Skip to content
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
  • News
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    Western Pressure on Ethiopia Intended to See Weak Gov’t, Nation – Scholars

    July 10, 20210

    Journalist demands UNWFP to tell truth about missing trucks

    October 3, 20210

    ብርሃኑ ባይህ እና አዲስ ተድላ ምህረት ሊደረግላቸው ይችላል ተባለ

    December 19, 20200

    አብንና ባልደራስ ከተሸነፉ ” ውጤቱን አንቀበልም” ሊሉ የሚችሉ ፓርቲዎች እንደሚሆኑ ዲፕሎማቶች ገለጹ

    May 23, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1866
  • Design
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ሚስጥራዊ የቻይና ፖሊስ ጣቢያዎች በአሜሪካ ተገኙ

    December 19, 20240

    ሦስተኛው ዕድል እንዳይባክን … !

    May 21, 20220

    “Why I decided to extend my time at the club”

    May 24, 20230

    የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ዋና የጦሩ መሪ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለመንግስት እጁን ሰጠ

    February 24, 20220

    “Ethiopia’s success reflects a new alternative for Africa’s development”

    January 29, 20240
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • Video
    video

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለፓርላማ የሰጡት ማብራሪያ

    July 4, 2024
    video

    የህብታቸውን ምንጭ የሚያውቁ አይሰጉም! ማብራሪያ

    June 22, 2024
    video

    የሀገር አቀፍ የምክክር ሂደት ይፋዊ የማስጀመሪያ ሥነ ስርዓት

    June 4, 2024
    video

    የምክክር ሂደት ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር

    June 4, 2024
    Prev Next Showing 1 Of 5
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • News
  • Design
  • Video
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  ብልጽግና የኢትዮጵያን ጠላቶች ዕቅድና ማክሸፊያውን አስታወቀ
News

ብልጽግና የኢትዮጵያን ጠላቶች ዕቅድና ማክሸፊያውን አስታወቀ

Ethioreview newsEthioreview news—August 8, 20250
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ተላላኪዎቻቸውን በማሰማራት ኢትዮጵያን ከመንገዷ ለማስቀረት የመጨረሻ ሙከራ ለማድረግ ያቀዷቸው ስልቶችን ብልጽግና አመለከተ። ማከሸፊያ ያለውንም በዝዝር አስቀምጧል።

ከሐምሌ 30 ጀመሮ እስከ ነሃሴ ሁለት ስብሰባ ላይ የቆየው የብልጽግ ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ እነዚሁ ኃይሎች ኢትዮጵያን ለማተረማመስና ከጀመረችው ጎዳና ለማደነቃቀፉ ስድስት ስልቶችን መንደፋቸውን አስታውቋል። ሲዘረዝርም ለግድያ የሚፈላለጉ ኃይሎችን በጥቅም ማስተሣሠር፣ ኢትዮጵያን በሁከት ውስጥ ማቆየት፤ በመልካም አስተዳደር ችግር የተነሣ የሚፈጠሩ የሕዝብ ቅሬታዎችን ለዐመጽ መጠቀም፤ ብሶት ቀስቃሽ አጀንዳዎችን ማራገብ፤ በውጭ ምንዛሬ እና በሸቀጦች በኩል የኢኮኖሚ አሻጥርና ሚዲያዎችን የሁከት መቀስቀሻ መሣሪያ ማድረግ መሥራት እንደሆኑ አምልክቷል።

የብልፅግና ፓርቲ ም/ቤት የታሪካዊ ጠላቶችን የመጨረሻ ሙከራ ለመጨረሻ ጊዜ ለማምከን በቁርጠኝነት ለማከናወን ያስቀመጣቸው ሰባት ጉዳዮችንም ዘርዝሯል። በዚሁ መሰረት

ግጭትን ሊያስቀሩ የሚችሉ ሰላማዊ አማራጮችን በሁሉም አቅጣጫ ለመሞከርና በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለሚወስኑ ታጣቂዎች አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ፤

  • የሰላምን አማራጭ ባለመቀበል በሕዝብና በሀገር ንብረት ላይ ችግር ለመፍጠር በሚነሡ ኃይሎች ላይ በተጠናከረ መንገድ ሕግ ለማስከበር፤
  • በየደረጃው የሚነሡ የሕዝብ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሕና የኢኮኖሚ ጥያቄዎችን በኢትዮጵያ ዐቅም ልክ በየደረጃው ለመመለስ፤
  • ተገቢውንና እውነተኛውን መረጃ ለሕዝብ በየጊዜው ለመስጠትና ሐሰተኛ መረጃዎችን ለማጋለጥ፤
  • በየተቋማቱ ተመድበው የዲሲፕሊን ጉድለት፣ሙስናና የአስተዳደር በደል የሚያደርሱ የሥራ መሪዎችንና አገልጋዮችን ለመታገል፤
  • በግብርና፣ በአምራች ኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ እንደዚሁም በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመርናቸውን የልማት ሥራዎች የበለጠ ስኬታማ በማድረግ፤ የተጀመሩ ኢኒሼቲቮችን ለውጤት በማብቃት፤ የሕዝብን ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ የከተማና የገጠር ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ፤
  • በዲፕሎማሲው መስክ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች በሁሉም መንገድ ለማስከበር፤ የሚሉ ናቸው
More stories

በመተከልና ሌሎች አካባቢዎች ተፈጥረው በነበሩ ግጭቶች የሱዳንና የግብፅ እጅ እንዳለበት ተገለጸ

March 5, 2021

የመከላከያን ጨምሮ የአሜሪካንን ሚስጢር “ለትውልድ አገሩ አቀብሏል” የተባለው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ” ብሄራዊ ጀግና” እየተባለ ነው

October 1, 2023

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ወይም ሞት እያለ ነው

March 22, 2022

“የኢትዮጵያ አምላክ እንደ ወትሮው ከእኛ ጋር ነበር ” ዐቢይ አህመድ ወደ ቢሮ መመለሳቸውን ገለጹ

December 8, 2021

የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት ሙሉ መግለጫ

እኛ የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ከሐምሌ 30 እስከ ነሐሴ 02 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረግነው መደበኛ ስብሰባ በዓለማዊ፣ አህጉራዊ፣ ቀጣናዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በዝርዝር ተወያይተናል።

ምክር ቤታችን አሁን ባለው የጂኦ ፖለቲካ ሁኔታ ውስጥ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ስለሚከበርበት መንገድ ተመልክቷል፡፡ በመደመር መንገድ ወደ ብልጽግና ለመድረስ እየተደረገ ስላለው ጥረትም ገምግሟል።

በዓለማችን ላይ እየተፈጠሩ ያሉ ጂኦ ፖለቲካዊ ሁኔታዎች ለሀገራችን ዕድልና ፈተና ይዘው መምጣታቸውን የተመለከተው ምክር ቤቱ፣ ፈተናዎችን በመሻገርና ዕድሎችን በመጠቀም ይበልጥ የሀገራችንን ጥቅም ስለምናስጠብቅባቸው ስልቶች በስፋት ተነጋግሮ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

እንደሚታወቀው፣ ከጥቂት ዓመታት በፊት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የገጠመንን ጦርነት በአሸናፊነት ተወጥተናል። በአሸናፊነት መወጣት ብቻ ሳይሆን፣ ወታደራዊ ድላችንን በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ቋጭተናል። ዳሩ ግን ይፈልጉት የነበረው የተራዘመ ጦርነት በስምምነቱ የተጨናገፈባቸው ጠላቶቻችን ሌሎች ስልቶችን ወደ መሞከር ገብተዋል።

ምንም እንኳን እንዳሰቡት እየሆነላቸው ባይሆንም፣ እነዚህ አካላት በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኞችን በመጠቀም የመንግሥትን ኃይልና የሕዝብን አንድነት ለመከፋፈል ጥረት ማድረጋቸውን ቀጥለዋል። በታሪካዊ ጠላቶቻችን መሪነት እና አስተባባሪነት፣ በአንዳንድ ባንዳ ጽንፈኞች መሣሪያነት ዛሬም ጠላቶቻችን የጦርነት አምሮታቸው አልቆመም።

ባለፉት ሁለት ዓመታት ጠላቶቻችን የሕዝብንና የመንግሥትን አንድነት ለመፈታተን ሁለት መንገዶችን ተጠቅመው ነበር። አንደኛው በየአካባቢው ግጭትን ማበራከት ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በዲጂታል ሚዲያ መንግሥትን ማሳጣት ነው። ነገር ግን በሁለቱም ዘመቻዎች እንዳሰቡት አትራፊ መሆን አልቻሉም። ኢትዮጵያን የማዳከም ዕድላቸው እየጠበበ ነው። ባለንበት ልንከስም እንችላለን የሚለው ሥጋታቸውም ጨምሯል።

ዛሬ ያለነው ትውልድ፣ ከታሪካዊ ስብራቶቻችን እና ከዓለም ነባራዊ እውነታ ተምረናል። እንደ ድሮው በተቀደደልን ከመፍስስ ይልቅ፣ ብሔራዊ አንድነታችንንና ተቋማዊ ዐቅማችንን ለማጠናከር እየሠራን ሲሆን ይሄም ተጋላጭነታችንን በእጅጉ ቀንሶታል። ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ ብሔራዊ ራዕያችንን ማሳካት የሚችል ብሔራዊ ዐቅም መገንባታችን ይቀጥላል።

ከሁሉ በላይ አዲሱ ስልታችን ሰላማዊ የፖለቲካ ዕድሎችን አሟጥጦ ይጠቀማል። ተግዳሮቶች በበረቱባቸው ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ በሁሉም መስክ ድል አስመዝግበናል። በተለይም በሦስት ብሔራዊ አጀንዳዎች ላይ ተጨባጭ ለውጥ አምጥተናል፡-

• ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጦች በተግዳሮቶች ሳይበገሩ አንሠራርተዋል። ይሄም ውስጣዊ ተጋላጭነታችንን አጥብቦ፣ ባንዶችን ቦታ አሳጥቷል።

• በዓባይ ላይ ተገቢውንና ሕጋዊውን ተግባር በማከናወን በቀጣናው ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመናችንን ለውጠናል።

• የባሕር በር የማግኘት ተፈጥሯዊና ታሪካዊ መብታችንን ዓለም አቀፍ አጀንዳ አድርገነዋል። በዚህም በቀይ ባሕር የነበረንን ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና ለመመለስ ከአንድ ምዕራፍ በላይ ተራምደናል።

ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጦቻችን በተግዳሮቶች ሳይረቱና ሳይዋጡ በስኬት እየተራመዱ ናቸው፡፡ ለውስጣዊ ተጋላጭነታችን መነሻ መሆናቸው ቀርቶ፣ ወደ ብሔራዊ ዐቅምነት ተቀይረዋል። ውስጣዊ ስንጥቃቶችን በሽብልቅ እያሰፉ፣ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር አብረው ኢትዮጵያን ለመውጋት ለሚተባበሩ ባንዳዎች፣ ብሔራዊና ብሔረሰባዊ አጀንዳ አሳጥተናቸዋል። ፖለቲካችን ማንነትን ከሚያጫርተው የፖለቲካ ገበያ እንዲወጣ አድርገነዋል። በኅብረ ብሔራዊ አንድነት ላይ ተመሥርቶ ብልጽግናን በሚያረጋገጥ መንገድ ቀይሰነዋል።

በአንድ በኩል በጀመርናቸው ተቋማዊ ሪፎርሞች እና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች የሀገራችንን ውስጣዊ ዐቅም አጠናክረናል። በሌላ በኩል ደግሞ የጂኦፖለቲካውን ቅኝት በሚገባ በመገንዘብ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች አስከብረናል።

ኢትዮጵያ ያለ ጥርጥር እያንሠራራች ነው። በዓይን አይቶ፣ በእጅ ነክቶ፣ በመረጃ አጣርቶ፣ በመስክ ተሠማርቶ፣ ይሄንን እውነት ማረጋገጥ ይቻላል። ከሀገራዊ እስከ ዓለማዊ መድረኮች ለዚህ ስኬት ሚልዮን ምስክሮች አሉ። ይህ ግን ለታሪካዊ ጠላቶቻችንና ለእነርሱ ተላላኪዎች የሚዋጥላቸው አይደለም። ስለዚህም ኢትዮጵያን ከመንገዷ ለማስቀረት የመጨረሻውን ሙከራ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

በዚህ የመጨረሻ ሙከራቸው ስድስት ስልቶችን ለመጠቀም እንደተነሡ ምክር ቤታችን ገምግሟል። እነዚህም ለግድያ የሚፈላለጉ ኃይሎችን በጥቅም ማስተሣሠር፤ ኢትዮጵያን በሑከት ውስጥ ማቆየት፤ በመልካም አስተዳደር ችግር የተነሣ የሚፈጠሩ የሕዝብ ቅሬታዎችን ለዐመጽ መጠቀም፤ ብሶት ቀስቃሽ አጀንዳዎችን ማራገብ፤ ሚዲያዎችን የሑከት መቀስቀሻ መሣሪያ ማድረግ፤ እንዲሁም በውጭ ምንዛሬ እና በሸቀጦች በኩል የኢኮኖሚ አሻጥርን መሥራት ናቸው።

ይሄንን የታሪካዊ ጠላቶቻችን የመጨረሻ ሙከራ ለመጨረሻ ጊዜ ለማምከን እኛ የብልፅግና ምክር ቤት አባላት በቃልም በተግባርም ዝግጁ፣ ቆራጥና ውጤታማ መሆን እንዳለብን ተገንዝበናል። በዋናነትም በሚከተሉት ሰባት ጉዳዮች ላይ ከሚጠበቅብን በላይ ለማከናወን ቆርጠን ተነሥተናል።

• ግጭትን ሊያስቀሩ የሚችሉ ሰላማዊ አማራጮችን በሁሉም አቅጣጫ ለመሞከርና በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለሚወስኑ ታጣቂዎች አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ፤

• የሰላምን አማራጭ ባለመቀበል በሕዝብና በሀገር ንብረት ላይ ችግር ለመፍጠር በሚነሡ ኃይሎች ላይ በተጠናከረ መንገድ ሕግ ለማስከበር፤

• በየደረጃው የሚነሡ የሕዝብ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሕና የኢኮኖሚ ጥያቄዎችን በኢትዮጵያ ዐቅም ልክ በየደረጃው ለመመለስ፤

• ተገቢውንና እውነተኛውን መረጃ ለሕዝብ በየጊዜው ለመስጠትና ሐሰተኛ መረጃዎችን ለማጋለጥ፤

• በየተቋማቱ ተመድበው የዲሲፕሊን ጉድለት፣ሙስናና የአስተዳደር በደል የሚያደርሱ የሥራ መሪዎችንና አገልጋዮችን ለመታገል፤

• በግብርና፣ በአምራች ኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ እንደዚሁም በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመርናቸውን የልማት ሥራዎች የበለጠ ስኬታማ በማድረግ፤ የተጀመሩ ኢኒሼቲቮችን ለውጤት በማብቃት፤ የሕዝብን ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ የከተማና የገጠር ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ፤

• በዲፕሎማሲው መስክ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች በሁሉም መንገድ ለማስከበር፤ ከመግባባት ላይ ደርሰናል።

በአጠቃላይ እኛ የብልፅግና ምክር ቤት አባላት፣ የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ከታቀደለት ጊዜ ፈጥኖ እንዲሳካ ለማድረግ “መመከት፣ መትጋትና ማጥራት” በሚል መርሕ ቀጣዩን ተግባራችንን ለማከናወን ወስነናል። የጠላቶቻችንን ፈተና እና ሤራ እንመክታለን። የኢትዮጵያ ብልጽግና በሁሉም መስክ እንዲሳካ ከወትሮው በበለጠ እንተጋለን። ለብልጽግና ጉዟችን ዕንቅፋት የሚሆኑትን አስተሳሰቦች፣ ባህሎች፣ ልማዶች፣ ሠርጎ ገቦች እና ባንዳዎች ደግሞ ተግተን እናጠራለን።

እኛ የምንወደው ሀገር፣ የምንቆምለት ሀገራዊ ዓላማ እና ሕልም አለን። የምናገለግለው ሕዝብ አለን። የምንገነባው ሀገር አለን። የሚናስከብረው ብሔራዊ ጥቅም አለን። ጠላት ደግሞ እነዚህን ሁሉ ማጥፋት፣ ለማፍረስና ለማሰናከል ይፈልጋል። ማልማት፣ መገንባት እና ማጽናት፤ ከማጥፋት፣ ከማደናቀፍ፤ ከማሰናከል እና ከማፍረስ በላይ ዐቅምና ትጋት ይጠይቃል።

ድል እና ኢትዮጵያ የተሣሠሩ ናቸው። ነገር ግን ከድሎች ሁሉ የሚበልጥ ድል አለ፡፡ እሱም ድልን በአነሰ ኪሣራ ማረጋገጥ እና ከዘላቂ ውጤት ጋር ማስተሣሠር ነው። ከድል ሁሉ የሚበልጠው ድል፣ ድልን ብቻ ሳይሆን ስትራቴጂያዊ ግብን ጭምር ማረጋገጥ ነው። ዘላቂ ድል ማለት ውስጣዊ ባንዳዎችን ብቻ ሳይሆን ውጫዊ ጠላቶችን ጭምር ስትራቴጂያዊ በሆነ መንገድ መርታት ነው።

ብልጽግና ብዝኃ ዐርበኝነትን ይጠይቃል። የደም ብቻ ሳይሆን የላብ መሥዋዕትነትን ይጠይቃል። ዐርበኝነት እና ዝግጁነት የሀገርን ታሪክ ይቀይራሉ። እኛ የብልፅግና ምክር ቤት አባላት ራሳችን ተግተን ሕዝብንም ለማትጋት ተነሥተናል። ራሳችን ጠርትን ሕዝቡንም ለማጥራት ወስነናል። እንደ ዐርበኛ አመራር በልካችን ለመታገል ቆርጠናል። የብልፅግና አመራር የኢኮኖሚም የግንባርም ዐርበኛ ነው። ሕዝብን ያስተባብራል። በግንባር ይፋለማል። ደጀኑንም ያጠናክራል። እኛም ይሄንን ከወትሮው በበለጠ ለመፈጸም ቃላችንን በድጋሚ እናድሳለን።

ዘመናችን ብዝኃ ታታሪነትን ይጠይቃል። ዓለም ተለዋዋጭ እና ብዙ ቀውስ አለበት። ሀገራችን ዘርፈ ብዙ የሕዝብ ፍላጎቶችና ችግሮች አሉባት። እንዲሁም የተለያዩ አደናቃፊ ኃይሎች ይፈትኗታል። እንዲህ ባለ ጊዜና ሁኔታ አመራርነት ዘርፈ ብዙ ብቃቶችን እና ታታሪነቶችን እንደሚጠይቅ ተረድተናል። ታሪካዊ ጠላቶቻችን እና ውስጣዊ ባንዳዎች ኢትዮጵያን ለማዳከም ቆርጠው ተነሥተዋል። በዚህ ወቅት በአንድ በኩል የጠላትን ጥቃት መከላከል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ዘላቂ ግቦቻችንን እና ዓላማዎቻችንን መተግበር እንደሚያስፈልገን በዝርዝር ተነጋግረን ወስነናል። በየደረጃው ያለን አመራሮች በአንድ ጊዜ ብዙ ተግባራትን የምንፈጽም መሆን እንዳለብን የተግባባን ሲሆን፤ ጠላትን ስንከላከል እና ጸጥታን ስናስከብር ከልማት የምንደናቀፍ መሆን የለብንም።

ብልፅግና ብዝኃነታችንን ያከበረ፤ አንድነታችንን ያስተሣሠረ ፓርቲ ነው። ከትናንት የተማረ ነገን ያሣመረ ትርክት ያነገበ ፓርቲ ነው። የጠላትን አፍራሽ ትርክት ለመመከትና የእኛን ትርክት ለማጋባት ዲጂታል ዐርበኝነትን በሚገባን ልክ እንጠቀማለን። ጠላት የሀገርን አንድነት ለማፍረስ እና ብልጽግናዋን ለማደናቀፍ በበቀል ስሜት አፍራሽ ትርክት ሰንቆ ተነሥቷል። እኛ ማንነታችን የተሣሠረበትን እና ርዕያችን የተሰነቀበት ትርክታችንን ለሕዝብ ለማጋባት ዐርበኛ ልንሆን ወስነናል።

ሕዝብን እያማረሩ ያሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍ እና የሕዝብን ርካታ ለመጨመር በትኩረት እንሠራለን። የሕዝብን የቅሬታ ምንጮች በመለየት እንፈታለን። የሕዝብን ቅሬታ በመስማት፣ በዕቅድና በክትትል ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እንተጋለን። ሕዝባዊና ብሔራዊ ለሆነው ዓላማችን ውስጣዊ ዕንቅፋት የሆነው ሠርጎ ገብነትን እናጠራለን፤ ብሔርተኝነትን እንገራለን፤ ሌብነትንና ሕዝበኝነትን ለማጥፋት እንታገላለን። በውጭና በሀገር ውስጥ የሚኖረው የውጭ ምንዛሬ እንቅስቃሴ በሀገር ፍቅር ስሜት እንዲንቀሳቀስ በማድረግ፣ እንዲሁም የሸቀጦችን ዝውውር ጤናማነት በማረጋገጥ፣ የኢኮኖሚ አሻጥር የሚሠሩ የውጭና የውስጥ ጠላቶችን እንታገላለን፡፡

ከዚህም በተጨማሪ መጪው ሰባተኛ ሀገራዊ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ፣ ሕጋዊ፣ እና የሕዝቡ ምልዐተ ተሳትፎ የሚንጸባረቅበት እንዲሆን እንደ ብልፅግና ፓርቲ አመራርና አባል ብሎም እንደ ኢትዮጵያዊ ዜጋ በንቃት እንሳተፋለን።

ከላይ የገለጽናቸው ውሳኔዎቻችንና ቃል የገባናቸው ግቦች ተሳክተው የኢትዮጵያን ብልጽግና በአስተማማኝ መሠረት ላይ ለመመሥረት እንድንችል፣ መላው የብልፅግና አባላትና ኢትዮጵያውያን በኅብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲሰለፉ ጥሪ እናደርጋለን።

የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

Ethioreview news

A journalist

ብሔራዊ ባንክ በዱባይ ያሉ ድርጅቶን ተጠንቀቁ አለ
አፍሪካ ልማት ባንክ ለግዙፉ አየር ማረፊያ ግንባታ ገንዘብ የማሰባሰብ ኃላፊነቱን ሊረከብ ነው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 20260
Load more
Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 20260
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 20260
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 20260
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedbusinesshotarchivetips
    © Copyright 2026, All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2
    • Home Demo news