሱ ተዘርዝሯል።

3ኛ ክስ ደግሞ በ1ኛ፣ 4ኛ፣ 6ኛ፣ 9ኛ፣ 13ኛ፣ 14ኛ፣ 15ኛ፣ 16ኛ፣ 17ኛ፣ 18ኛ፣ 19ኛ እና 21ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ የቀረበ ሲሆን፤ ተከሳሾች የመንግስትን መመሪያ በመተላለፍ ከተቋሙ ባንክ ሂሳብ ቁጥር በተለያዩ ጊዜያት 11 ሚሊየን 447 ሺህ 304 ብር ወደ ራሳቸዉ እና የተለያዩ አካላት ባንክ ሒሳብ በማስተላለፍ የማይገባ ጥቅም በማግኘት፤ በማስገኘት እና በዚሁ ልክ መንግስት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ በመሆናቸዉ፤ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል።

4ኛ ክስ በ1ኛ፣ 2ኛ እና 4ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ የቀረበ ያለ ገቢ ደረሰኝ ገንዘቡን በመቀበል ለሁሉም ሰልጣኞች ኦርጅናል ሰርተፍኬት በመስጠት ማዕከሉ ለሰጠው አገልግሎት ሊሰበሰብ የሚገባውን ገንዘብ ባለመሰብሰብ እና የተሰበሰበውንም በመመሪያው አግባብ በደረሰኝ ገቢ ያላደረጉ በመሆናቸው በዚህ ልክ በመንግስት ላይ ጉዳት ያደረሱ በመሆኑ።

የተቋሙ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሆነው ሲሰሩ የአሰራር መመሪያውን በመተላለፍ ለተቋሙ ገቢ ሊደረግ የሚገባውን ገንዘብ ገቢ አለማድረግ እና ወጪ ሊሆን የማይገባውን ወጪ በማድረግ ወደ የተለያዩ አካላት ባንክ ሒሳብ በማስተላለፍ ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ በመሆናቸዉ፤ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል።

በ1ኛ፣ 2ኛ፣ 4ኛ፣ 5ኛ፣ 7ኛ፣ 12ኛ፣ 20ኛ፣ 21ኛ፣ 22ኛ፣ 23ኛ እና 24ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ የቀረበው 5ኛ ክስ ደግሞ የተቋሙ ማኔጅመንት አባላት ሆነዉ ሲሰሩ የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት ወይም ለማስገኘት እና በመንግስት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ወጪን ለመቀነስ የተዘጋጀ የአፈጻጸም መመሪያ በመተላለፍ ለአካባቢው ማህበረሰብ እንዲሰጥ በመወሰን 80 ሺህ ብር 1ኛ ተከሳሽ የግዢ ወጪ በማዘዝ፤ 4ኛ ተከሳሽ የግዢ ወጪን በማረጋጋጥ እና ማፅደቅ፤ 7ኛ ተከሳሽ የግዢ ወጪ ሂሳብ በመስራት በግለሰቦች ሂሳብ ገቢ በማድረግ ለግል ጥቅም እንዲውል በመደረጉ እንደሆነ ተብራርቷል።

ተከሳሾቹ በአጠቃላይ ከ15 ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብን ለግል ጥቅማቸዉ በማዋል ነዉ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዩች ችሎት ክስ የተመሰረተባቸዉ።

በሲፈን መኮንን FBC

law
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ፓርላማው ለ2018 በጀት ዓመት የ1.93 ትሪሊዮን ብር በጀት አጸደቀ
የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚሰረዙባቸው ተጨማሪ ምክንያቶችን የያዘ የአዋጅ ማሻሻያ ለፓርላማ ቀረበ  
Related posts
  • Related posts
  • More from author
law

ህገወጥ የውጭ ምንዛሪ ወንጀል የፈጸሙ 123 ተጠርጣሪዎች የባንክ ሒሳብ ታገደ

September 20, 2025
law

እነ ቀሲስ በላይ በሙስና ወንጀል ሊፈርድባቸው እንደማይገባ ጠቅሰው ያቀረቡት ይግባኝ ውድቅ ሆነ

July 26, 2025
law

የአዲስ አበባ የከንቲባ ፅ.ቤት ፕሮቶኮልን ጨምሮ 12 ተከሳሾች በሌብነት ተከሰው ተፈረደባቸው

July 23, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2