Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  በማይካድራ ከተማ ከ17.6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙ ተገለጸ
News

በማይካድራ ከተማ ከ17.6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙ ተገለጸ

Ethioreview newsEthioreview news—February 28, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በንፁኃን ግድያ የተጠረጠሩ ‹‹እኛ ሰላማዊ ዜጎች ነን›› አሉ

ጥቅምት 30 እና ኅዳር 1 ቀን 2013 ዓ.ም. በማይካድራ ከተማ በደረሰ ጉዳት ከ17.6 ሚሊዮን ብር በላይ ውድመት መድረሱ ተገለጸ፡፡

ይኼ የተገለጸው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን በከተማው በተጠቀሱት ቀናት በንፁኃን ነዋሪዎች ላይ ዘርን መሠረት ባደረገ ግድያ ላይ ተሳትፈዋል በማለት ተጠርጥረው የታሰሩ 36 ተጠርጣሪዎችን፣ የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ባቀረበበት ወቅት፣ በተፈቀደለት የምርመራ ጊዜ የሠራውን የምርመራ ሪፖርት ለፍርድ ቤት ሲያቀረብ ነው፡፡ 

ቡድኑ ለፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት እንዳስረዳው፣ በከተማው የደረሰውን የንብረት ጉዳት የሚያሳይ ፎቶና የቪዲዮ ማስረጃዎችን ማሰባሰቡን ተናግሯል፡፡ ቡድኑ የ20 ሰዎች የምስክርነት ቃል መቀበሉን፣ ከጎንደር ሪፈራልና ከሳንጃ ሆስፒታሎች የ177 ሰዎችን የጉዳት መጠን የሚገልጽ ማስረጃዎች ማሰባሰቡንም አክሏል፡፡

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ተጨማሪ የሰው ምስክሮች ቃል መቀበል፣ ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የ117 ጅምላ መቃብር የወጣ የአስከሬን ምርመራ ውጤት መቀበልና ከወንጀሉ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ማስረጃዎች ማሰባሰብ እንዲችል ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡ 

የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች ባቀረቡት መከራከሪያ ሐሳብ እንደገለጹት፣ መርማሪ ቡድኑ ያቀረበው ሪፖርት ቀደም ብሎ ካቀረበው ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ የምርመራ ሒደቱን የሚያሳየው ሰነድ (ለፍርድ ቤቱ ያቀረበውን) ኮፒ ምርመራው ምን ላይ እንደደረሰ ለመከታተል እንዲረዳቸው ኮፒ እንዲሰጣቸውም ጠይቀዋል፡፡

የወንጀል ምርመራ የሚደረገው አንድ ሰው የፈጸመው የወንጀል ተሳትፎ ተለይቶ ሲታወቅ መሆኑን ጠቁመው፣ በማይካድራ በንፁኃን ሰዎች ላይ ጭፍጨፋ (ፖሊስ እንደሚለው) ተሳትፋችኋል ብሎ እየመረመራቸው በመሆኑ፣ ተሳትፏቸውን ለይቶ ማቅረብ እንዳለበት፣ ይህ ካልሆነ ግን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መፈቀድ እንደሌለበትም ተናግረዋል፡፡

ድርጊቱ የተፈጸመው ጥቅምት 30 እና ኅዳር 1 ቀን 2013 ዓ.ም. በመሆኑ ሦስት ወራት ከ18 ቀናት እንደሆነው ጠበቆቹ አስታውሰው፣ መርማሪ ቡድኑ በሦስት ወራት ውስጥ የተጠርጣሪዎችን ተሳትፎ ለይቶ እንዲያቀርብ ማድረግ ካልተቻለ፣ መርማሪ ቡድኑ የጅምላ ምርመራ ውጤትን ማቅረብ እንደ አማራጭ እየተጠቀመበት እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡

በወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁጥር 59(2) ድንጋጌ ላይ የጊዜ ቀጠሮ መጠየቂያ ገደብ ባይቀመጥም፣ ኢትዮጵያ ፈርማ የሕጓ አካል ባደረገቻቸው ዓለም አቀፍ የሕግ ድንጋጌዎችና አፍሪካ ሰብዓዊ መብት ቻርተር መሠረት መሥራት እንዳለበትም ጠቁመዋል፡፡ በጣም ውስብስብና በርካታ አካላት ተሳትፈውበት የሚፈጸመውን የሽብር ወንጀል ለመከላከል ወጥቶ ሲሠራበት የነበረው የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 እንኳን ከአራት ጊዜ በላይ ጊዜ ቀጠሮ እንደማይሰጥም አስታውሰዋል፡፡ በ108 ቀናት ውስጥ የተጠርጣሪዎችን ተሳትፎ ለይቶ ማቅረብ ካልተቻለ ገና በርካታ 14 ቀናቶች እንደሚቀሩም አክለዋል፡፡

በምርመራ መዝገቡና በጊዜ ቀጠሮ መጠየቂያው ሰነድ ላይ የሚኖረው የምርመራ ይዘት ተመሳሳይ ነው ብለው እንደሚያምኑ የተናገሩት ጠበቆቹ፣ በምርመራ መዝገቦች ላይ የሚጠቀሱት ከባባድ ድርጊቶች የዋስትና መብት ለማስከልከል ‹‹ተጠርጣሪዎቹ ከሕወሓትና ኦነግ ሸኔ ጋር በመቀናጀት የተፈጸመ ወንጀል ነው፤›› በማለት እየቀረበ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ነገር ግን ፍርድ ቤቱ መገንዘብ እንደሚችለው በችሎት የቀረቡት ተጠርጣሪዎች በዚያ ደረጃ የሚሆኑ እንዳልሆኑ ግንዛቤ መውሰድ እንደሚችል ገልጸዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹን ማግኘት እንዳልቻሉና በታሰሩበት ቦታ ሄደው እንደሚያገኟቸው ሲጠይቁ፣ መርማሪው ወደ ሌላ ኃላፊ፣ ኃላፊው ደግሞ ወደ ኮሚሽነሩ በማለት ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ከአሥረኛው ቀን እንዳገኟቸው በማስረዳት፣ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸውም ጠይቀዋል፡፡ አንዳንዶቹ ተጠርጣሪዎች እንደነገሯቸው (ለጠበቆቹ) እነሱ የፈጸሙት ግድያ እንደሌለና ሰላማዊ ዜጎች መሆናቸውን ነው፡፡ 

በወቅቱ የእርስ በርስ ግጭት ስለነበር ሁሉም በየፊናው ተበታትኖ እንደነበርና ስለሆነው ነገር ምንም እንደማያውቁም እንደነገሯቸው ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡ በወቅቱ በደረሰው ጉዳት ተጎጂዎች በስሜት ተነሳስተው ጉዳት ሊያደርሱባቸው እንደሚችሉ በመግለጽ፣ ፖሊስ በአንድ ማቆያ ቦታ እንዳስቀመጣቸው ገልጸው፣ የተወሰነ ጊዜ እዚያው (ማይካድራ) አቆይተው ወደ ጎንደር እንደወሰዷቸውና ከዚያም ወደ አዲስ አበባ አምጥተው እንዳሰሯቸው አስረድተዋል፡፡

እነሱ (ተጠርጣሪዎቹ) ከምንም ውስጥ እንደሌሉበትና እንዲያውም በእነሱ ላይ በተለይ በማይካድራና በጎንደር በቆዩባቸው ጊዜያቶች ኢሰብዓዊ ድርጊት እንደተፈጸመባቸው፣ በረሃብና ሕክምና ዕጦት ሦስት አብረዋቸው የታሰሩ ሰዎች እንደሞቱ ተናግረዋል፡፡ የዩኒሴፍ ሐኪሞች ለማከም ቢጠይቋቸው መከልከላቸውን ከመካከላቸው በጥይት የተመቱ እንዳሉና በክላሽ ሰደፍ ጨምሮ ድብደባ እንደተፈጸመባቸውም ተናግረዋል፡፡ 

ወደ አዲስ አበባ አባ ሳሙኤል እስር ቤት ከተዛወሩ በኋላም ሕክምናና ሌሎች አገልግሎቶችን እያገኙ እንዳልሆነና እስር ቤቱ የሚጠበቀው በማረሚያ ቤት ፖሊሶቸ በመሆኑ፣ ቤተሰቦቻቸው ሊጠይቋቸው ሲመጡ ሊያስገቧቸው እንዳልቻሉና ‹‹የሉም›› ብለው እንደሚመልሷቸው አስረድተዋል፡፡ አብረዋቸው በእስር ቤት የሚገኙ ሕፃናት ልጆቻቸው (ሰባት ናቸው) ተጠርጣሪ ስላልሆኑ ሕክምና መከልከላቸውንም አክለዋል፡፡ ይህ ሁሉ የሚደረገው እነሱን ከማይካድራ ለማፈናቀልና ንብረቶቻቸውንና ቤታቸውን ለመውሰድ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

አንዳንዶቹ ተጠርጣሪዎች በታሰሩበት ቦታ የሰጡት ቃል በምስክርነት ፎርም ላይ መሆኑንና ስለተጠረጠሩበት ጉዳይ እንዳልሆነ ጠቁመው፣ ለምስክርነት ከሆነ በአዋጅ ቁጥር 699/2003 ድንጋጌ መሠረት ጥበቃ አድርገው ሊለቋቸው እንደሚገባም ጠይቀዋል፡፡ የማይካድራው ጭፍጨፋ የተፈጸመው ቀድሞ የነበረው ኃይል ሲለቅና አዲስ የሚገባው ኃይል ሲገባ የተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ምንም ዓይነት ችግር እንደሌለባቸውም አክለዋል፡፡ 

እንደ ጠበቆቹ ገለጻ ሕፃናቱ የሥነ ልቦና ችግር እንደገጠማቸውና ሕገ መንግሥቱ፣ የአፍሪካ ሕፃናት መብቶች ቻርተር፣ ዓለም አቀፍ የሲቪልና ፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን ታልፈው መታሰራቸው ተገቢ ባለመሆኑ፣ መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸውም ጠይቀዋል፡፡ በአጠቃላይ ምርመራው በሕግ አግባብ እየተካሄደ ነው የሚል እምነት እንደሌላቸው ተናግረው፣ የተጠየቀው 14 ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ውድቅ እንዲደረግና የዋስ መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል፡፡  

መርማሪ ቡድኑ በድጋሚ ባቀረበው መከራከሪያ እንደገለጸው፣ በሌላ ቦታ ስለደረሰባቸው ነገር እሱ የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ተናግሮ፣ ቡድኑ የሚያውቃቸው ከጥር 19 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ መሆኑን አስረድቷል፡፡ ወንጀሉ በተደራጀና በቡድን የተለያዩ ስለቶችን በመጠቀምና መታወቂያ በመጠየቅ በማንነት ላይ ያነጣጠረና የተፈጸመ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ወንጀሉ በጋራ የተፈጸመ በመሆኑ ተጠርጣሪዎቹን የለዩዋቸው ተጎጂዎች መሆናቸውንና በማቆያ ከነበሩ 4,000 ተጠርጣሪዎች ውስጥ ፍርድ ቤት የቀረቡት ወንጀሉን በቀጥታ ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩ መሆናቸውን አስረድቷል፡፡ የ22 ተጠርጣሪዎች የተከሳሽነት ቃል መቀበሉንና በምስክርነት የተቀበላቸው እንደሌሉ አክሏል፡፡  

በጎንደር ሆስፒታል ኮማ ውስጥ ያሉ እንዳሉና እስከሚነቁ እየተጠበቁ መሆኑንም ተናግሯል፡፡ የሞቱትን ሰዎች በሚመለከት በቁጥር እንዳልገለጸና በ117 ጉድጓዶች የተቀበሩት ሰዎች አስከሬን ምርመራ ውጤት እየተጠባበቀ መሆኑን ጠቁሞ፣ የጠየቀው 14 የምርመራ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ ለተጨማሪ ምርመራ 11 ቀናት ፈቅዷል፡፡ የእያንዳንዱ ተጠርጣሪ የወንጀል ተሳትፎ ለይቶ ከመዝገቡ ጋር እንዲያያዝ፣ ቤተቦቻቸው እንዲጠየቋቸው እንዲያደርግ፣ ፖሊስ የተጠርጣሪዎቹን መብት ባከበረ መልኩ እንዲይዛቸው ትዕዛዝ ሰጥቶ፣ ለየካቲት 29 ቀን 2013 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ Byታምሩጽጌreporter amharic

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Ethiopia is Fighting Another Battle Today to Protect its Sovereignty
US Attempt To Make Pronouncements On Ethiopia’s Internal Affairs Regrettable :MoFA
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2