Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ክቡር ገና በመጪው ምርጫ ኢዜማን ወክለው በአዲስ አበባ ምክር ቤት ለመወዳደር በዕጩነት ቀረቡ
News

ክቡር ገና በመጪው ምርጫ ኢዜማን ወክለው በአዲስ አበባ ምክር ቤት ለመወዳደር በዕጩነት ቀረቡ

Ethioreview newsEthioreview news—January 23, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በተስፋለም ወልደየስ

የቀድሞው የኢትዮጵያ እና የአዲስ አበባ ምክር ቤት ፕሬዘዳንት የነበሩት አቶ ክቡር ገና፤ በመጪው ምርጫ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲን ወክለው በአዲስ አበባ ምክር ቤት ለመወዳደር በዕጩነት ቀረቡ። በኢዜማ የመሪነት እና የምክትል መሪነት ስልጣን ያላቸው ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አንዷለም አራጌ፤ ለተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመመረጥ ከሌሎች የፓርቲው እጩዎች ጋር በነገው ዕለት ይፎካከራሉ።

ኢዜማ፤ ፓርቲውን ወክለው ለተወካዮች ምክር ቤትም ሆነ ለክልል ምክር ቤቶች የሚወዳደሩ ዕጩዎችን የሚያስመርጠው፤ በየምርጫ ወረዳዎቹ ባሉ ጠቅላላ ጉባኤ አባላት በሚሰጥ ድምጽ ነው። ፓርቲው አሉኝ ከሚላቸው 435 የምርጫ ወረዳዎች ውስጥ በ329ቱ የዕጩዎች ምርጫ አካሄዶ ማጠናቀቁን አስታውቋል። በዛሬ እና በነገው ዕለት ደግሞ በ71 የምርጫ ወረዳዎች የዕጩዎች ምርጫ ለማካሄድ ቀነ ቀጠሮ ይዟል። 

በነገው ዕለት ከሚካሄዱ የፓርቲው የምርጫ ዕጩዎች ፉክክር ውስጥ፤ በአዲስ አበባ ከተማ የሚደረጉቱና ዕውቅ ግለሰቦች የሚሳተፉባቸው ውድድሮች የሚጠበቁ ሆነዋል። ከዚህ ቀደም ከኢዜማ ጋር በተያያዘ ስማቸው ተነስቶ ከማያውቀው ከአቶ ክቡር ገና በተጨማሪ ቀድሞ በግብርና ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታነት አገልግለው የነበሩት ዶ/ር በላይ በጋሻው በነገው የዕጩዎች ምርጫ እንደሚሳተፉ ከፓርቲው የተገኘው መረጃ ያመለክታል። 

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

አቶ ክቡር ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ለመወዳደር በዕጩነት የቀረቡት በሚኖሩበት ወረዳ 21 እና 22 ነው።  የፓርቲው ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት አቶ ክቡር ኢዜማን በአባልነት የተቀላቀሉት ከሁለት ሳምንት በፊት ቢሆንም እርሳቸውን ለማግባባት ጥረቶች ሲደርጉ የቆዩት ካለፈው ዓመት ግንቦት ወር ጀምሮ ነው። 

ኢዜማ “ለምክር ቤቶች የሚደረጉ የዕጩዎች ውድድርን” አስመልክቶ ያወጣው ህግ፤ አባል ከሆኑ ስድስት ወር ያልሞላቸው አባላት የመመረጥም ሆነ የመምረጥ መብት እንደሚኖራቸው ይደነግጋል። እነዚህ አዲስ አባላት ይህን መብት ለማግኘት ግን ወደ ኋላ ተመልሰው የስድስት ወር የአባልነት መዋጮ መክፈል እንደሚጠበቅባቸው ያትታል። ኢዜማ ይህን አካሄድ የተከተለው፤ ፓርቲው ከተመሰረተ አጭር ጊዜ አንጻር “ስድስት ወር ያልሞላው አባል መምረጥና መመረጥ እንዳይችል ማገድ የፓርቲውን የተሻሉ ዕጩዎች የማቅረብ አቅም የሚያጠብ በመሆኑ” እንደሆነ በህጉ ላይ አብራርቷል። 

የዚህ ህግ ተጠቃሚ የሆኑት ሌላኛው ዕጩ ዶ/ር በላይ በጋሻው ናቸው። መኖሪያቸውን ለበርካታ ዓመታት በአሜሪካ ያደረጉት እኚሁ ተወዳዳሪ፤ በምርጫው ላይ ለመሳተፍ በማሰብ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሱ በኋላ፤ ኢዜማን በአባልነት የተቀላቀሉት የዛሬ ወር ገደማ መሆኑን የፓርቲው ምንጮች ተናግረዋል። ዶ/ር በላይ ኢዜማን ወክለው ለተወካዮች ምክር ቤት በተወዳዳሪነት ለመቅረብ የሚፎካከሩት በአዲስ አበባ ወረዳ 15 ነው። 

ኢዜማ እንደ አቶ ክቡር እና ዶ/ር በላይ አይነት “በስራቸውም፣ በልምዳቸውም” የሚታወቁ ግለሰቦችን በመጪው ምርጫ በተወዳዳሪነት ለማሳተፍ ለበርካቶች ጥያቄዎች አቅርቦ እንደነበር የሚናገሩት አንድ የፓርቲው ምንጭ፤ ሆኖም ብዙዎቹ የፓርቲውን ጥያቄ ሳይቀበሉ በመቅረታቸው ጥረቱ ሳይሳካ መቅረቱን አስረድተዋል። ስለ ጉዳዩ የተጠየቁት የኢዜማ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ናትናኤል ፈለቀ፤ ፓርቲው በዚህ ምርጫ በህዝብ ዘንድ ከሚታወቁ ሰዎች ይልቅ፤ በሚኖሩባቸው አካባቢዎች አስፈላጊ ለሆኑ ሰዎች ይበልጥ ትኩረት መስጠቱን ተናግረዋል። 

ባለፉት ሳምንታት በተካሄዱ የዕጩ ተወዳዳሪ ምርጫዎች ኢዜማን እንዲወክሉ ከተመረጡት ውስጥ አብዛኞቹ ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በታች መሆኑ የጠቀሱት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው፤ ይህም ፓርቲው “ለወጣቶች እና የመስራት ፍላጎት ላላቸው ሰዎች የሰጠውን ቦታ ያመለክታል” ብለዋል። በዕጩ ተወዳዳሪነት ከተመረጡት ውስጥ አብዛኞቹ “ትምህርት ቀመስ” መሆናቸውንም አክለዋል። 

ኢዜማ እያካሄደው ባለው የዕጩዎች ምርጫ፤ በፓርቲው መዋቅር ውስጥ ቁልፍ ቦታ የያዙ ግለሰቦች በተወዳዳሪነት ሳይሳተፉ ቀርተዋል። ከተወዳዳሪነት ውጪ እንዲሆኑ ከተደረጉት ውስጥ የኢዜማ ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ ምክትላቸው ዶ/ር ጫኔ ከበደ እንዲሆም የፓርቲው ዋና ጸሀፊ አቶ አበበ አካሉ ይገኙበታል።  

የፓርቲዎቹ አመራሮች በምርጫው የማይሳተፉት በፓርቲው ህገ ደንብ በተቀመጠባቸው ክልከላ ምክንያት እንደሆነ አቶ ናትናኤል ተናግረዋል። ከእነርሱ በተጨማሪ የፓርቲው የምርጫ ወረዳዎች በሊቀመንበርነት፣ በምክትል ሊቀመንበር እና በጸሀፊነት የሚያገለግሉ አመራሮችም በህገ ደንቡ መሰረት በተወዳዳሪነት እንደማይሳተፉ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አስረድተዋል። የኢዜማ ህገ ደንብ ከምርጫ ተሳትፎ የማያግዳቸው የፓርቲው መሪ እና ምክትላቸው ግን በነገው ዕለት በዕጩዎች ምርጫ ላይ እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል።

የኢዜማ መሪ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በመኖሪያቸው ወረዳ 23፤ ፓርቲውን ወክለው ለተወካዮች ምክር ቤት በዕጩነት ለመቅረብ ከሌሎች ሶስት የፓርቲው አባላት ጋር ነገ እሁድ ይወዳደራሉ። የእርሳቸው ምክትል የሆኑት አቶ አንዷለም አራጌም ተመሳሳይ ቁጥር ካላቸው ተፎካካሪዎች ጋር በወረዳ 12 እና 13 ለምርጫ ይቀርባሉ። 

እያንዳንዱ የፓርቲው የምርጫ ወረዳ፤ ለተወካዮች ምክር ቤት በዕጩ ተወዳዳሪነት የሚያሳልፈው አንድ ግለሰብ ቢሆንም በወረዳ 24 ግን በተቃውሞ ፖለቲካ ዝና ያላቸው ሁለት ግለሰቦች ለምርጫ እንደሚወዳደሩ ታውቋል። ተወዳዳሪዎቹ ዕውቁ ኢኮኖሚስት ዶ/ር በፍቃዱ ደግፌ እና በርካታ ዓመታትን በእስር ያሳለፈው ክንፈሚካኤል አበበ (አበበ ቀስቶ) ናቸው።

በአንድ ወቅት ብቸኛ የተቃዋሚ የፓርላማ አባል የነበሩት አቶ ግርማ ሰይፉ፤ ኢዜማን ወክለው በድጋሚ ወደ ተወካዮች ምክር ቤት ለመግባት በሚቀጥለው ሳምንት በሚኖሩበት ወረዳ 6 ከሌሎች ፓርቲ አባላቶች ጋር እንደሚፎካከሩ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ መሰረት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች የዕጩዎች ምዝገባ ከየካቲት 8 እስከ 21 ባሉት ቀናት ይካሄዳል። ዕጩዎቹ የምረጡኝ ቅስቀሳ ወይም የምርጫ ዘመቻ እንዲያካሄዱ የተፈቀደላቸው ከየካቲት 8 እስከ ግንቦት 23 ባለው ጊዜ ነው።

(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የገንዘብ ማስተላፍ ገደብ ተግባራዊ ከሆነ በሁዋላ የውጭ ምንዛሬ የጥቁር ገበያ ዋጋ ቅናሽ አሳየ
“ነጭ ቀለም ያላቸው የአረብ ወታደሮች በኢትዮ ሱዳን ድንበር እየሰፈሩ፣ አዳዲስ ከምፕ እየገነቡ ነው”
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2